June 22, 2022
3 mins read

ልበ ደንዳና፣ አንገተ ወፍራም መሪ ፕሮፋይል እና ከቨር ፎቶ መቀየር ውስጥ ይደበቃል – ዩሀንስ ሞላ

287613935 3037034889940244 2713958192887927026 n
287613935 3037034889940244 2713958192887927026 nሕዝብ ሲቆጣ ማስቀየሻው ፎቶ መቀየር ነው። ምናልባት እንደ ተራ ፌስቡከር ላይክ ለቀማ? (በጭብጨባ ስለመጣ መጽናኛው ይሆናል) ወይ ደግሞ ለራሱም “I’m alright” የሚልበት መንገድ። ወይስ “ምን ታመጣላችሁ? ተዘቅዘቁ” የሚልበት መንገድ?
ብቻ ከዚህ ቀደም ለመጨረሻ ጊዜ ፎቶዎቹን የቀየረው January 11 እነ ስብሀት ነጋ ይፈቱ በተባለ ማግስት “እነ ስብሀት ነጋ ይፈቱ ሲባል፣ እኔም ደንግጫለሁ” ብሎ ያላገጠ እና ሕዝብ የተቆጣ ጊዜ ነበር።
289231832 7623360881038494 8116964725364439940 nይኸው ስንትና ስንት ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፎ ሲታዘን፣ ምን ታመጣላችሁ በሚመስል መልኩ ፎቶዎቹን ቀይሯል።
ይኽ ድርጊቱ እስከዛሬ ካደረጋቸው በላይ፣ ስለታየው እና ስላልታየው ማንነቱ በደንብ የሚያሳይ ነው።
ሕዝብ ፕሮፋይሉን በጥቁር ሲለውጥ፣ የሚመገበው ደም ደም ሲለው፣ ምድር ላይ ቀይ የደም አሻራ ታትሞ ሲለቀስ፣ እሱ አረንጓዴ አሻራ ብሎ መለጠፉን ታሪክ ይቅር አይለውም። የጎረቤት ለቅሶ እንኳን ይከበራል። በየትም አገር አስከሬን በክብር ያልፋል። ለእሱ ምናልባት የሰው ልጅ ዋጋ ከእንጨትም በታች ነው።
በዚህ ልክ እንዴት ልበ ደንዳና መሆን ይቻላል?
ለማንኛውም “እንደ እኔ የተሰደበ የለም” ብሎ እልሁን ቢዘረግፍም፣ እንደሱ የተደገፈ የለም።
ሕዝብ ካናቴራ አሰርቶ የድጋፍ ሰልፍ ካደረገ፣ ዛሬ አራት አመቱ።
ቦንብ ያፈነዱበት ሰኔ አስራ ስድስት ዛሬ አራት አመቱ።
ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦ “የቀን ጅቦች” ካለ አራት አመቱ።
ይገርማል ብቻ። ያኔ fbi መጥቶ ያጣራ ሲባል እንኳን ለምን ማለት አይቻልም ነበር።
ዛሬ እንጠይቅ እስኪ። ከሌላው ግድያ ምን ለይቶት ነበር ኤፍቢአይ ያጣራ የተባለው? ውጤቱስ ምን ነበር? ማን አፈነዳው? የውጤቱን ማለቴ እንጂ ውስጥ ውስጡን ተብሎ ያለቀውን ማለቴ አይደለም።
በዚያ ድንጋጤ ውስጥ ዘና ብሎ ሆስፒታል ድረስ ወስዶ ያስጠየቀው “አዛኝነቱ” ዛሬ የት ገባ?
ያኔ የቆሰሉት ግን ደህና ናቸው?
ብቻ ይኽም ቶሎ ይረሳል።
ያም ሆነ ይህ ግን የደነደነ አንገት ሁሉ መሰበሩ አይቀርም!

\

2 Comments

  1. አንተም ጎልያድን ጥለኸው በጠጠር
    መልሰህ ጎልያድ ሆነህ ብትወጠር
    ጥቂት ጊዜ አለህ ግፍህ ሞልቶ ተርፎ
    ተገፊ እስኪጥልህ በጠጠር ወንጭፎ

  2. ይሄ ሰውዬ አረመኔ ነው ሳይሞቱ ነው አፈር የመለሰባቸው እንዴት እህል ወደ አፉ ይገባል ህጻናት አሮጊቶች አቅመ ደካሞች ዋይ ዋይ እያሉበት?ጴንጤ ማለት እንዲህ ጨካኝ ነው ወይስ እምነት ሰፈር የለም? ሰው እያስገደለ ተሰደብኩ ግደሉ ብሎ ለውሾቹ ት እዛዝ ይሰጣል ጁዋርስ ከዚህ በላይ ምን አደረገ? ይስራችሁን ይስጣችሁ አሟሟታችሁ አያምርም፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

International Amhara Association Logo
Previous Story

ከዓለም አቀፍ የዐማራ ጉባኤ የተሰጠ ወቅታዊ የአቋም መግለጫ

Grave diger and Killers
Next Story

ኢትዮጵያዊነትን እያጥላሉ እና እያገለሉ  ኢትዮጵያ ማለት እንዴት ይሆናል ?

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop