June 22, 2022
3 mins read

ልበ ደንዳና፣ አንገተ ወፍራም መሪ ፕሮፋይል እና ከቨር ፎቶ መቀየር ውስጥ ይደበቃል – ዩሀንስ ሞላ

287613935 3037034889940244 2713958192887927026 nሕዝብ ሲቆጣ ማስቀየሻው ፎቶ መቀየር ነው። ምናልባት እንደ ተራ ፌስቡከር ላይክ ለቀማ? (በጭብጨባ ስለመጣ መጽናኛው ይሆናል) ወይ ደግሞ ለራሱም “I’m alright” የሚልበት መንገድ። ወይስ “ምን ታመጣላችሁ? ተዘቅዘቁ” የሚልበት መንገድ?
ብቻ ከዚህ ቀደም ለመጨረሻ ጊዜ ፎቶዎቹን የቀየረው January 11 እነ ስብሀት ነጋ ይፈቱ በተባለ ማግስት “እነ ስብሀት ነጋ ይፈቱ ሲባል፣ እኔም ደንግጫለሁ” ብሎ ያላገጠ እና ሕዝብ የተቆጣ ጊዜ ነበር።
289231832 7623360881038494 8116964725364439940 nይኸው ስንትና ስንት ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፎ ሲታዘን፣ ምን ታመጣላችሁ በሚመስል መልኩ ፎቶዎቹን ቀይሯል።
ይኽ ድርጊቱ እስከዛሬ ካደረጋቸው በላይ፣ ስለታየው እና ስላልታየው ማንነቱ በደንብ የሚያሳይ ነው።
ሕዝብ ፕሮፋይሉን በጥቁር ሲለውጥ፣ የሚመገበው ደም ደም ሲለው፣ ምድር ላይ ቀይ የደም አሻራ ታትሞ ሲለቀስ፣ እሱ አረንጓዴ አሻራ ብሎ መለጠፉን ታሪክ ይቅር አይለውም። የጎረቤት ለቅሶ እንኳን ይከበራል። በየትም አገር አስከሬን በክብር ያልፋል። ለእሱ ምናልባት የሰው ልጅ ዋጋ ከእንጨትም በታች ነው።
በዚህ ልክ እንዴት ልበ ደንዳና መሆን ይቻላል?
ለማንኛውም “እንደ እኔ የተሰደበ የለም” ብሎ እልሁን ቢዘረግፍም፣ እንደሱ የተደገፈ የለም።
ሕዝብ ካናቴራ አሰርቶ የድጋፍ ሰልፍ ካደረገ፣ ዛሬ አራት አመቱ።
ቦንብ ያፈነዱበት ሰኔ አስራ ስድስት ዛሬ አራት አመቱ።
ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦ “የቀን ጅቦች” ካለ አራት አመቱ።
ይገርማል ብቻ። ያኔ fbi መጥቶ ያጣራ ሲባል እንኳን ለምን ማለት አይቻልም ነበር።
ዛሬ እንጠይቅ እስኪ። ከሌላው ግድያ ምን ለይቶት ነበር ኤፍቢአይ ያጣራ የተባለው? ውጤቱስ ምን ነበር? ማን አፈነዳው? የውጤቱን ማለቴ እንጂ ውስጥ ውስጡን ተብሎ ያለቀውን ማለቴ አይደለም።
በዚያ ድንጋጤ ውስጥ ዘና ብሎ ሆስፒታል ድረስ ወስዶ ያስጠየቀው “አዛኝነቱ” ዛሬ የት ገባ?
ያኔ የቆሰሉት ግን ደህና ናቸው?
ብቻ ይኽም ቶሎ ይረሳል።
ያም ሆነ ይህ ግን የደነደነ አንገት ሁሉ መሰበሩ አይቀርም!

\

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop