May 24, 2022
4 mins read

“የሕግ ማስከር ሂደት ሰብዓዊ መብቶችን በመጣስ መሆን የለበትም” – ኢሰመኮ

በተለያዩ አካባቢዎች በመፈጸም ላይ ያሉ የጋዜጠኞች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎችና የሌሎች ሰዎች እስሮች
10 journos 2
Ten journalists, media personalities arrested in Bahir Dar, Addis Abeba in just Three days

የተወሰኑት ተጠርጣሪ ታሳሪዎች በቤተሰቦቻቸው የተጎበኙና በተለያየ የጊዜ መጠን ወደ ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም፤ በርካታ ታሳሪዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ መታሰራቸውን፣ ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን፣ በቤተሰብ አለመጎብኘታቸውን ተመልክቷል

10 journos 2 1200x675.jpg
Ten journalists, media personalities arrested in Bahir Dar, Addis Abeba in just Three days

የፌዴራል መንግሥት እና የክልል የፀጥታ ኃይሎች “በተቀናጀ መንገድ የሕግ በላይነትን ማስከበር” በሚል ባለፉት ጥቂት ቀናት መውሰድ በጀመሩት እርምጃ፣ ጋዜጠኞችና የማኅበረሰብ አንቂዎችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ታስረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሁኔታዎችን በቅርበት እየተከታተለ ሲሆን፤ የተወሰኑት ተጠርጣሪ ታሳሪዎች በቤተሰቦቻቸው የተጎበኙና በተለያየ የጊዜ መጠን ወደ ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም፤ በርካታ ታሳሪዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ መታሰራቸውን፣ ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን፣ በቤተሰብ አለመጎብኘታቸውን ተመልክቷል።  በተለይም በአማራ ክልል በርካታ ታሳሪዎች ከመደበኛ መኖሪያ አካባቢያቸውና ከመደበኛ እስር ቦታዎች ውጭ ጭምር በመታሰራቸው ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን እንኳን ለማወቅ መቸገራቸውን ኮሚሽኑ ተረድቷል፡፡

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕግና ሥርዓትን ለማስከበር መንግሥት በሕጋዊ መንገድ ሊወስድ የሚችላቸውን እርምጃዎች ኢሰመኮ ቢገነዘብም “የዚህ አይነት የሰብአዊ መብቶች መርሆዎችን ያልተከተለና የተስፋፋ እስር ተገቢ አለመሆኑን” የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ገልጸዋል። “በተለይም የፌደራልም ሆነ የክልል የፀጥታ ኃይሎች ተጠርጣሪዎችን ከወንጀል ምርመራ በፊት ከማሰር፣ ጋዜጠኞችን በስራቸው ምክንያት ከማሰር እና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ ሰዎችን ከማሰር ሊታቀቡ ይገባል። እንዲሁም በማናቸውም አይነት ሁኔታ የታሰሩ ሰዎች ሁሉ ቤተሰቦቻቸው ወዲያውኑ እንዲያውቁ እንዲደረግና ወደ ፍርድ ቤትም ሊቀርቡ ይገባል” ብለዋል፡፡ ዋና ኮሚሽነሩ አክለውም ኢሰመኮ በማናቸውም ስፍራ በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎችን ሁኔታ በድንገተኛ ጉብኝት ለመከታተል በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት፣ ክትትል በማድረግ ላይ ስለሆነ ሁሉም የፌደራል እና የክልል መንግሥታት አካላት ለኮሚሽኑ ሥራ የመተባበር ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

1 Comment

  1. Daniel Bekele says :

    “Federal and regional security forces should refrain from arresting suspects before criminal investigations and imprisoning journalists because of their work and arresting people irrespective of a court warrant and notify family members when individuals are arrested as well bring them before a court.”

    This is not the first time Daniel B. tells the government to refrain from violation of the constitution and other laws, but the government does not “refrain” from any of its illegal activities. Let alone refrain, t’s not even responding to his statements; it simply ignores him.

    If the government does not listen to its human rights officer, what the hell is Daniel B. doing as head of the institution? Isn’t his repeated empty cry of foul simply enabing the government to do what it wants to do more and more? If he stays as the top human rights officer who make statement with no consequences, how is he different from the arresting and torturing agents and judges that cooperate with the agents? At some stage, he should say enough.

    I feel that Daniel B. should resign from his position. He might claim that he better stay in his postion to further expose the illegal activites of the governemt. That argument might have made sense when he was appointed for the positon to verify the widely held opinion at the time that human rights situation is improvingi n the country. Two years after, it’s more than clear that the government is the worst violater of human rights the country has ever known.

    Daniel is supposed to know what to do under the prevailing situatio: RESIGN.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

FB IMG 1640090744711
Previous Story

ከ”አለም አቀፍ  ኢትዮጵያውያን የተባበረ ዳያስፖራ ጥምረት ”  የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ 

284096199 5086189774795634 4336136551388013426 n
Next Story

መስከረም አበራን በሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት እና አማራ ክልልን ከፌደራል መንግሥቱ ለመነጠል ትሰራለች ብሎ እንደጠረጠራት ለችሎት አስረድቷል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop