April 12, 2022
5 mins read

የጥፋት እሣትና ኢትዮጵያዊነት (በመኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ)

እሣት ፣ እሣት ፣ እሣት ነው ፤ ዘመኑ
የሚጋረፍ ፣ የሚለበልብ ፤ ወላፈኑ
የሚቀቅል ፣ የሚጠብሥ  ፤ ሙቀቱ
የሚያከሥል ፣ የሚያሣርር  ፤ ቁጭቱ ፡፡

………………………………………..
ጉልቻ  እየተቀያየረ  ከተረሳ  ድስቱ
አይቀርም  በእሳት  መጎርናቱ  ፡፡
ገብስ እንኳ  ፣ በወግ ካልሆነ አቆላሉ
በእሳት ፣ አራሪው ይበዛል ከብሥሉ ፡፡

…………………………………
ለዚህ ነው እናቶች ገብሥ ሲቆሉ
የአሻሮ እና የቆሎ ጉልቻን የሚያሥተካክሉ ፡፡
ለቆሎ ጥቂት አሸዋ ምጣዱ ላይ የሚበትኑ
ገብሱን ከማረር ፣ ከአሻሮነት ሊያድኑ ፡፡

………………………………………..
አገር ተገንዘብ  ወግኛውን የእሣት ጫወታ
በገዛ አገርህ ሳያደርግህ ከርታታ ና አውታታ
ዛሬ እጅግ ረቋልና  የእሣት ጫወታ

እንዳይመስልህ ሥካር ፤ የፖለቲካ ሞቅታ  ፡፡

አእምሮ ቢሱ ፣ ሲጫወት እያየህ ፣ የሞት ጫወታ ፡፡

………………………………………………
ሰው ሆይ ፣ አስተውል ፤ አትሆን አጉል ተቺ
እወቅ ፣ሚሊዮን ኢትዮጵያዊ እንዳለ ፣ ለሰው ሟቺ ፡፡
ለአምሳየው ተጨናቂ ፣ ተሟጋቺ ።
ከእሣት ጋራ ተናናቂ
እሣትን ጣይ አስወዳቂ
አለ እጅግ ብዙ ፣ ጀግና ወጣት  በአገሬ
መሰዋት ሆኖ የሚያኖረኝ በየመንደሬ  ።

(በመኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ )
ሚያዚያ 3/ 2014

 

ማሳረጊያ
( ሚያዚያ 1/2014 ዓ/ም በመኖርዬ ጊቢዬ ውሥጥ የተከሰተው ይኽ ፣ እሣት ፣ ብዙ ንብረት እንዳያወድምና ከእኔ ቤት አልፎ በአካባቢው መኖሪያ ቤቶች ላይ እንዳይዛመት ሲሉ ፤ ልብሳቸውን አውልቀው ፣ በቁምጣ ፣ ከሚጋረፈው እሣት ጋራ ተናንቀው ፣ አንድ ነፍስ ሳትጠፋ ፣ ድል ለነሱ ፣ የናዝሬት ነዋሪዎች ( ወርቅ ሰዎች ) ፣ ከቅርብና ከሩቅ መጥተው አካባቢውን ላጥለቀለቁት ና ላዘኑልኝ በሺ ለሚቆጠሩ ሰው መሆናቸውን ብቻ ለሚያውቁ የፈጣሪ ፍጡራን ሸዎች ፣ በሙሉ ፣ ይኽ ግጥም መታሰቢያ ይሁንልኝ ። በዚህ አጋጣሚ እሣቱን የናዝሬት ወጣትና ጎልማሣ በአፈር ና በውሃ ከተቆጣጠረው ከአንድ ሠዓት በኋላ የመጣው ፣ የአዳማ እሣት አደጋ መሥሪያ ቤት የሥልክ መሥመር ዕዳ አለው ተብሎ ተቋርጧል መባሉን መንግሥት አጣርቶ አሥቸኳይ የእርምት እርምጃ እንዲወሥድና በየቀበሌው ቋሚ የለሊት የየመንደር ጉብኝት በፀጥታ አካላት እንዲደረግ አሣሥባለሁ ። የመብራት ኃይል አሠራር እጅግ እየተበላሸ እንደመጣና ( እሥከዛሬ መብራቱ አልተቀጠለልንም ) ለሥራ ዳተኛ መሆኑ እየባሰ ብቻ ሣይሆን ፣ የእሣት አደጋ ሲፈጠር መሥመሩን ለማቋረጥ ፈጥኖ ባለመድረሱ ፣ የሚያሥከትለው እልቂት ወደፊት ሊኖር ሥለሚችል ፣ ከወዲሁ ቢታረም መልካም ነው ። እንደመብራት ኃይል ና እንደ እሣት አደጋ የመንግሥት ተቋም ዳተኝነት ቢሆን ኗሮ በዚህ እሣት አልቀን ነበር ። ሆኖም ለፈጣሪ እየፀለየ ባለው በፆሚው ክርስቲያን እና ሙሥሊም የናዝሬት ህዝብ ከእልቂት ተርፈናል ። ክብር ለፈጣሪያችን ። አሜን ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop