ከፋኖ አማራ በሸዋ የተላለፈ መግለጫ!

የሸዋ ፋኖ በምንጃር እና ሸንኮራ ልዩ ስሙ አውራ ጎዳና በተባለ ቦታ የኦሮሚያ መንግስት ታጣቂዎች ያደረጉትን ጥቃት አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ።

እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ መዋቅራዊ በሆነ ጥቃት ብዙ መሰዋዕትነት መክፈል ከጀመረ ከሰላሳ(30 ) አመታት በላይ አስቆጥሯል ዛሬም እንደ ትላንቱ በመንግስት ስልጣን እና መዋቅር በመታዘዝ ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አውራ ጎዳና የሚባል ቀበሌ ላይ የመንግስት ታጣቂዎች ማለትም የኦሮሚያ ልዩ ሃይል የኦሮሚያ ሚሊሻ እና የኦሮሚያ ሰላምና ደህንነት ሃላፊ በጥምረት በከፈቱት ጥቃት የአንድ ወንድማችን ሂወት ሲሰዋ 6 የሚሆንኑ ወንድሞች ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የኦሮሚያ ሚሊሻ ልብስ የለበሱ እና መታወቅያ የያዙ በባለ ሶስት ከከብ ማዕረግ ወታደር እየተመሩ መነሻቸውን መጋቢት 20/2014 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ዜጎች ላይ የቡድን መሳርያ ተኩስ በመክፈት እና አካባቢው ላይ ያሉ የፌደራል ፖሊሶችን በመግደል ወደ ሌላ ጥቃት ሊሸጋገሩ ሲሉ በጀግናው የምንጃር ህዝብ እና የሸዋ ፋኖ ትብብር ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ ቀርተዋል።

ሰላም ወዳዱ የአማራ ህዝብ የማንም ሰው ህይወት ሳይጠፋ እነዚህን ታጣቂ አካላቶች በሰላም እጅ እንዲሰጡ እና በሰላም ችግሩ እንዲፈታ ቢጠይቁም አሻፈረኝ በማለታቸው እና ተኩስ አቁሙ በሰላም እጃችሁን ስጡ ሲል የነበረን ወንድማችን ላይ በመተኮስ በመግደላቸው ብሎም ሌሎች ሰወች በማቁሰላቸው ራስን ለመከላከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ህወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

ከላይ እንደተባለው የኦሮሚያ መንግስት የጸጥታ አካል እንደሆኑ ብዙ መረጃወች እጃችን ላይ የሚገኝ ሲሆን ራሱ ገዢው መንግስት ባወጣው ህግ የማንኛውም ክልል ሚሊሻ እና ልዩ ሃይል ወደ ሌላ ክልል ያለምንም ስምምነት ወይም ፍቃድ ወደ ሌላ ክልል መግባት የማይቻል መሆኑ እየታወቀ ድንበር ጥሰው ገብተው ጥቃት ለማድረሳቸው በቂ መረጃ እያለ መንግስት ግን ግጭቱ የተፈጠረው ድንበር ጥሰው በመጡ ታጣቂዎች አማራ ክልል ላይ ጥቃቱን መፈጸማቸውን በመካድ ኦሮሚያ ክልል እንደተፈጸመ አርጎ ያወጣው መግለጫ የአማራ ህዝብን የካደ እና በሞቱት ወገኖቻችን ደም መቀለድ መሆኑ ታውቆ እንዲስተካከል ስንል እናሳስባለን በመሆኑም የሸዋ ፋኖ የሚከተሉትን ባለ 4-ነጥብ መግለጫ አውጥቷል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቅዱስ ፓትርያርኩ የወለጋና ጋምቤላውን ጭፍጨፋ አወገዙ

1) የዚህ ጥቃት ዋና አቀነባባሪ የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት በህግ እንዲጠየቁ ስንል እናሳስባልን

2) በኦሮሚያ ክልል እንደተፈጸመ ተደርጎ በየሚዲያው የሚሰጠው መግለጫ ፍጹም ስህተት መሆኑ ታውቆ የአማራ ህዝብን ይቅርታ እንዲጠየቅ ስንል እናሳስባለን።

3) ኦሮሚያ ክልል ወደ አማራ ክልል የሚደረገውን ህገወጥ ወረራ እንዲያቆም ግጭቱ የተፈጠረው አማራ ክልል ሆኖ ሳለ ኦሮሚያ ክልል እየተደረገ ፈንታሌ ቆርኬ ቀበሌ የተባለው ባስቸኳይ ማብራርያ እንዲሰጥበት እናሳስባለን

4) መላው የአማራ ህዝብ በብልጽግና መንግስት አማራ ላይ እያደረገ ያለውን መዋቅራዊ ጥቃት እውቅና እንዲኖረው ስንል ጥሪያችንን እያስተላለፍን ለቀጣይ መንግስት ሃገር በውሸት እና በሴራ እንደማይመራ አውቆ ከላይ የጠቀስናቸውን ማሳሰቢያዎች ባስቸኳይ መፍተሄ እንዲሰጥ ስንል እያሳሰብን ባስቸኳይ መፍተሄ የማይሰጠን ከሆነ ህዝባችንን ይዘን ወደ ሌላ የትግል ምዕራፍ እንደምንሸጋገር እናሳስባለን

አማራ በልጆቹ ክንድ የተቃጣበትን የህልውና አደጋ ይቀለብሳል!

ሸዋ ፋኖ!

2 Comments

  1. ፎቶው የአልቃይዳን ይመስላል። ጀርባቸውን የሰጡት ምን ሆነው ነው? አማራን ፈሪና ሽብርተኛ ለማሰኘት ነው? ይኸ የወያኔ ሥራ መሆን አለበት!

  2. Amharas have no choice other than confederation simply because federation does not work. Why?

    As a multi-ethnic country, Ethiopia will not have a fair and free election without the domination of one or another ethnic group. The way Oromo rose to power and now control the entire country through proxy regional governments is the proof. Tigreans did it for the last thirty years and Oromos have stepped in their shoes to impose similar one ethnic group rule. With their number and size of their region, Oromo rule will be much worse than Tigrean`s. Give another ten years to Oromo rule, Ethiopia will be the tail of the world by all standards of measure.

    So, it is time for Amharas to exercise self-determnation and vote on confederation. This will give them the opportunity to attract direct foreign nvestment since confederation will enable them to have economic diplomats and even have embasies abroad cutting the Oromo controlled foreign ministry diverting foreign investment to Oromia. They can also have a defense force which will protect them from foreign invaders including ethnic Oromo organizations.The Belgian model is something to explore.

    In any event, Ethiopia needs vast decentralization resembling confederation since the federalism the country has is unitarism in disguise. Controlled from the centre, it cannot develop let alone prosper.

    Tigreans have floated the idea of confederation, Amharas must follow. Tigreans know that they will not be fairly treated under Oromo rule; as a result, their choice of confederation is just. Amharas must seize the opportunity to decide their destiny via self-determination as well without wasting another decade under incompetent Oromo rule. Despite all the atrocities they have committed, Tigreans are being heard and embraced by the Oromo rule since Oromos now feel tobe the savours of Ethiopia. Falks! Don’`t be fooled!. Oromos pretend to be “savours” only if they rule the entire country as one piece. Like any other ethnic group that aspire to dominate, they are after resources. If Amharas want to be heard and embraced as Tigreans, they have to go for confederation. If confederation does not work, they have to say good bye to Ethiopia.

    It is outdated for Amharas to handg on “mama ethiopia” cry since nobody in the country is interested in it any more. What Amharas got from this cry it atrocotoes, redicule and shame. All these on Amhara because it gave them a country which they are not ready and willing to let go. If Amhara Insist on confederation, they might call the army on it to protect the unity of the country! Laghing stock.

    Amhara! Wake up and smell the coffee. Tell Oromos that you want confederation – if not confederation then separation and see Oromo crack down will soften even disappear as it did for Tigreans. But real confederation is the only wayout from the decades long quagmire. Oromo softeneing does not take anywhere.

    Try it! It will work and catapult Amhara development and growth to the sky. It will eventually liberate Oromos too from their bloody distructive path poised to takie everybody else down with them.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share