April 2, 2013
4 mins read

ሱዳንም ቀደመችን?! ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ሜሪ አርምዴ፡-

ዕድሌ ነው እንጂ ሀብት መች አነሰኝ፤
ብርቱካን ሲታደል ሎሚ የደረሰኝ፡፡

ብላ መዝፈኗ የዕድልን መጥመም ለማመልከት ነው፡፡

የዛሬ 24 ዓመት ገደማ 81ዓ.ም ክረምት ላይ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ አዲስ አበባ ላይ ሲካሄድ በመንግሥት ለሥራ ተመድቤ በጉባኤ አዳራሹ ውስጥ ነበርኩ፡፡ ያኔ ሣተናው አልበሽር የሱዳንን መንግሥት በጉልበቱ ከገለበጠ ገና ሦስት ቀናትን እንኳ አላስቆጠረም፡፡ ነገር ግን ስብሰባውን ለመካፈል ሰተት ብሎ ወደ አዲስ አበባ መጣ፡፡ ያልተገረመ ሰው አልነበረም፡፡ እኔም ያን ሁኔታ ባሰብኩት ቁጥር ሁልጊዜ ይገርመኛል፡፡ ጓደኞቹን እንዴት ቢተማመን ነበር ሥልጣኑን ሳያረጋጋ ሊመጣ የቻለው? ነው የሡዳኑ እንትን ገትሮ ያዘለት?

ዕድሜ ደጉ ዛሬ ደግሞ ልብ ገዝቶ ሀገሩን ሱዳንን ከቀውስ ሊያድን ጉዞውን ‹ሀ› ብሎ እንደጀመረ በታወቁ ሚዲያዎች እየሰማን ነው፡፡ ‹የቆዬ ሰው ከሚስቱ ይወልዳል› ይባል የለም? እንደ አንድ ለዓለም የሚጨነቅ ተራ ዜጋ የሱዳንም ጉዳይ ያሳስበኝ ነበርና ይህን ዜና ስሰማ በጣም ነው የተደሰትኩት፡፡ ‹ሰላም እንድታድር ጎረቤትህን ሰላም ያሳድርልህ› መባሉን መዘንጋት አይገባም፡፡ በዚያ ላይ ሁላችንም – እንጥቆር፣ እንቅላ ወይ እንንጣ እንጂ ሁላችንም የአዳምና የሔዋን ዘሮች ነን፡፡ የሶርያውያኝ ሠቖቓ የማይሰማው ሰው ቢኖር ሰው ሳይሆን ሣር ባይበላም ከብት ነው፡፡ በዘርና በሃይማት ጥላ ሥር ተጠልሎ ‹የኔ ወገን ካልሆነ የራሱ ጉዳይ› ማለትም ከመጥፎ ከብትነት ተራ የሚያስመድብ የክፋት ምንጭ እንጂ ሰው አያሰኝም፡፡

‹የፖለቲካ እሥረኞችን እፈታለሁ፤ ዱር ቤቴ ያሉ ብረት ያነገቡ አማፂያንን ጨምሮ ሁሉንም ተቃዋሚዎች ለሰላም ድርድር ጠርቼ እነጋገራለሁ፤ ለሀገሬ ሱዳን ለውጥ ለማምጣት ቆርጫለሁ› ባለ ማግሥት ዛሬ ጧት     ስድስት የፖለቲካ እሥሮችን በነጻ ለቀቀ – ቃሉንም በተግባር አስመሰከረ፡፡ ግሩም ነው፡፡ የንቃተ ኅሊና ዕድገትና የልቦና መከፈት ማለት እንደዚህ ነው፡፡ ለሱዳን ጽዋችንን እናንሳ!

የኞቹ ሕወሓቶችስ ከሱዳኑ መሪ ከኦማር አልበሽር የሚማሩት ነገር ይኖር ይሆን? አንዳች መንፈሳዊ ቅናት ወረር አያደርጋቸው ይሆን? ማሙሽ ከነሽበቱ መሆንን ዕርም የሚሉበት ዘመን እንደተሸሸገ ይቀር ይሆን? የኛ ያስፈራል፤ ግን ለሁሉም ጊዜ አለ፡፡

ከሃሌ ኩሉ ቸሩ መድሓኔ ዓለም ለሱዳኑ መሪ የላከውን የዕርቅና የስምምነት መንፈስ ለኢትዮጵያም እንዲልክ ሱባኤ እንግባ፤ ነገር ቢበዛ በአህያ አይጫንም፡፡ በቃኝ፡፡ (እነዚህን ጨምሮ በ297 ቃላት ያለቀ የመጀመሪያው አጭር ደብዳቤየ እንደሆነ ይመዝገብልኝ! ‹እስከመቼ›ዎች ባላችሁበት ይመቻችሁ፤ ምክራችሁ መሬት አልወደቀም ፡፡)

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop