Hiber Radio: “ቦሌ ኤርፖርት ፓስትፖርቴን የሰጠሁት ሰራተኛ አለቃዬን ላነጋግር ብሎ ገብቶ የፓስፖርቴን አንድ ገጽ ቀዶ በመጣል አንድ ገጽ ጎሎታል አለኝ፤ ቀረሁ” – ኢንጂነር ይልቃል

/

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ መጋቢት 14 ቀን 2006 ፕሮግራም

<<...አሜሪካ ለመምጣት ቦሌ ፓስፖርቴን የሰጠሁት የኢሚግሬሽን ሰራተኛ ቆይ አለቃዬን አነጋግሬ ልምጣ ብሎ ወደ ሌላ ቢሮ ገብቶ ተመልሼ ሲመጣ ፓስፖርትህ አንድ ገጽ ጎሎታል አለኝ። አንድ ገጽ ቀዶለት ነበር የመጣው። ድርጊቱ ከአገር እንዳልወጣ የተደረገ ነው ..አገሪቱም እነሱም ምን ያህል የወረደ ደረጃ ላይ እንዳሉ የሚያሳይ አሳፋሪም አስቂኝም ድራማ ነበር.. .>>

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር ወደ አሜሪካ እንዳይመጡ ስለታገዱበት ሁኔታ ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ

<<...ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በኩዌት ያሉ ወገኖቻችን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ማጣራት እያደረግን ለኩዌት መንግስትም በየኤምባሲያቸው በኩል በኢትዮጵአውያን ላይ በኩዌት ሚዲያ የሚደረገውን ቅስቀሳ ተከትሌ የጥቃት ሰለባ እንዳይሆን መብታቸው ተጠብቆ አገራቸው የሚሄዱትም እንዲሄዱ እንቅስቃሴ ጀምረናል። ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችንም ስለ ጉዳዩ እናሳውቃለን...>>

ወ/ት ሜሮን አሀዱ የዓለም አቀፉ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ተቆርቋሪ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ በኩዌት ስላሉ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከህብር ጋር ካደረገችው ቆይታ

ደብዛው የጠፋው የማሌዢያ አየር መንገድ ጉዳይ እና ያልተሳካው ፍለጋ እስከምን ይዘልቃል (ልዩ ዘገባ)

በቬጋስ ለስራ ማቆም አድማ ወጥቶ ሕይወቱ ስላለፈው የታክሲ አሽከርካሪ መታሰቢያና የተቃውሞው ተሳታፊዎች የወደፊት እርምጃ ውይይት

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

* በኦጋዴን የልማትና የኢኮኖሚ ጥያቄ ያቀረቡ የአገር ሽማግሌዎች መታሰር በአካባቢው ውጥረትና ስጋት ማስነሳቱ ተነገረ

* የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ቦሌ ላይ በድንገት ከፓስፖርታቸው አንድ ገጽ ተቀዶ ወደ አሜሪካ እንዳይወጡ የታገዱበት ሂደት አስገራሚ ድራማ ነበር አሉት

* በወላይታ ተደብድበው የታሰሩት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ትላንት ተለቀቁ

– የተነጠቁት ሞባይላቸው ባልታወቀ ነገር ተነክሮ እንዲበላሽ ተደርጓል

* አሜሪካ ከኢትዮጵያ የምትወስዳቸው የማደጎ ህጻናት ቁጥር ማሽቆልቆሉ ተገለጸ

* በአዲስ አበባ ተሳፋሪዎችን የጫነ አንበሳ አውቶብስ ድልድይ ውስጥ ገብቶ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ

* ኤርትራ በጥቂት ቀናት ውስጥ ሶስት ጄኔራሎቿን በሞት አጣች

* የአስመራው መንግስት ኢትዮጵያ አዲስ የዲፕሎማሲ ዘመቻ ከፍታብኛለች አለ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 (PDF)

6 Comments

  1. Enginer yelkal getnet.hailu shawel.beyene petros.negasso gidada.merrar gudina.bulcha demekessa.they all are fake opposition leaders who work for weyane behind curtain .and thier party is fake that they are helping weyane to show the wester world that there is a multiparty system in Ethiopia.

    • Nesanet,
      Who do you think are your real opposition figures: siye Aberha,, becket semone, Abdul’s gemeda? Please, let us know the leadership of your real opposition party? Please?

  2. Nesanet,
    Which western country(ies) believe that there is multiparty system in Ethiopia? How do you justify the presence of multiparty system: a compromise on policy, negotiated bills or a coalition in executive power!
    It would have been nice to substantiate your claim on western understanding of Ethiopian political landscape before just jotting down.

Comments are closed.

Share