ሃገራዊ ጥሪ ከ 2007 ምርጫ በፊት!

ስለ ሃገራችን ኢትዪጵያ መከራ፣ ስለ ህዝባችን ስቃይ፣ ስለ ኢህኣዴግ ግፍ፣ ስለ ተቃዋሚዎች ህብረት ኣልባ መሆን፣ ሌላም ሌላም ከሚገባው በላይ ተጽፈዋል፣ ተነግረዋል፣ ነገር ግን ያመጣነው ለውጥ የለም – እንዲያውም የባሰ መለያየት፣ መወቃቀስ፣ ማጥላላት፣ እና የኢህኣዴግን ኪስ እንዲሰፋ ኣስተዋጽኦ ኣድርገናል። ኣሁንም ኣሁንም ለውጥ ከተፈለገ እኛ ራሳችን መለውጥ ኣለብን: የሃገር ሃገራዊ ራእይ ኣግኝተን መስማማት የግድ ይላል።

ኣሉታዊ ኣስተዋጽኦ
በብልጣብልጥ እና በኣጭር ጊዜ ስልጣን ለመጨበጥ የሚደረገው ሩጫ ካለፈው 20 ኣመት እንዳየነው የትም ኣያደርስም። ለስልጣን መውጣጫ የሚደረጉ ኣስመሳይ ፈጠራዎች ሁሉም ነቅቶባቸዋል፣ ሰዎች ዝም ይበሉ እንጂ በልባችው መሳቃቸው ኣልቀረም። በዘር፣ በጎሳ፣ በጥቅማጥቅም ወዘተ የሚደረጉ ስብስቦችና መሳጥሮች ስንቶችት በታትነዋል:: በኣንጻሩ ደግሞ ኢሕኣዴግን ከነበረው ደካማነት ኣጠናክረውታል።

ስለዚ መጠላለፉ እና ሩጫው ይቅርና ረጋ ብለን ተሰባስበን፣ ተነጋግረን፣ ተመካክረን፣ ላይ ታች ብለን፣ ግዝያዊ የሃገር ኣመራር መመስረት የግድ ይላል። ወደ ሌላ ውጥን ሳንሄድ በቅድሚያ ያሉትን ድርጅቶች ተሰባስበው ግዝያዊ የሽግግር መድረክ እና ስርኣት – መመስረት ኣለባቸው። ከፓሪስ ኮንፈረንስ፣ ከኢድሃቅ ፣ ከህብረት፣ ከቅንጅት….መማር መቻል ኣለብን።

ስላለው የድሮ ታሪካችን ብቻ እያወራን እኛ ግድፈት የሞላበት ታሪክ እየሰራን መሆናችን ማወቅ ኣቅቶናል። ኣገራችን ለመጀመርያ ግዜ ወደብ ኣልባ ሁናለች (የተጀመረው ግን ከዓድዋው ጦርነት ጣልያን መረብ ምላሽ ሲቆጣጠር ነው) ፣ ገበሬዎች ከርስታቸው እየተፈናቀሉ; መሬታቸው ለባእዳን በርካሽ ዋጋ እየተክራየ ይሰቃያሉ፣ መንግስት ህገ መንግስት ተገን ኣድርጎ የፈለገው ያስራል፡ ያሰቃያል፡ ይገድላል፡ ይበትናል ወዘተ፣ ለሱዳን መሬት እየተሸጠ ነው፣ ፍርድ ቤቶች የመንግስት ፓለቲካ መሳርያ ሁነዋል፤ ታዲያ ከዚህ ሁሉ የባሰ ምን ሊመጣብን ነው። ይህን ሁሉ ማገናዘብ ኣቅቶን ለመፍትሄ መተባበር ሰንፈን መጠላለፍ ማንነታችን ኣድርገነዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የችግር መንስኤ መድኃኒት / መፍተሄ አይሆንም !!! - ማላጂ

ትምክህተኝነት ከዛም ጠባብነት እንዲሁም መጠላለፍ ኣሁን ደግሞ ሙስና ኣገሪትዋን እየዶቆሳት ነው። ከጅማሪዎች የነበረች ሃገር። ታሪኳና ባህልዋ እያከሰምን ወደ ታች ዓዘቅት እየከተትናት መሆናችን እና ጸጸቱ ኣብሮን እንደሚቀበር ማወቅ ኣለብን። ከዚህ ውርደት ተስማምተንና ተከባብረን በሰላም መኖር እንዴት ያቅተናል። ጣልያንን ያሸነፉ ኣያቶቻችን እኮ ወድ ህይወታችው ገብረው ነው እንጂ እንደኛ እየተለጣጠፉ ኣልነበሩም።

ሁላችን ማውቅ እና መቀበል ያለብን ኣንድ ድርጅት ብቻው ስልጣን ልይዝበት የሚችል ግዜ ኣብቅተዋል። እስካሁን ድረስ በነበሩት ኣስከፊ የከፋፍለህ ግዛ ስርዓቶች ምክንያት በህዝብ ላይ ነቀርሳ ፈጥረዋል። የይቅርታና የእርቅ ስራ ኣልተሰራም። ሰለዚህ መተማመን የለም። ሙሱናም የሰዎች ራእይ ሁነዋል:: ይህ ለመንቀል የተደራጀ ሃይልና ህግ ያስፈልጋል። ይቻላልም።

ስለዚህ ከዚህ ሁሉ ውጣ-ውረድ ተምረን በህይወታችን መልካም ስራ ሰርተን ለመኖር እንብቃ። ለራሳችን ቃል ገብተን እንነሳ። የሌሎች ተበደልን የሚሉትን ወገኖች ብሶት ለማዳመጥ ትእግስት ይኑረን። ያኔ ነው ተግባብተን ለመስራት የሚቀለን። ከሙሱና ነጻ ሁነንም ገለልተኛ የፍትህ ተቋማት እያስፋፋን ህዝባችንን እያስተባበርን እየተረዳን፣ መልካም ስራ በመስራት ራሳችንን ደስ ኣሰኝተን፣ ሃገራችንን እየረዳን፣ ለተተኪ ትውልድ ገንቢ ባህል እያስተላለፍን፣ ሌሎችም በድህነት ሳይሆን በክብር እንዲያውቁን ማድረግ የምንችለው።

ኣወንታዊ ኣስተዋጽኦ
ኣሁን ተቃዋሚ ድርጅቶችን የሚያጣላቸው ፕሮግራም ወይም ፓሊሲ መኖር ኣልነበረበትም: ከነጻ ምርጫ ስርዓት ጋር ተያይዞ ህዝቡ ሊቀበላቸው ላይችል እኮ ይችላል፣ ግዜው እንዴት እየተለዋወጠ እንዳለ ለምን ኣይረዱም; ቢሆንስ ፍጽማዊ የሆነ ፕሮግራም እኮ የለም ዋናው በሰላም መመካከር እንጂ።

1. በሃገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ ድርጅቶች ተባብረው ለመስራት በንኡስ ፕሮግራምም ቢሆን መስማማት ኣለባቸው።
2. በውጭ ያሉት ተቃዋሚ ድርጅቶችም የበለጠ ሰፊ ስብስብ መፍጠር ይጠበቅባቸዋል።
3. የሃገር ውስጥና የውጭውን ደግሞ የመንግስት ተንኮል ግምት ውስጥ በማስገባት ግንኙነቱ በዚህ ኣንጻር ሊከናወን ይችላል; ዋናው መተማመን እና ላንድ ኣላማ መቆም ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የድንበሩና የዐባይ ጉዳይ!! (አንተነህ ሽፈራው)

የተቃዋሚ ድርጅቶች፡ ኣንድነት (USA)፣ ሸንጎ፣ ግንቦት 7፣ ኦነግ፣ ኢህኣፓ፣ መኢሶን ሌሎችም ተባብራችሁ ማእከላይ ኣመራር መስርታችሁ፣ የውጭውን ግፊት መምራት እና በሃገር ውስጥ ላሉት ተቃዋሚዎች የሚገባውን ድጋፍ እና ኣጋር መሆን ነው። ሌላ ኣማራጭ ኣለን የሚል ካለ መልካም። ከኢሳያስ ኣፈወርቂ በኩል የሚደረግ ስልታዊ ትብብር ግን ከጠቀሜታው ጉዳቱ ከመጠን ያለፈ እንደሆነ ያለፍት 40 ኣመታት ተመኩሮ ኣስተምሮናል። የጋራ ማእከላይ ኣመራሩ ከተቀበለው ግን ልንስማማበት እንችላለን።

ልዩነትን ተቻችሎ ሀገር መገንባት
እስካሁን ድረስ እንደታዘብነው እርስ በርሳችን መጠላለፍ፣ ለኢህዓዴግ በጎሳና በዘር እየፈረጅን እኛው ራሳችን በጎሳና በዘር ተሰባስበናል፣ ተበደልን የሚሉት ሳናዳምጣቸው ኣልተበደላችሁም እንድያውም ደልትዋችሃል ብለናቸዋል፣ ብሄራዊ ማንነታችን ያለ ህብረት ሊጎለብት ኣይችልም; ህብረት ደግሞ ኣላከበርንም; ተከተሉን እናውቅላችሃለን በዝተዋል። ሀገር ለመገንባት ልዩነትን ኣቻችሎ መደማመጥ; መከባበር; ለበጎ ስራ መትጋት ይጠበቃል። ሁላችን መሪዎች መሆን ኣንችልም ኣንድ መሪ ግን ማስቀመጥ ኣለብን። ትእግስትና ስብእነት ያስፈልጋል።

ኢህኣዴግ መውደቁ ሲቃረብ የተኪው ህብረት ጎልብቶ መውጣን ደግሞ ኣይታይም፣ እንዲያውም ሻክረዋል። ይህ ኣይነት ሂደት የሶማልያ የኢራቅ የኣፍጋኒስታን የመሳሰሉትን ሁኔታዎች እንዲከሰት በር ከፋች ነውና። ኢህኣዴግ ቢውድቅ ምን የፈጠርነው ኣብሮ የመስራት ባህል ኣለና? ልዮነትን ኣክብሮ መሰረታዊ በሆኑ ኣበይት ሕጎች ኣብሮ የመስራት ጅማሮ ማሳየት ኣለብን። የጓደኝነት ይሉኝታ ኣስወግደን ዘላቂ ሃገራዊ ራኢይ ውስጥ እንሳተፍ።
ታደሰ ገብረስላሰ

2 Comments

  1. Ato tadesse I don’t agree with your article. because we can’t push the opposition to work together. they know which party or movmant to work with them. first of all you are one sided person. how can Shengo and MESON are work together. G7, EPRP and OLF( G> Kemal )they can work together they are the same strategic.

  2. We need to push each oppostion parties to gather and form a united leadership. EPRDF is much better than them to be united.
    Laikun

Comments are closed.

Share