አትሌት ሽህ አለቃ ደራርቱ ቱሉ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፈች

ጀግናዋ አትሌት ሽህ አለቃ ደራርቱ ቱሉ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት ታህሳስ 29/2014 ዓ.ም ከእስር ለተፈቱት እስክንድር ነጋ፣ስንታየሁ ቸኮል፣ቀለብ ስዮም እና አስካለ ደምሌ” እንኳን ደስ ያላችሁ፤እንኳን ለቤታችሁ አበቃችሁ” በማለት መልካም ምኞቷን ገልፃለች። አትሌቷ ከእስር ለተፈቱት አመራሮች መጭው ጊዜአቸው የተቃና እንዲሆን እና ኢትዮጵያም ሰላሟ፣አንድነቷ እና ክብሯ እንዲመለስ ያላትን ምኞት ገልፃለች።
የባልደራስ ፕሬዝዳንት እስክንድር ነጋ በበኩሉ አትሌት ሽህ አለቃ ደራርቱ የፓርቲው ፅ/ቤት ድረስ ቃሏን አክብራ በመልካም መንፈስ በመገኘት ይህንን እውቅና በመስጠቷ ከልብ አመስግኗል። በተጨማሪም “በቀጣይ በኢትዮጰያ ሰላምና ልማት ይሁን። ሲል መልካም ምኞቱን ገልጿል። ሌሎች ከእስር የተፈቱ የፓርቲው አመራሮች አትሌቷ ቃሏን አክብራ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት “የእንኳን ደስ ያላችሁ”መልዕክት በማስተላለፏ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
Source Balderas
ተጨማሪ ያንብቡ:  የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጭ የሀገራቸውን ጥሪ ተቀብለው ለመጡ የዲያስፖራ አባላት ለማስተዋወቅ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share