ከነ “ጃሥ“ከእሥር መፈታት ጀርባ ታላቅ ሤራ አለ ። ሲና ዘ ሙሴ  

ከዚህ የእሥር መቋረጥ በሥተጀርባ የተጠነሰሰ ታልቅ ሤራ እንደነበረ  ወደፊት ገለፅ ይሆናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ። ወደፊት እነ ጃሥ የራሳቸው ኃይለኛ ሤራ እንደሚኖራቸውም ይገመታል  ።

ክሳቸው የተቋረጠላቸው እነ ጃሥ ( ጃዋርና ሥብሐት ) ቆጥሮ ለመጨረሥ ዓመታትን የሚያሥቆጥር ረብጣ ብር እንዳላቸው የታወቀ ነው ና የሤራ ፖለቲካቸውን  እሥር  ቤት አቅደው ዛሬ ከእሥር ውጪ ለመተግበር ክሳቸው ተቋርጦላቸዋል ።  እናም ፣ በሤራ ፖለቲካ ፈረሥ እየጋለቡ ፣ እነዚህ  የቢሊዮን ዶላር ባለቤቶች  በታላቅ ጥንቃቄ ና ምሥጢር  ሥራ አጡን ፣ በንቃተ ህሊናው ዝቅተኝነት ተጠቅመው ለጥፋት ዓላማቸው ሊጋልቡት ና  ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ  የአገር አውዳሚነት ተግባር ሊያሠልፉት ይችላሉ ። ምናልባትም የ1969/70 ዓ/ም ቀይ ና ነጭ ሽብርን በሌላ መልኩ ሲደገም እናይ ይሆናል ። ይኽ ከሆነ ደግሞ  ። ” ኢትዮጵያ  ወይም ሞት  ! ”  የምንል ይኽ አገር አጥፊ ድርገት ሲከሰት እንደ ቀደመው ጊዜ ፣ እጃችንን አጣምረን አንቀመጥም ።

ጉዳዪ የሞት የሽረት ትግል በመሆኑ በተጋድሎ ለመሰዋት ዝግጁ እንሆናልን እንጂ፣   እንደ ቀድሞው የገዛ እጃችንን  አሥረን በማጅራታችን አንታረድም ።

ይኽ የጥቂት የመንግሥት ከፍተኛ አመራር ሥህተት  ብዙዎቻችን በማጅራታችን እንድንታረድ ለጠላቶቻችን አሣልፎ እንደሰጠን እናውቃለን ። እንዲህ አይነቱ የህፃን ድርጊት ይፈፀማል ብለን ከቶም አላሰብንም ። እኛ ተናንቀን ለመሞት የምንችለውን ብቻ ሣይሆን የወለዱንን አያሌ እናቶች የኽ መብረቃዊ ውሳኔ አሥደንግጧቸዋል ። ከተረጋጉ በኋላም አብይን እንደወደድንህ ጠላንህ ።

ልባችን ውሥጥ ነበርክ ከልባችን ወጥታሃል ሲሉ በጆሮዬ ሠምቻለሁ  ። እናት ሠላምን አጥብቃ እንደመሻቷ ፍትህም በአገር እንዲነግሥ በብርቱ ትፈልጋለች ። እናም በፍርድ ቤት ደረጃ  ፣ በችሎት ተከራክረው ፣  በወንጀል የተጠረጠሩት “ እነ ጃ – ሥ  “ (  ጃዋርና ሥብሐት )   ከተመሠረታቸው ክስ ነፃ ናቸው ። ” ተብለው ቢፈቱ ኖሮ እንዲህ ልባቸው አይሰበርም ነበር ። የፍርድ ቤት ውሳኔ በመሆኑ እና በግልፅ ጥፋተኛ አይደለንም ብለውየሚከራከሩበትን ጭብጥ ህዝብ ሥለሚያቅ ። የሁን እንጂ ፣ የፍርድ ሂደቱን ፣ ብልፅግናን ለመሪነት ያበቃው ህዝብ በአንክሮ እየተከታተለ ሣለ ና  የጀግኖች ልጆቻችን ደም ሣይደርቅ ፣   በቀጥታ ከጦርነት አውድማ ላይ የተማረኩትን ነፍሰ ገዳዮች ክስ ና በአማራ ደም የተጨማለቀ እጅ ያላቸውን የሰው ጭራቆች ክሥ  ማቋረጥ ፣  በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወንድ ና ሴትን የወለዱ  እናቶችን ልብ መሥበር ነው ። ዛሬም ሰው መሆንን በካዱ   የእንስሳ ጭንቅላት ባላቸው ፣ ደንቆረዎች አያሌ ንፁሐን ዜጎች እንደ በረሮ እየተቆጠሩ እየሞቱ ነው    ። ጠ/ሚ አብይ አህመድ  የሰጡት ምላሽም የጲላጦስን ያህል አያረካም ።

በነገራችን   ላይ ጲላጦስ  ኢየሱስ ክርስቶስን ለመልቀቅ ይፈልግ ነበር ። ህዝቡ ግን “ ሥቀሎ ! ሥቀሎ ! ይሳቀል ! ይሰቀል ! “  ብሎ በመጮሁና ወንበዴውን ፣ ጨካኙን ባርባን እንዲፈታ በመጠየቁ  ባርባንን ፈቶ ኢየሱስን ለእነሱ ለማሥረከብ ወሰነ ። ሆኖም እኔ ከደሙ ንፁነኝ ። ለማለት እጁን በአደባባይ ታጠበ። እናም እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው ። ይኽ እውነት የሚያሥተምረን መሪ ምንጊዜም የህዝብን የልብ ትርታ ለማዳመጥ ዝግጁ ካልሆነ ፣ ህዝብ ቢሳሳት እንኳን ከጎኑ ከልቆመ አወዳደቁ የከፋ እንደሚሆን ነው ።  ህዝብ ከጫፍ እሥከጫፍ ግልብጥ ብሎ ከሥልጣን ውረድ ቢልህ ምን ታደርጋለህ ?  ከሥልጣን ከመውረድ በሥተቀር ። ይልቁኑስ ማረኝ ፣ በድዬሃለሁ ። እምነትህን በልቻለው ። ብሎ በአደባባይ ይቅርታ መለሠን ያዋጣል ። እንደ እውነቱ ከሆነ ፣ ጠለ/ሚ ክስ ማቋረጥ ብቻ ሳይሆን በፍፁም ምህረት ከእሥር ቤት መፍታት ያለበት ፣ ለሰዎች ሰብአዊ መብተ ና ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ተሞጋቺ  ጋዜጠኛ እሥክንድር ነጋ ብቻ ነበር ። ከእርሱ ጋር በርባኖችን ደባልቆ መፍታቱ ጠ/ሚ አብይን ጲላጦስ አያሰኘውም ።  …

ተጨማሪ ያንብቡ:  በፍቅር ልንወድቅ የሚገባ ከማሸነፍ ወይስ ከትግል አይነት። (ዳዊት ዳባ)

ከዚህ አንፃር ክስ የተቋረጠላቸው የተፈቱበት ግልፅና አሳማኝ አይደለም ። ይላል ህዝብ ። ጠ/ሚሩም የሰጡት ምላሽ   እጅግ የተምታታ ነው ። ወንጀለኛ በዕድሜው ና በጤና ችግር  የተነሳ ይፈታ ከተባለ በሺ የሚቆጠሩ እሥረኞች ከኦቦይ ጋር መፈታት ነበረባቸው ። …

ደሞም አንዳንድ የምናከብራቸው ምሁራን እንደሚሉት ፣ ይኽ የንግድ ወይም የፖለቲካ ቢዝነስ ጉዳይ አይደለም ። “ እናተርፋለን ። እንከሥራለን ።  “ የሚባል ጉዳይ እዚህ ላይ አይሰራም ። ወዳጄ በህይወት ጉዳይ ውሥጥ ቃላት ሥንጠቃ ና አይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁም ቦታ የላቸውም ። ጉዳዩ እኮ  ፣ ህይወታቸውን ገብረው የአፋርና የአማራን ህዝብ ነፃ ያወጡ  ፣ የመከላከያ ሠራዊት  አባላት ጉዳይ ነው ። የጥቃቱ ሰለባዎች  የአፋርና የአማራ ልዩ ኃይል ጉዳይ ነው ። የአማራ ፋኖ ና የአፋር ወጣት አርበኞች  ጉዳይ ነው ።ይኽ ጉዳይ  የኢትዮጵያ ፍቅር የሚያንገበግባቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ የእሸቴ ሞገሶች ጉዳይ ነው ። ይኽ ጉዳይ የጥቂት ተሸላሚ ጀግኖች ጉዳይ ብቻም አይደለም ። ጉዳዩ ልጥቂት ከሞት የተረፉ ጓዶቻቸው የጦር ሜዳ ጀብዷቸውን የሚመሠክሩላቸው  በይፋ ያልተሸለሙ ፤ በይፋ ሥማቸው ያልተጠራ ፤ የአያሌ የጦር አመራሮች ፣ የአያሌ መሠረታዊ ወታደሮች ደም ና አጥንት ጉዳይ ነው ። ይኽንን መሠዋትነት ያቃለለ መሪ ለአንድ ቀንም ቢሆን ሥልጣን ላይ መቆየት የለበትም ።   ማንም ከኢትዮጵያ በላይ አይደለምና !!!!!!!!!!    )

በነገራችን ላይ ኦቦይ በግል   አብይን ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው  ። ዶክተሩም ፣ ይቅር ለእግዜር  ሊሏቸው ይችላሉ ። ዶ/ር አብይ በኦቦይ ሥብሐት በግልፅ ተሰድበዋል ። የጨዋነታችን ሥነ ምግባር ሥለማይፈቅድልኝ የኦቦይን  ሥድብ አልደግመውም ።  በዚህ ሣቢያ ግን ዶ/ር አብይ   በኢትዮጵያ ጠ/ ሚኒሥተርነታቸው   ፣ የአውሬ ና የጭራቅ  ድርጅትን ደግፈው ፣ ዘግናኝ ድርጊት በመከላከያ ላይ  ” ሀ ”  ተብሎ የፈፀም ዘንድ አባሪ ና ተባባሪ ሆነው መቀሌ ከተማ ሰዘባነኑ  እና ውሥኪ ሲራጩ  የነበሩትን ፣ ሰውነትና የሰው ክብር ምን እንደሆነ የማይገነዘቡ  ደናቁርታት ክስ እንዲቋረጥ  ማድረግ ግን አይችሉም ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፈጣሪ ፊቱን ወደ ሰው ይመለስ ዘንድ ፤ ሰው ሁሉ  ፤ በነገር ሁሉ ፣ እግዛብሔርን ማስቀደም አለበት - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

” አይ ! ነገሩ ወዲህ ነው ። አሜሪካ  በምላሹ ፣ ኢትዮጵያን ወደ  አገዋ   ( AGWA ) መልሳ በማሥገባት  እንደ መንግሥት ከተደቀነባት ዘርፈ ብዙ ችግር አንዱ ና ዋንኛውን እቀርፍላቸዋለሁ ፣ ብላ ቃል በመግባቷ ነው ። ” ከተባለም ፣ እርሱ ሱሚ ነው ። አሜሪካ የደርግ ጀነራሎችን በፎርጅድ ዶላር ሣይቀር ገዝታቸው እንደነበር አሥታውሥ ። ሲአይ ኤ  እንደ ኬጂቢ በራሱ ሰው አይቀሳቀሥም ። እንቅሥቃሴው በራሳችን ሆዳም ምሁራኖች ፊት አውራሪነት የሚታገዝ ነው ። ይኽም ከቅኝ ገዢነት ና ተገዢነት ልምድ የተወሰደ አሠራር ነው ። ቅጥረኞችም    ዶላር ና ምቾት አምላካቸው የሆነ   ከፍተኛ ባለሥልጣናት ናቸው   ። የልጆቻቸውና የሚስቶቻቸው የእረፍት ጊዜ  ፣ አሜሪካና ዱባይ  እንዲሆን የሚሹ   ።በጥቂት ወራት ቢሊዮነር ለመሆን የሚፈልጉ  የሲአይኤ ልጆች ናቸው የአሜሪካ መንግሥትን ግብ የሚያቁት ።

የሲአይኤ ቲያትር ዛሬ ነው ግልፅ ሆኗል ። ይኽንን ቲያትር አሣምረው የሚያውቁት እነሥብሐት በአሜሪካ ሚሥጢራዊ ሠራተኞች ( ተላላኪዎች ) በታላቅ ምሥጢር በመጠቀም ከእሥር ተፈተዋል ።

እንደምታውቁት    ከአሸባሪ ድርጅት ጋር አሜሪካ አትደራደርም ። ይሁን እንጂ የእኛን ህግ ና የፍትህ መንገድ ፈፅሞ አትቀበልም ። አሜሪካ ሁሌም የምታየው ጥቅሟን ሥለሆነ ሆዳም ና ደንቆሮ በለሥልጣናትን ( ከጥበብ የራቁ ለማለት ነው ።) በገንዘብ ና በጥቅማ ጥቅም በመግዛት ፣ የብዝበዛ መንገድ ለማግኘት ብርቱ ጥረት ታደርጋለች ። ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ። የሚለውን ጥቅሥ እዚህ ላይ አምጣው ። ከመጣኸው ዘንድ የነሥብሐትም እሥር ከጅምሩ ድራማዊ ነበር ። ሾ ነበር ። እንዴት ብትል ፣  ለሽብር ተሠልፈው ፣  ለጥፋት ሠራዊቱ ለትህነግ ወታደራዊ ክንፍ ፣  የሞራል ሥንቅ በመሆን ፣ በአፋርና በአማራ ህዝብ ላይ  ከፍተኛ ጥፋት ካደረሱ በኋላ ፣ ለዘላለም ለመኖር አቅደው እኮ ነው ፤  ከገቡበት ዋሻ ለመውጣት የፈለጉት  ። ከቢሊዮን ያላነሰ ብር እያለኝ እዚህ ዋሻ ውሥጥ በችግር ና በችጋር ለምን እሞታለሁ ብለው ፤  የነገ መውጫቸውን በማሥላት እኮ ነው ፣ እጃቸውን የሰጡት ።  በብር ወደ ጥልቁ ታዝለው ገቡ በዘዴ ከጥልቁ ወጥተው በቂሊንጦ ሆቴል በታላቅ እንክብካቤ ኗረው ፣ ዛሬ፣ ወደ  ተደላቀቀ ቪላቸው በክብር ተሸጋገሩ  ። …

በሚገረም  መልኩ ፣ ከምቾትና ከመድሃኒት አቅርቦት አንፃር ፣  ህይወታቸው አደጋ ላይ በመውደቁ ፣ ራሳቸው ያሉበትን ቦታ እንዲጠቆም በመፍቀድ መልክተኛ ልከው   ፣ በታላቅ ጥንቃቄ በመከላከያ ሠራዊታችን  ፣ ” ከጥልቁ ምሽግ ”  ታዝለው   በመውጣት  ፣ ለፖለቲካ  ትርፍ ሲባል ፣ ድራማዊ   በሆነ መልኩ ፣   እጃቸው በሰንሰለት ታሥሮ ካየን በኋላ ፣ ወዲያው ደግሞ  ቁጭ ብለው እየሳቁ ቁርጥ ሥጋ ሲበሉ በኢቲቪ  ያየነው እውነታ እዚህ ላይ አክለህ ፣ እውነቱን ተረዳ ።  ተረዳህ ? ግባልኝ  !!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ባንዳ ሆይ ይብቃህ! ይብቃህ!

እናም የኢትዮጵያ መሪዎች  እራሳችሁ ተሞኝታችሁ እኛን አታሞኙ ።  የአሜሪካ መንግሥት የሚፈልገው ፣ በእፍኝ  ሰጥቶ በቁና መቀበልን ነው ። እናም በሰፊው ለመበዝበዝ ፍቃደኛ ሁኑ ። ቻይናንን ፊት ንሱ  ። የአሜሪካ ካምፓኒዎችን በከርሰ ምድርህ ሀብታችን ላይ አሰማሩ ። ለ1% ቱጃሮች ቢዝነሥ ዋሥትና ሥጡ ። በመንግሥት  ሁሉም ፖሊስ ላይ ፣ ፈላጭ ቆራጮቹ እነሱ እንዲሆኑ አድርጉ ። ይኽንን ካደረጋችሁ ዓለም በጎናችሁ ታልፋለች ።  ( ጥቂቶቻችሁ አሜሪካና አውሮፓ ለዘር ማንዘራችሁ የሚሆን የግል ትውልዳችሁ ሳይለፋ ፣ ሳይጥር ና ሳይግር ተደላቆ የሚኖርበት ቢሊዮን ዶላር ይኖራችኋል ።) ሲአይ ኤ ለራሱ ከምፓኒዎች ጥቅም ሲል  መከላከያን  ያዘምናል ። በአፍሪካ  ከግብፅ ቀጥሎ ፈርጣማ ጡንቻ ያለን ተከባሪ ና ተፈሪ   ጦር እንድንገነባ ያግዛል  ። ከኤርትራ ጋርም በኮንፊደሬሽን ማዋሃድ ለእርሱ ቀላል ነው  ። ሁሉን በነሱ ቁጥጥር ካደረግህ ፣ ሁሉን እንደሚሰጡህ  ዕወቅ ። እነሱ ናቸውና  የባህር በር ያሳጡህ ፤ መልሰው ራሳቸው የሚቆጣጠሩት የባህር በር  ያሰጡሃል  ። በአፍሪካ ውሥጥ የትኛውም የባህር በር የእንግሊዝ ፣ የፈረንሳይ የአሜሪካ ና የጀርመን ጥቅም ማግኛ መሣሪያ ነው ። ደግሞም  በሤራ ቲዎሪ ራሻና  ቻይና ጫፋቸው አይደርሱም ።

የአሜሪካ  ሤራ ደግሞ ከሁሉም የላቀ ነው ። በቢሊዮን ዶላር  የሚታገዝ ከመሆኑም በላይ እጅግ የረቀቀ  ነው ።  ሤራው  ከላይ  ባነሳሁት ” የቢሆናል ሃሳብ ”  ብቻ የሚቋጭ አይምሰልህ ። ሌላም የቢሆን ሃሳብ አለኝ ።

አሜሪካኖቹ በሲአይኤ አማካኝነት  አንድ ሺ አማራጭ ፣ የሤራ ረቂቅ  ይዘው ነው የሚደራደሩት ። የሤራ ረቂቅ ንድፉም  ፣ በየጊዜው የሚከለሥ ነው ። እቅዱም  ራሱን የቻለ ቡድን ና አሥፈላጊ የሆነ የሎጀሥቲክ  ድጋፍ ያለው  ነው  ። ዋና መሪው ደግሞ ሲአይኤ ነው ። ( መአከላዊው   የአሜሪካ የስለላ ድርጅት ) እንበልና   ፣ ከሲአይኤ  ከአንድ ሺ አንድ እቅዱ አንደኛው ዕቅድ ደግሞ ጠ/ሚር አብይ አህመድን በቅጥር ነፍሰ ገዳይ ማሥገደል ና   ፣ ሁነኛ የአሜሪካ መንግሥት ሎሌ ወይም በሪሞት ኮንትሮል የሚያንቀሳቅሱት  አሻንጉሊት  መንግሥት  በመንበሩ ማሥቀመጥ ቢሆን እና ይህንን የነፍስ ግድያ እቅድን ሲተገብሩ የሚያሳይ  ረቂቅ የአኒሜሽን ቪዲዮ ለጠቅላዩ  ቢያሳዮቸው    ፣ ጠቅላዩ  ይኽንን እውነት ከተረዱ ”  የት ድረሥ መሄድ እንደምትችሉ በቪዲዮ ምሥል ተደግፋችሁ ካሳያችሁኝማ ፣ ቻይናም ሆነች ሩሲያ እኔን ማዳን እንደማይችሉ  በበቂ ሁናቴ  ተገንዝቤያለሁ ። ትዕዛዛችሁን ለመፈፀምም ዝግጁ ነኝ ። ”  ቢሉ ምን ይገርማል ።

 

4 Comments

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share