የአሸባሪው ህወሓት ኃይሎቹ ወደ ትግራይ እንዲመለሱ ማዘዙን ለተመድ በደብዳቤ ገለጸ

የአሸባሪው ህወሓት ሊቀመንበሩ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በኩል ለተባበሩት መንግሥታት በጻፈው ደብዳቤ ኃይሎቹ ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለሱ ማዘዙን ገለጸ።
የህወሓት ኃይሎች ካለፈው ዓመት ሰኔ ወዲህ ከትግራይ ክልል ባሻገር ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በመግባት በርካታ ቦታዎችን ተቆጣጥረው ውጊያ ሲደረጉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ኅዳር ላይ መንግሥት የመከላከያ ሠራዊቱን፣ የክልል ልዩ ኃይሎችንና ሚሊሻዎችን በማቀናጀት ባካሄደው መጠነ ሰፊ ዘመቻ በርካታ አካባቢዎችን መልሶ ለመቆጣጠር ችሏል።
በህወሓት መሪዎች በኩል ግን ኃይሎቻቸው እንዲወጡ የተደረገው “በስልታዊ ውሳኔ” መሆኑ የተገለጸ ቢሆንም፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የሆኑት ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ ለቢቢሲ “አማጺው ሽንፈት ገጥሞት” ይዟቸው ከነበሩ ቦታዎች እንዲወጣ መደረጉን ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ታሪካዊቷን የላሊበላ ከተማን ጨምሮ በርካታ የሰሜን ወሎ አካባቢዎችን ከአማጺያኑ ስር በማውጣት መቆጣጠሩን መንግሥት ያስታወቀ ሲሆን፤ የቀሩ አካባቢዎችን መልሶ ለመያዝ ዘመቻው እንደቀጠለ በተነገረበት ጊዜ ነው የህወሓት ሊቀ መንበር ደብዳቤ መጻፋቸው የተሰማው።
ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ለመንግሥታቱ ድርጅት ትናንት እሁድ ታኅሣሥ 10/2014 ዓ. ም. ጻፉት በተባለው ደብዳቤ ላይ ኃይሎቻቸው ከትግራይ ክልል ውጪ ከነበሩባቸው አካባቢዎች “ለሰላም ዕድል ለመስጠት” ለቀው እንዲወጡ ማዘዛቸውን አመልክተዋል።
ይህም ውሳኔ “ወዲያው ተግባራዊ” እንደሚሆን በደብዳቤያቸው ላይ አመልክተው፤ በአስቸኳይ ግጭቶች ቆመው ድርድር እንዲጀመር ጠይቀዋል።
BBC

https://amharic.zehabesha.com/debretsion-appeal-to-un-secretary-general-anthony-gutierrez-for-peace-negotiation-with-ethiopia/

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፓርላማው የሚኒስሮች ም/ቤት መመልከት የሚገባው ረቂቅ አዋጅ ላይ መወያየቱ ጥያቄ አስነሳ

1 Comment

  1. ቆይ ግን የትግራይ ልጆችና የወያኔ ደጋፊዎች የትኛውን ወሬ ነው አምነው ከወያኔዎች የሚቀበሉት? ጦርነቱ አልቋል፤ ከማን ጋር ነው የምንደራደረው፤ ከቤትህ እንዳትወጣ እንዳላሉን አሁን ደግሞ ዞረው ተመልሰው ስልታዊ ማፈግፈግ አረግን ብለው በተናገሩበት በቀናት ውስጥ ሰራዊታችን ከአፋርና ከአማራ ክልል አስወጥተናል ይላሉ። ወያኔ ማለት ውሸት ተግቶ ሌላውን የጋተ አንድም ነገሩ የማይታመን፡ የሰውን ሥጋ እንደ ቄራ ከብት የሚቆራርጥ ፍጽም አረመኔ ቡድን ነው። ይህ በትግራይ ህዝብና በቀረው የሃበሻ ምድር ሰቆቃ ሲያዘንብ የኖረው የማፊያ ቡድን ጥርቅም ሰላምን ጭራሽ አያውቃትም። በቅርብ አንድ የድሮ ከፍተኛ ባለስልጣን ከነበረ የአሜሪካ ዲፕሎማት ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ ስንጫወት እንዲህ አለኝ። ገና በለንደን ድርድር ሲደረግ የወያኔ ተወካዮች ይሰጧቸው ከነበሩት አስተያየቶች የተረዳሁት “ኢትዮጵያ ጠል መሆናቸውን ነው” በማለት ነበር ያጫወተኝ።
    አይገርምም አሁን ድረሱልኝ በማለት ለእልፍ ሃገራትና የመንግስታት ተጠሪዎች ደብዳቤ የጻፈው ይህ ድርጅት አሁን ደግሞ የመቀሌን ወጣቶች እያደራጀን ነው በማለት መልሶ ሲለፈልፍ ምን ለማለት ፈልጎ ነው። የትግራይን ህዝብ ማንም አይነካም። ግን ወያኔ ራሱን ለማዳን መወሸቂያው የትግራይ ህዝብ በመሆኑ መጡብህና መጣንብህ እያሉ ሰውን ያጫርሱታል። የትግራይ ህዝብ ሊነቃ ይገባል። በቃ በማለት ወያኔን ሊፋለመውና ሊፋረደው ይገባል። ከውጭ ሆነው የስማ በለው ጥሩንባ እየነፉ ድላና እሳት የሚያቀብሉት የትግራይ ልጆችም እውነትን ፈትሸው ከእውነት ጎን መሰለፍ አለባቸው። በጅምላ አስተሳሰብ 50 ዓመት ሙሉ መነዳት ጤነኝነት አይደለም። ወያኔ አውሬ ነው። በአፋር፤ በወሎ፤ በጎንደርና በሽዋ ምድር ያደረሰውን ጭፍጨፋና ዝርፊያ ማየት ተገቢ ነው። ወያኔ ከስልጣን ወርዶ በምትኩ የትግራይ ህዝብ ያለምንም ፍርሃትና የጠበንጃ ጋጋታ የራሱን ወገኖች መርጦ መኖር እስካልቻለ ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም አይኖርም። ወያኔ ሰላምን አያውቃትም። የአሁን የሰላም ጥሪ ይህ ሁሉ እብደት ሳይከሰት ከእናቶች እንባ ጋር ቀርቦለት አናንቆታል። ካህን ከቤ/መቅደስ፤ ሸሁን ከመስጊድ እያወጣ የረሸነ የዘር ሰካራም እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ሰላምን የሚቀበለው?
    አሜሪካኖችና የአውሮፓ እውራን መንግስታትና የተራዶ ድርጅቶች ከወያኔ ጋር የሚያብሩት ሰርቀው ያበሏቸው ስለነበርና ተላላኪዎቻቸው ስለነበሩ ነው። ለትግራይ ህዝብ አይገዳቸውም። ያ ቢሆን ኑሮ 27 ዓመት በስልጣን ላይ ወያኔ እያለ የሚጠጣ ውሃ እንኳን በትግራይ ባዳረሰ ነበር። እነዚህ የአድዋ ስብስቦች አሳፋሪ ፍጥረቶች ናቸው። በምንም ሂሳብ ወያኔ በትግራይ ህዝብ ጀርባ ላይ እያለ የትግራይ ህዝብ በሰላም መኖር አይችልም። አሁን ብለው ብለው ሻቢያ ድሮን ልኮ ደበደበን እሰማለት ደርሰዋል። የትግራይ ቲቪን ለተመለከተ ዛሬም ታንቡርና ክራር እየመቱ ጀጋኑ ሲሉ መስማት የጠራ ጭንቅላት ላለው ገዳም አስገብቶ ያስመንናል። ለነገሩ በወያኔ ጊዜ ገዳሙም ተደፍሯል። አታድርስ ነው ጀግናው የትግራይ ሰራዊት እንዲህ አርጎ እንዲያ አርጎ ሲሉ አለማፈራቸው። የትግራይ ሰራዊት ማለት ናዚ ጀርመኒ ማለት ነው። ለእንስሳትና ለእጽዋት እንኳን የማያዝን የመከራ ምንጭ። እንዴት ሰው መሬት ላይ ያለውን ግድ አይቶ ከእውነት ጋር ተሰልፎ እነዚህን አሪዎሶች በስማቸው ሰይጣኖች መሆናቸውን አምኖ መቀበል ያቅተዋል? ግን በቋንቋውና በዘሩ በተዘረፈ የሃገር ሃብት ለሚኖሩ የትግራይ ታጅሮችና የወያኔ ፍርፋሪ ለቃሚ አማራና ኦሮሞዎች እውነት አትታያቸውም ሆዳቸው እንጂ! የትግራይ ህዝብ ማወቅ ያለበት ዝምታም ከወያኔ ጋር መተባበር እንደሆነ ነው። እናውቃለን ወያኔ በሰንሰለት ያሰረው ህዝብ እንደሆነ። ይህን እርግማን በጥሶ መውጣት አለበት። ደግሞም የትግራይ ህዝብ ከፈለገ ይችላል። በወሎ ህዝብ ላይ ወያኔ የፈጸመው ግፍ ሰማየ ሰማያትን አልፎአል። በአፋር የተደረገው አሰቃቂ ጭፍጨፋ ትውልድ አይረሳውም። በሽዋ እናቶን የደፈረው የወያኔ መንጋ ህሊና የለሽ የከብቶች ጥርቅም ነው። በጎንደር በአንድ ቤት ውስጥ መላ ቤተሰብን በልተው ጠጥተው መረሸናቸው ወያኔ ዛሬም ወደፊትም ከአራዊቶች መንጋ የሚመደብ መሆኑን ያሳያል።
    አሁን ደግሞ ይባስ ተብሎ እንደራደር። በፊትም ተናግረናል። የአሜሪካው ጥሩንባ፤ የአውሮፓው ኡኡታ፤ የወያኔው ግፍ የሚገታው እሳትን በእሳት መፋለም ሲቻል ብቻ ነው። አሁን በ 11ኛው ሰአት እንደራደር ማለት ምን ማለት ነው። ትግራይ እኮ ሃገር አይደለችም። የአንዲት ሃገር ክፍለ ሃገር እንጂ። ተመድ በዚህ ምን አገባው? አውቃለሁ እንገነጠላለን ይላሉ እሰይ አርጎት ነው ጭልጥ በሉ። እናንተን አልባ ኢትዮጵያ የሰላም ሃገር ትሆናለች። ስልጣን ላይ እያለ ያልዘመረውን የመገንጠል መዝሙር አሁን ወያኔ ያላዝነዋል። እኮ በል ሂድና እንይ። ገና ከምስረታችሁ ተግባራችሁ ሃገር ማስገንጠልና ማፍረስ ለመሆኑ ያወጣችሁት ህገ መንግስት ቁልጭ አርጎ ያሳያል። የኢትዮጵያ መንግስት ከወያኔ ጋር የሚያደርገው ሚዛን የለሽ ድርድር ራሱን ወያኔ ያረገዋል። የተዘረፈውን ሁሉ የሊጥ እቃ ሳይቀር ማስመለስ አለበት። አውሬው ወያኔ ሙሉ ትጥቁን መፍታትና ሌላ አዲስ ሃይል የትግራይን ሰላም ማስከበር አለበት። ለወደመው ለተዘረፈው ሁሉ ማጣጫ ከኢትዮጵያ ህዝብ በትግራይ ህዝብ ወይም በራሳቸው ስም በውጭ ሃገራት ያካበቱት ሃብት ተመልሶ ለትግራይ ህዝብና ወያኔ ላፈረሳቸው ተቋማት መልሶ መገንቢያ እንዲሆን መደረግ አለበት። ወያኔ በየዓለማቱ የደበቀውን ገንዘብ ለመፈለግና ለማግኘት ከሁሉ ክልል ትግራይን ጨምሮ የተወጣጡ ባለሙያዎችን በማዋቀርና በየአለማቱ ያሉ የህግ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወይም ሌሎችን በመጠቀም ቆፍሮ ማውጣት ይቻላል። ከዚህ ውጭ ዝም ብሎ ጦርነት ይቁም ማለት ለወያኔ ጊዜ መስጠትና ራስን ለዳግመኛ ወረራ ክፍት ማረግ ነው። የአማራውና የአፋሩ ህዝብ ማወቅ ያለበት ዳግም በወያኔ ሊወረር እንደሚችል አምኖ መሰልጠን፤ መታጠቅ፤ ለህግ ተገዢ ሆኖ አንድ ለአንድ ተደራሽ የሚሆንበትን ሁኔታ ማመቻቸትና በአንድ እጅ ትጥቅ በሌላው መዶሻና አካፋ ሌላውንም የሥራ ተግባሮችን መፈጸም አለበት፡፡ ወያኔ እያለ ሰላም በጭራሽ አይኖርም። ለምሳሌ አንድ ገበሬ ሲናገር ኦነግ ሸኔ ሚስቴን ከወሰድብኝ ወራት ተቆጠረ ይላል። እነዚህ ናቸው የኦሮሞን ህዝብ ነጻ የሚያወጡት? የእህል ክምር አቃጣዪች። ስለዚህ ዝም ብሎ ማሪያም ድረሽልኝ፤ ፈጣሪ ያወጣኛል ማለት ሁሉ ጅልነት ነው። ተዘጋጅተው እየተዋጉ እንዲያ ቢሉት ፈጣሪም ሊረዳ ይችላል። በር ዘግቶ መቀመጥ፤ ወይም ከተማንና መንደርን ጥሎ መሰደድ ጭራሽ የማያዋጣ ምርጫ መሆኑን አሁን ወደ ቤታቸው የተመለሱ ሰዎች ተረድተውታል። ሴት ወንድ ልጅ ሽማግሌ አሮጊት ሳይባል ወራሪዎችን ለማጥፋ ዝግጅት መደረግ ያለበት አሁንም ወደፊትም ነው። ከዚህ የወያኔ ክፋት የማይማርና አቋሙን የማያስተካክል ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ አይነ ሰውር ነው። እልፍ ግፍ ተሰርቷል። ሴቶች ለመድፈር ታግለው እምቢኝ ሲሉ ተገለዋል፤ ቆስለዋል። ጣሊያን ይህን አላረገም። ወያኔና የትግራይ ወራሪ ሃይሎች ግን ፈጽመውታል። መነኩሴ የሚደፍሩ ጎዶች። ለመብቱ የማይቆም ህዝብ ሁሌም በባርነት ይኖራል። ወያኔ 27 ዓመት ሙሉ ህዝባችን በባርነት ውስጥ አኑሮታል። አሁንም የሚሻው የራሱን የበላይነት ነው። እንታጠቅ፤ እንዘጋጅ፤ ይህ ትጥቅና ዝግጅት ግን የግፍ በትር አይሆን። ከግፍ መከላከያ እንጂ።
    ማሳሰቢያ።
    እኔ የሃበሻው ህዝብ ለሥጋ ያለው ፍቅር ይገርመኛል። እንዲያው ለእንስሳቱም አታዝኑም እንዴ? ወያኔ አርዶ ሲበላቸው፤ ሌላውም ያለ ሥጋ አይሆንልኝም ሲል፤ ለጦሩ እየተባለ የሚቀርቡት ሁሉ አያሳዝኑም? እንዴት ሰው ሥጋ እየበላ ሥጋ ለባሽን ይገላል? ኸረ ተው ይህ ሥጋ መብላት የጤና አይደለም። ደግሞስ የሚታረድት የቁም እንስሳት ቁጥራቸው እትየ ለሌ ከሆነና በድርቁ ሳቢያ የሚረግፉት እንስሳቶችን ጨምሮ ሲፈለግ የሚበላ ቢታጣ ምን ልትሉ ነው። እንደ ሞኙ ገበሬ ለዘር ያስቀመጣችሁትን ልትበሉ ጥቂት ነው የቀራችሁ። ሥጋ መብላት የቅንጦት ምልክት አይደለም። የበሽታ እንጂ። በልኩ ይሁን። ለእንስሳት ያላዘነ ልብ ለሰው ህይወትም አያዝንም።
    ሌላው ለከያኔዎች ገጣሚችና ለአዝማሪዎች ነው። ኦ ለካ አሁን አዝማሪ አይባልም። ግራም ነፈሰ ቀኝ የቂጥሽ የባትሽ፤ የጡትሽ ሞትኩልሽ የሚለው ዘፈናችሁ ቋቅ ብሎናል። የጥበብ ሰዎች አንድ ብልሃት ጊዜን ተደግፈው የሚሰሩት ሥራ ነው። አሁን መሰራት ያለበት ስለ አፋር ጀግኖች፤ ስለፋኖ ተጋድሎ፤ ስለ ሰራዊቱ ተጋድሎ፤ ስለ ሃገር አንድነትና ህበረት ጠላትን ለመመከት መሆን ይኖርበታል። አውቃለሁ ከቴዲ ጀምሮ እነ ዳኜ ዋለ፤ ወንዲ ማክ፤ ሰማኽኝ በለው፤ ዲበኩል ታፈሰና ሌሎችም ለሃገርና ለወገን ልብን ሞቅ የሚያደርግ ሥራ እየሰሩ ነው። በርቱ እላለሁ ለእናተ። ሌሎችንም ዝም አትበሉ ገጣሚውም ይጻፍ፤ ተናጋሪውም ይደስኩር፤ አስተማሪውም ያስተምር። የፍቅሩን ዘፈን ፍቅር ሲሰፍን ትዘፍኑታላችሁ። ለአሁን ቆም ይበል። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share