ጦቢያ እናቴ !

ጎብጣ የምትቃና በመከራ አልፋ
ወድቃ የምትነሳ ከፊት ተሰልፋ
እጇን ከቶ አትሰጥም ዛሬን ተሸንፋ
ምኞቷ ሳይሰምር ሳትቀመጥ አርፋ
የመከራው ማእበል ችግሯም ቢበዛ
ውጣ ዝም የምትል አቅልላ እንደዎዛ
ተመስገን የምታውቅ ፈጣሪውን ይዛ
የነገን ተስፋውን በሆዷ እርግዛ
ቁንጅናዎ ቢረግፍ ወዘናዎ ደርቆ
ስጋዎ ቢከሳ ከላይዎ ላይ አልቆ
ሐዘን ቢበዛባትም ነፍሷን እስጨንቆ
የእናትስ ምርቃት መሬት አይቅር ወድቆ
የመከራን ዳገት ትንፏቅቃ የወጣች
በደከመው ክንዷ ሰንደቅ ያነገበች
የእመ-እምላክን ሐገር ከአውሬ የታደገች
እቻትና ጦብያ ምስኪኗ ሐገሬ  ትውልዱን ያኮራች
እቻት እማምዬ ባለ ማሕትቧ ባለ አልባሶ-ክዳን ባለ ንቅሳቷ
እንደ አራስ ነብር አትንኩኝ የሚለው የሚቆጣው ፉቷ
ልጆቿን ሲነኩባት ክብሯን ሲያቀሉባት እይበርድም ንዴቷ
ሰንደቋን ከፍ አድርጋ ተራራው ላይ ቆማ ሐገሬን እያለች ይታያል ምሬቷ
Maraki – Sweden
ተጨማሪ ያንብቡ:  ዐምሐራ ይግደለኝ!!! - ያሬድ መኩሪያ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share