ጠላትን ወዳጅ ለማድረግ መለማመጥ መጋጋጥን ብሎም መጥፋትን ያስከትላል (ሀዱሽ መለስ)

map of amhara
Ethiopia

የአገራችን ኢትዮጵያ ታሪካዊ የውጭ ጠላቶች በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ቀዳሚና ቁጥር አንድ የአገር ጠላት በሆነው ወያኔ ጋር እየተመሳጠሩ አገራችንን ለማጥፋት እየተረባረቡ ይገኛሉ፡፡ ወያኔ ከኢትዮጵያ ህዝብ ለ27 አመታት ዘርፎ በውጭ አገራት ባከማቸው ቢሊዮኖች ዶላሮች ክፍያ እየተገዙ የእምዬ ኢትዮጵያ ጠላትነታቸውን ቀይ መስመር በማለፍ ጭምር አሰላለፋቸውን ብቻ ሳይሆን በአድርጎታቸው ጸረ ኢትዮጵያነታቸውን በተግባር እያሳዩን ነው፡፡ ተከፋዮቹ የምእራባዊያን ዋና ዋና የዜና አውታሮች፣ ጋዜጠኞች ፣የአለም አቀፍ ልዩ ልዩ ድርጅቶች ሀላፊወች ….. ወዘተ በኢትዮጵያ ላይ ያላሴሩት ሴራ ፣ያልጎነጎኑት ተንኮል ፣አገሪቱን ለማጥፋት ያልክፈነቀሉት ድንጋይ የለም፡፡ ኢትዮጵያ ሰላሟን አጥታ፣ በውስጥ ጦርነት ዳሽቃ፣ ለውጭ ወራሪወች ደካማ ሆና፣ ህዝቧም እርስ  በእርስ ጦርነት እንዲጠፋፋ ብሎም አገሪቱ እንደ ሶሪያ፣ የመንና ሊቢያ የወደቀች አገር (failed state)  እንድትሆን አበክረው እየሰሩ ነው፡: እስካሁን በጸረ ኢትዮጵያ አሰላለፍ ውስጥ ከታዩት የውጭ ሀይሎች ቀጥታ ጥልቃ ገብነቶች ውስጥ ይበልጥ የከፋው ሀምሌ 6 ቀን 2021 በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኩል የወጣው መግለጫ ነው፡፤ መግለጫው በእንግሊዝኛ መሆኑና ከአሜሪካ መሰማቱ እንጅ በወይን ጋዜጣ ላይ ከመቀሌ የወጣ የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ መግለጫ ነው ቢባል ቅንጣት ማጋነን አይሆንም፡፡

የመግለጫውም ገራሚ ክፍል እንዲህ ይነበባል፡፡ complete withdrawal of ….. Amhara forces from Tigray ….. and an affirmation that neither the internal nor external borders of Ethiopia will be changed by force or in contravention of the constitution …

ይህ መግለጫ ሱዳን ኢትዮጵያን ስለመውረሯ ምንም ነገር አይልም፡፡የመግለጫው እንቆቅልሽ ሲመነዘር ብዙ ገጽታ አለው፡፡ይህንን መግለጫ በወይራነቱ ካየነው መግለጫው  የሚለው ወልቃይት ፣ ራያ፣ ጠገዴና ጠለምት የወያኔ ናቸው ነው፡፤ የዙሪያ መሄድ አያስፈልግም፡፤ አሜሪካ ለዚህ እውን መሆን ጠባቂውም አስፈጻሚውም እኔ ነኝ እያለችን ነው፡፡ አለቀ፡፡ ከዚያ ውጭ ያለው እንቶ ፈንቶ ነው፡፤ በሌላ መልኩ ይህ ምን ማለት ነው?? ይህ ማለት ወያኔ ወልቃይትን ወስዶ ወደሱዳን መውጫ መግቢያ በርን ይቆጣጠራል ማለት ነው፡፤ ይህ ማለት ወያኔ የራያና የሁመራ ለም የአማራ መሬቶችን ይወስዳል ማለት ነው፡፡ ከዚያስ?? ከዚያማ በነአብይ አህመድ ላይ በአሜሪካ የተጣለው ማእቀብ ይነሳል ማለት ነው፡፡ ከዚያ በኋላም የአብይ አህመድ ሚስትና ልጆቹ ወደ አሜሪካ ወደነበሩበት ደንቨር ኮሎራዶ መመለስ ይችላሉ ማለት ነው፡፤ ከዚያ በኋላስ?? ከዚያማ በኋላ የፈረደበት የወልቃይት ፣ ራያ ፣ጠለምትና ጠገዴ የአማራ ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለዘለአለም ከርስቱ ተነቅሎ ይባረራል ማለት ነው፡፤ ወያኔ ወልቃይትን ይዞ ወደሱዳን መውጫ መግቢያ በርን ተቆጣጠረ ማለት በኢትዮጵያ ጉረሮ ላይ ማረጃ ካራ አረፈባት ማለት ነው፡፡ በአሁኑ ፖለቲካና የሀይል አሰላለፍ  ይህንን በሰፊው ካየነው ወደ ሱዳን መውጪያ መግቢያ በር የሆነው ወልቃይት በወያኔ ቁጥጥር ስር ሆነ ማለት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች  የዘመናት ያልተሳካ ሙከራቸውን በድል አጠናቀቁ ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት  ከአጼ ቴወድሮስ ጀምሮና አጼ ዮሀንስን ይዞ በየዘመናቱ ህይወታቸውን ለኢትዮጵያ አንዲነት የገበሩ ታላላቅ የአገሪቱ የጦር መሪወች ፣ጀግኖች አርበኞችና የህዝቡ የአርበኝነት ታሪክ በአሁኑ  ዘመንና በተናጠልም በአብይ አህመድ አመራር በሚያሳፍርና በሚያሳቅቅ ሁኔታ አፈር ዲሜ በላ ማለት ነው፡፤ አገሪቱም እንደተፈራው ፈረሰች ማለት ነው፡፡ሁሉን አቀፍ የርስበርስ ጦርነት እውን ሆነ ማለት ነው፡፤

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከላይ ሆነን ስናይ - ገለታው ዘለቀ

አብይ አህመድ ይህንን በመርዝ የተቀመመ መደለያ ተቃውሞ አሜሪካ በዚህ አይናውጣነት ደረጃ በአገራችን ጉዳይ ፈላጭ ቆራጭ መሆን እንደማትችል በግልጽና በይፋ በአስቸኳይ ወጥቶ ካልተቃወመ የሚነፍሰው ንፋስ ልክ ነው ማለት ነው፡፡አብይ ይህንን ካላደረገ ያልተገነዘበው ጉዳይ አለ ማለት ነው፡፤ ይህም  በዚህ ስራው ራሱ ከባድ የአገር ክህደት የፈጸመ መሆኑንና እልፍ ሲልም ይህ የክህደት ስራ በድምር ውጤቱ መጨረሻ ላይ ራሱንም ቤተሰቡንም ሊያድን አለመቻሉን ነው፡፡ እዚህ ላይ ጀግናው በላይ ዘለቀ ልጁና ሚስቱ በወራሪው የጣሊያን ጦር ተማርከው ለእነርሱ ሲል እጁን እንዲሰጥ ሲጠየቅ የሰጠውን መልስ ያስታውሷል!!

አብይ ለፓርላማው እንዳስረዳው ”መደብ ላይ ተኛ ብባል የለመድኩትና ያደግኩበት ስለሆነ አይገደኝም” እንዳለው ሁሉ የኢትዮጵያ ህዝብም የቀረው ይቅር እንጅ ነጻነቱ ይበልጥበታልና ባርነትንና ለጠላት ማጎብደድን ፈጽሞ አይቀበልም፡፡ በአገር ደረጃም ሆነ በእስካሁኑ መሪወቿ ደረጃ ኢትዮጵያ የዚህ አይነት ታሪክ የላትም፡፡ ስለዚህ አብይ አህመድ ሆይ፦ የአገሪቱ የወቅቱ መሪ ስለሆንክ በቃል የምትለውን በተግባር ሁነህ ተገኝ!!! ሁሉም እንደ ጎርፍ ያልፋል፡፤ አገርና ህዝብ ግን ለዘለአለም ይኖራሉ፡፡አገራችን ባለው የወቅቱ የአገራት ፖለቲካዊ አሰላለፍ  የወሳኝና ጠንካራ የውጭ አገራትን ድጋፍ በአስተማማኝ አላት፡፡ በአለም አቀፍ ግንኙነት የሁለት ሀያላን ጎራወች መኖር ሚዛኑና አዋችነቱ  ቢለያይም ለደካማ አገሮች ጥቅሙ ወሳኝነት አለው፡፡ አብይ ሆይ፦ በአገር ውስጥም ሙሉ በሙሉ ሰፊ የህዝብ ድጋፍ አለህ፡፤ ስለዚህ መልመጥመጡ ለምንድን ነው?? ለተልካሻ ነገር ያለአግባብ ይህንን ያህል ወርዶ ሸብረክ ማለት አያድንህም፡ አያዋጣህም፡፤ አገሪቱንም ይገድላታል፡፡ የሚያዋጣህ ፣የሚያድንህ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም በእስካሁኑ ዝምታህና በሚጠረጠረው  አድራጎትህ ከገፋህበት አገር ጎድተህ ትእዛዛቸውን ለጊዜው ብትፈጽምም ጠላቶችህ አንተን ካላጠፉ አያርፉምና በመሀል ሊደልሉህ በሚሞክሩ የውስጥም የውጭም ሀይሎች አትሞኝ፡፡ በእውንም ከኦሮሙማ የጸዳህ ከሆንክና በሙሉ ኢትዮጵያዊነት በእምነትና በስሌት የምትጓዝ ከሆነ በውስጥ ለእነማን ጋሬጣ እነደሆንክ ራስህም ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብም ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፤ ምክንያቱንም የነዚህ ጋሬጣወች የውጭ  ገፊ ሀይል ከጀርባ ማን እንደሆነ ለእኛ ኢትዮጵያዊያን ቁልጭ ብሎ ይታያልና፡፡ከውጭ በኩል ያሉትም የማይቀመሱ የሚመስሉ ገፊና ደላላ ሀይሎች/አገሮች ለጊዜው መተንፈስ ያስችሉህ ይሆናል እንጅ እነርሱ በአለም ውስጥ በገቡባቸው አገራት ሁሉ ታሪካቸው የሚያሳየው ታክቲካል አጋር ያደረጉትንም ሀይል (ግለሰብ) ከማጥፋት አይመለሱምና፡፤ በተለያዩ አገሮች ውስጥ በፈጸሟቸው የፖለቲካ ቁማሮች የጠላትነት ልምዳቸው፡ ታሪካቸው የሚያሳየው ይህንኑ እውነታ ነው፡፡ስለዚህ በአጭሩ በአገራችን ላይ የመጡ ጠላቶችን ለመቃውም፤ እምቢ ለማለት፣ ለመመከትና ለማስወገድ ፍጹም አታወላውል፡፤ ህዝቡ ከአንተ ጋር ነውና፡፤  ይህንኑ በሚመለከት አንድ ወርቃማ የአገራችንን አባባል አለ፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  “እንፈላለጋለን!” (ፀጋዝአብ ለምለም ተስፋይ)

እልም ነው ጭልጥ ነው ዉሀ አይላመጥም

ጠላት ወዳጅ ላይሆን አልለማመጥም

 

4 Comments

  1. በሀሰት በግፋ ና የአሳደህ በለው ፕሮፓጋንዳ ተጠምዳቹሀል፥ንፁሓንን ለፖለቲካ ትርፍ እያስፈጃቹህ ነው፥፥፥ቀድሞውንም የናንተ ያልነበረ መሬት፥ ርስት አስመላሽ ብላቹ ኮሚቴ አቋቁማቹ እንደነበር ሁሉም ይመሰክራል ፥አመቺ አጋጣሚ እስክታገኙ ትጠባበቁ እንደነበር የማንዘነጋው ነው ፥፥ከጦርነቱ በፊት ሰርጋቹ ገብታቹ የትግራይ ተወላጆችን እንደገደላቹ በቅርብ የታሪክ መዝገብ ተሰንዷል፥፥እየሄዳችሁበት ያለ አካሄድ አደገኛ እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው አርሶአደሮችን በከንቱ አላስፈላጊ በሆነ ጦርነት ውሥጥ ክቡር ሕይወታቸውን በከንቱ ከመሠዋት በቀር በስተመጨረሻ የድል ተቋዳሾች እንደማትሆኑ እስካሁን ያየናቸው በጦር ሜዳ የተፈፀሙ ነባራዊ ሁኔታዎች ያረጋግጣሉ፥፥ባዕዳን ወራሪ ሀገሮችንና ዘመናዊ መሣሪያዎችን አሰልፋቹ ያልተሳካላቹ ቁመህ ጠብቀኝን ያነገቱ አርሷደሮች አሰልፋቹ ምን ያህል ርቀት ልትጓዙ እንደምትችሉ የታያቹ አልመሰለኝም፤፤ዋና መልዕክቴ ሕዝባቹህን አታስጨርሱ፥ወገናቹህን የሀሰት መረጃ እየሰጣቹ ወደ ጦር ሜዳ ሂዶ የናንተ ደጀን እንዲሆን በማሰብ አትማግዱት፥፥ምክር ነው ማስፋራርያ አይደለም፥፥ፉከራና ቀረርቶ አያድንም፥የዋሁ ገበሬ ከማን ጋር እንደሚዋጋ እንኳን በቅጡ የሚያውቅ አይመስለኝም፥፥እባካቹህን ለጥፋት አላማቹህ መጠን ለከት አብጁለት በኋላ ላይ በከንቱ የወገኖቻቹህን ሬሳ ታቅፋቹ ከማልቀስ ፥፥ይህን መልዕክት ሳስተላልፍ ወገኖቼ በረሀብና በጥይት በእናንተ ወገኖች እያለቁ መሆናቹህን ግን ላሰምርላቹ እፈልጋለሁ፥፥ይህ ሆኖ ሳለ ግን የናንተ ወገኖች በከንቱ በሀሰት ትርክት ተሞልተው ሲያልቁ አዝናለሁ፥፥ሕዝባችንን በረሀብ አትፍጁብን ከመሬታችን ለቃቹ ውጡልን፥የእርዳታ ሰጪ ተሽከርካሪዎችን አታግዱብን፥፥በተለያዩ ከተሞችና ገጠሮች ያሉ ተጋሩ ወገኖቻችንን አትግደሉ አታሰቃዩብን፥፥ምናልበትም የወገናቹ ሞት የሚገዳቹ ከሆነ በርግጠኝነት በኋላ ታዝኑበታላቹ፥፥ወንድወሰን ተክሉ በትግራይ የደረሰባቹህን ነግሯቹሀል፥፥ይህ የጎጠኝነት ና የዘረኝነት ጉዳይ አይደለም ፥ሌላውን እስካላገለለ ድረስ ሁሉም ወገኑን ይደግፋል፥ተፈጥሯዊና ተገቢ ነው፥፥ከዕዳን ሀገራት ጋር ሆናቹ በትግራይ ሕዝብ ላይ የፈፀማቹሁት ግፍ የበለጠ ጥንካሬ ሰጥቶን የገዛ መሬታችንን ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማንል ልታውቁ ይገባል፥፥የወገናቹ ዕልቂት አስቁሙ ፥በከንቱ እንዲያልቁ አታታሏቸው፥፥ሌላውን ሕዝብ ኦሮሞንና መላው የኢትዮጵያ ሠራዊት እየቀሰቀሳቹ እንደሆነ፥ገንዘብ አዋጡ እያላቹ እያስገደዳቹ እንደሆነ ደርስንበታል፥፥ለሚደርሰው ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂ ናቹ፥፥ትግራዋይ ከርስቱ ነው ያለው፥፥ሃያሰባት አመት ይሄ ተፈፀመ ሕውሓት ይህን አደረገ የት ነበራቹ የሚሉ አመክንዮ ምክንያታዊ ሰብዕና አሁን አያዛልቃቹሁም፥፥ፍትህ ለንፁሓን ከትግራይ ውጡልን

    • ከላይ ለፃፍከው አስተያየት ያለኝ መልስ አለቆችህ ጌታቸው ረዳና ፃድቃን ወልደትንሳይ በአማራ ህዝብ ላይ ሂሳብ የማወራረጃ የጦርነት አዋጅ ሲያውጁ አለሰማህም:: እራሱን ለማዳን አማራ ሆኖ የተፈጠረ ሁሉ መደራጀትና መታጠቅ ይኖርበታል:: ማይካድራ በምንም መልኩ አይደገምም:: ሌላው ያለው ሀቅ ህውሀት ሲፈጠር ኢትዮጵያን በመበታተን ፕሮግራም አውጥቶ 17 አመታት በሽምቅ ውጊያ ተዋጋ:: በነበረው ብልሹ የደርግ ስርአት የደከመች ኢትዮጵያን ተቆጣጠረ:: በ27 አመታት አገዛዙ ኢትዮጵያዊነትን ሳይላበስ በትግራይ የበላይ ገዢነት ሀገሪትዋን ዘርፎ ህዝቧን በጎሳ ሸንሽኖ አዳክሞ ሄደ:: አሁን ሁለተኛ ዙር ጦርነት በህዳር ወር ጀምሯል:: በዬትም ሀገር አንድ ፅንፈኛ የባንዳ ቡድን የሀገር መከላከያ ስራዊትን ጨፍጭፎ ሴቶችን ጡት ቆርጦ ምርኮኞች ላይ ሲኖ ትራክ ነድቶ ይህን አረመኔያዊ ጥቃት የማይከላከል የፌዴራል መንግስት በአለም አይኖርም:: የመላው ትግሬ ጥያቄና ቁጭት ትናንትም ሆነ ዛሬ ማንም ሊያስረዳኝ አይችልም:: በታሪክ በንጉሱም ጊዜ ትግራይ የምትስተዳደረው በራሷ ልዑል ራስ መንገሻ ነው:: ከዚያም በሗላ በትግራይ ከትግሬ ውጪ አስተዳዳሪ ተሹሞ አያውቅም:: የምናውቀው ኦሮሞ ጉራጌና አማራ ትግራይ ሰፍሮ ህዝብን የበደለ ባለሀብት ወይንም አስተዳዳሪ ሰምተን አናውቅም:: ትግሬዎች በምን ተበደሉ? ዬትኛው የኤኮኖሚ ምንጫቸው በኢትዮጵያ ተዘረፈ:: በእውነት እንነጋገር ከተባለ ትግራይ ህዝብ ያለኢትዮጵያ በልቶ ለመኖርስ ይችላል? በ 2018 በታክስ ከትግራይ የተሰበሰበው 5 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው:: ከመላው ኢትዮጵያ 198 ቢሊዮን ተሰብስቧል:: የፌዴራል መንግስት 13 ቢሊዮን በአመት ይደጉማል:: እነዚህ ሰዎች ለምን የበሉበትን ወጪት ይሰብራሉ?
      የ1991 ና የ2021 የተለያዩ ኢትዮጵያ ናቸው:: ዐቢይ መንግስቱ አይደለም:: ሰኔ 14 ታሪክ ተለውጧል:: እኔ እንደ አማራጭ የሚታየኝ ሰላምና ልማት የሚፈልጉ ትግሬዎች በጦርነቱ ያልተሳተፉ ወንጀል ያልሰሩ በወንጀል የማይፈለጉ ስብሰባ አድርገው የፌዴራል መንግስት ጋር ድልድይ ያብጁ:: ዐቢይን እንገለብጣለን የሚለው ቅዠት እየቆየ ይረዱታል:: በጀት ልቀቅልን እኛ መጥተን እንወጋሀለን:: ለብዙዎች አስቂኝ ድራማ ይመስላል ሆኖም ችግር የሚያስታቅፉት የትግራይን ህዝብ ነው:: በምንም መልኩ ኢትዮጵያ አትፈርስም:: በእውነት እልሀለሁ የአማራን ህዝብን አታውቁትም:: ለኢትዮጵያዊነት ሟች ነው:: ማንም ባንዳ እየተነሳ ልግደልህ መጣሁ ሲል ዝም ብሎ ይጠብቀኛል ብለህ አታስብ:: ታሪክን አገላብጥ አማራ ማሞኘት ይቻላል ግን ማሸነፍ አይቻልም:: ይህ አብረን እንጠፋለን የሚለው የጦርነት ስልት አይሰራም በዚህ አትጃጃሉ::

    • ወስላታ – የማን ወገን ቆሞ የማን አለቀ? ከሁሉ ወገን አይደል እልቂቱ። ደግሞስ በ 27 ዓመቱ የወያኔ አገዛዝ ስንቶች አፈር እንደተመለሰባቸው ጠፍቶህ ነው እንዲህ የምትቀባጥረው። አብሮ መኖርን የማያውቅ ወያኔ ነው። ወያኔ በራሱ አስቦ ለራሱ በልቶ ነጻ አወጣሁህ የሚለውን የትግራይ ህዝብ ለመከራ የዳረገ ተልካሻ ድርጅት ነው። ልክ ነው መገዳዳል ኋላ ቀርነት ነው። ጉራም ለማንም አያዋጣም። ሂሳብ እናወራርዳለን የምትሉ እናንተ፤ ለዓለም ህዝብ የአዞ እንባ የምታነቡ እናንተ። የትኛውን ሃገር ነው ለቃችሁ ውጡልን የምትለው? በጉልበት ስምና ባህሉን ቀይሮ ወያኔ በአረመኔነት እጅ የቆረጠበትን ወልቃይትና ጠገዴ፤ የራያና አካባቢውን መሬት ነው? ሲያምርህ ይቅር እንጂ ጭራሽ የማይሆን ነገር ነው። የአሜሪካ በጎናችሁ ሆኖ ቱልቱላ መንፋት ችግሩን ለማባባስ እንጂ እጃቸው የገባበት ነገር ሁሉ ከመፈራረስ አይተርፍም። የእነርሱ ማርሻል ፕላን የሚሰራው ለነጭ ህዝብ ብቻ ነው። ጥቁሩ ህዝብ መሳለቂያቸው ነው። ይህ ካልገባህ የደንቆሮ ደንቆሮ ነህ።
      ግን ያው የተጋትከው የወያኔን የፈጠራ ታሪክ በመሆኑ ለራስህ በራስህ አስበህ የመኖር እይታህን ተቀምተሃል። ያ ባይሆን ኖሮ ሁሉም በዘሩ እንዲቆም ጥሪ አታደርግም ነበር። የሰው ልጅ መለኪያው ሰውነቱ ብቻ ነው። ሌላው ሁሉ ያተላ ክምር ነው። ከሚያለያዪን ነገሮች ይልቅ አንድ የሚያረጉን ነገሮች ይበዛሉ። በሃበሻ ምድር ማንም ሰው የዚህ ዘር፤ የዚያ ወገን ተወላጅ ነኝ ማለቱ ሁሉ ሳይንሳዊነት የሌለው የአፈሙዝ ፓለቲካ ነው። በትግራይ ወይም በአማራ ወይም በኦሮሞ አካባቢ መወለድ የዚያ አካባቢ ተወላጅ ያደርግሃል እንጂ ዘርህን አስረግጦ አይናገርም። ስንገዳደል፤ ስንዘራረፍ፤ አንድ አንድ አግብቶ ሲፈታ፤ መልሰን ስንጋባ፤ ኸረ ስንቱ ይነገራል በትርምስ ውስጥ በኖርች ሃገር ዘር መቋጠሩ የአሽዋን ክምር እንደመቁጠር ነው። የትግራይና የአማራ ወገኖች በሰላም በአንድነት ያለውን ተካፍለው ቢኖሩ የተሻለ አማራጭ ነው። ይህ ግን ሂሳብ አወራርዳለሁ የሚል ደንቆሮ ባለበት ምድር ያው ተመልሶ የድሃ አደግ ልጆችንና ገበሬዎችን ማስጨረስ እንጂ ሌላ ትርፍ አይገኝም። አንተም የዚህ ውስልትና አንድ አካል እንጂ የመፍትሄው አካል ለመሆን አልቻልክም። ሌባ ሲሰርቅ አይጣልም ሲካፈል እንጂ። ወያኔ ሌባና ደም አፍሳሽ ድርጅት ነው። የ 45 ዓመት ታሪኩ ይህን አስረግጦ ያስረዳል።

      • ተስፋችን ልዑል እግዚአብሄር ይጠብቅህ የብዙ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ድምፅ ነው ያስተላለፍከው::አነዚህ ስግብግቦች የትግራይን ህዝብ ከኢትዮጵያ ከማራቅ ውጪ ከአሁን በሗላ አዲስ አበባን አይረግጡም::

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share