November 3, 2020
1 min read

የሞትንስ እኛ ነን! – ፊልጶስ

የሞቱትስ ሄዱ፣ ወደ እማይቀረው፣
የሞትንስ እኛ ነን፣ ቁመን ያየነው።
የሞትንስ እኛ ነን፣ እኛ ቀሪዎቹ
ይጣራል ድምፃቼው፣ የእናት የልጆቹ።
“ኤሉሄ! ኤሉሄ! ላም ሰበቅተኒ፣ ያ ሲቃ ዋይታቼው፣
ቀርቷል ከእኛ ጋራ፣ ውሻ የላሰውም ይጣራል ደማቼው።
ኧረ ይብልኝ ለእኔ፣ ኧረ ይብላኝ ለአንተ፣ ኧረ ይብላኝ ለአንች
ለሁሌ ምሾ አውራጅ፣ ለሁሌ አዲስ ሞቱ፣ ለጥቁር ለባሾች።
ሰምተን – እንዳልሰማን
አይተን -እንዳላየን
አውቀን – እንዳላወቅን
ጠርተውን ” ወይ” ሳንል፣ ሲማፀኑን ቀርተን።
ደማቼው እረክሶ፣ ከአባይ ውሃ ጅረት ፣ ከሚሞላው ደለል
ገላቼውም ሳስቶ፣ ንፋስ ከሚወስደው፣ ከላባ-ከቅጠል፤
እኛ ነን የሞትነው፣ የበሰበስነው
የቁም ሞትን ሞተን፣ አለን የምንለው።
ነገስ ምን ይዘናል?
ምንስ አስበናል?
የትላንት መታረድ
የዛሬ መረሸን
ምን አስተምሮናል?

——// ——
ፊልጶስ
e-mail: philiposmw@gmail.com

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ዋይ ለልስ – አማራ (ጲላጦስ – ከባህር ዳር)

Next Story

የህወሃት አመራር ሀገር የማተራመስ ተግባር ላይ መንግስት ጠንካራ እርምጃ ሊወስድ ይገባል! – አበጋዝ ወንድሙ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop