ወይ አገሬ ሆይ ዝንታለም መከራ ሁልጊዜ ዋይ ዋይ (ዘ-ጌርሣም)

ወይ አገሬ
(ዘ-ጌርሣም)
ወይ አገሬ ሆይ
ወይ ወገኔ ሆይ
ዝንታለም መከራ ሁልጊዜ ዋይ ዋይ
ሰላም ከዓይን ዕርቃ መኖር ይህ ነወይ
ትናንተ መደመር
ዛሬ መደናበር
ይቅርታው ተረስቶ
ኽውከት ተተክቶ
ሁሌም የናፈቅነው የሰላም አየር
አገኘነው ስንል ይርቀን ጀመር
ትናንት በአንድ ሁነን
ግፍን ተቋቁመን
ህይወትን በመክፈል
ለአንድነት ስንምል
ከጥላቻ ፍቅር
ለትውልድ እንዲቀር
ብለን ተማምለን
ያለፈውን ትተን
ወደፊት በማየት
ደግ ደጉን በማውሳት
ግንቡን አፈራርሰን
በድልድይ ተክተን
አልነበረም ወይ በቃል የተገባው
ድንገት ምን መጣና ምላስ የታጠፈው
ወይ አገሬ ወይ
ወይ ወገኔ ሆይ
ዝንታለም መከራ ሁልጊዜ ዋይ ዋይ
እስኪ ምን ጎደለ
ምኑ ጎረበጠ ያልተደላደለ
የትናንቱ ደስታ
እንዴት ተቀየረ በዛሬው ዕሪታ
ተጋብተው ተዋልደው
ልጆችን አፍርተው
መከራና ደስታን በጋራ ተካፍለው
በጋራ ዕድር ታቅፈው
አብረው እንዳልኖሩ
ምን ሰይጣን ገብቶ ነው
ህዝብ የሚያጫርሰው
ያውም በአሁኑ ውቅት
መቅሰፍት በበዛበት
እንዲህ መጨካከን
ለጥቅም ተገዝተን
ትናንት የበሉን
እኛኑ ሲያባሉን
በቃ የማንለው
ምን ቢጉልብን ነው
ወይ አገሬ ሆይ
ወይ ወገኔ ሆይ
ዝንታለም መከራ ሁልጊዜ ዋይ ዋይ
ሰላም ከዓይን ዕርቃ መኖር ይህ ነወይ

ተጨማሪ ያንብቡ:  አሳማ! - በላይነህ አባተ

1 Comment

  1. —–ትራምፕ አርቆ አስቦ
    -አለ ግብጽ ታጣለች ዳቦ

    —-አማራን ማን ያስብለት
    -እፉን ድፍን አድርገው ለጉመው አስረውት

    —–ኖቬምበር አንድ ቀን አሸሹ ጥበቃን ያለማስጠንቀቅያ
    –በኮሮና ዘመኅ የአለም ዕለተ bill ክፍያ

    —–ኧረ በትኩሱ አሰሙ ለመላው የአለም ጋዜጠኞች
    –ትራምፕ ባይደን ማለት ብቻን ትተው ትንሽ እንኳን ቢያነሱ ስለ ጉራሶ ሟቾች

    —- ኧረ ካልሆነ የንጉሡ ያለህ ይባል
    –ወያኔ የቀዘነው ጠቅላይ አብይ እያስጨርሰን በጥበቃ ማሸሽ ተንኮል

    ——- ያለፈው አላለፈም ብሎናል ፓርላማ ላይ አብይ በድፍረት
    – በቁም መሞታችንን ሲያረዳን ሲያስቀጥል የአማራን ሞት

    ——–ማን ነች እርሷ ስምዋ
    –ብትነግረን ስንት የአማራ ደም ቀይ መስመሮች እንደታለፉ በዘመንዋ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share