አምስት የኦነግ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች አባላቱ በአዲስ አበባ በቁጥጥር ስር ዋሉ

አምስት የኦነግ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች አባላቱ ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የድርጅቱ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ገለፁ።

የኦነግ ሥራ አስፈጻሚ አባላትን ጨምሮ ዘጠኝ ግለሰቦች በዛሬው ዕለት (ቅዳሜ) በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የድርጅቱ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ተናገሩ።

አቶ ቶሌራ አደባ፣ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ዛሬ ማለዳ አመራሮቹ በጋራ ይኖሩበት የነበረው ቤት በፖሊስ የተበረበረ ሲሆን፣ አካባቢውም በፖሊስ ተከብቦ ቆይቷል።

ከዚያም በተለምዶ ሶስተኛ ወደሚባለው ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸውን ይገልጻሉ።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሥራ አስፈፃሚ አባላቱ መካከል አቶ አብዲ ረጋሳ እና አቶ ሚካዔል ቦረን የሚገኙ ሲሆን የድርጅቱ የማህበረሰብ ጉባዔ አባል አቶ ኬነሳ አያና፣ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ያዴ አብዱልሽኩር፣ የዲፕሎማሲ አማካሪ ዶ/ር ሽጉጥ ገለታ እንዲሁም ሁለት ሹፌሮችና ሁለት ጠባቂዎችም ጨምሮ መታሰራቸውን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

አቶ ቶሌራ አክለውም “ዛሬ ማለዳ የአመራሮቹ ቤት መበርበር ከጀመረበት ሰዓት አንስቶ ልናገኛቸው ስላልቻልን የታሰሩበትን ምክንያት አላወቅንም”

አቶ ቶሌራ እንደሚሉት ዛሬ ማለዳ በአባላቶቹና በአመራሮቹ መኖሪያ የተደረገው ብርበራ ያለ ፍርድ ቤት ማዘዥ የተካሄደ ነው።

እነዚህ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኦነግ አመራሮች በጋራ ይኖሩ የነበረው አዲስ አበባ ካራ ቆሬ በሚባል አካባቢ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ቶሌራ፣ እስካሁን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው አካል ማን እንደሆነ እንዳላወቁ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ይህንን ጉዳይ ለማጣራት ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ደጋግመን ብንደውልም ምላሽ ማግኘት አልቻልንም።

ከአንድ ሳምንት በፊት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ባወጣው መግለጫ 350 የሚሆኑ አባላቶቹ በአዲስ አበባና፣ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ታፍሰው እንደታሰሩበት አስታውቆ ነበር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሸንጎ በሲያትል ዋሽንግተን የተሳካ ህዝባዊ ስብሰባ አካሄደ

BBC

1 Comment

  1. They do the same to many people here and there these citizens of superpowers . Thier identity priveleged them from facing the consquences of thier crimes .

    Afterall, the justice system is out there for the good of some members of our or thier society by demonizing the multitude impoverished group.Poor are supposed to fill jails while the rich are making profit out of this deal. We see people got arrested and freed for no junky reasons like the innocent people freed by Colonel Abiy, killer.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share