June 4, 2013
3 mins read

ሁመራን የብሄር ግጭትና የኤርትራ ታጣቂዎች አመሷት

(ሁመራ ከተማ)
ሁመራን የብሄር ግጭትና የኤርትራ ታጣቂዎች አመሷት 1

(ፍኖተ ነፃነት) በምዕራብ ሁመራ ማይካራ መቻች በተከሰተ የብሔር ግጭት የሰዎች ህይወት ጠፋ፤ መንግስት ግጭቱን ለማስቆም የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ በአካባቢው ተከታታይ ግጭቶች ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን የአካባቢው ምንጮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
ሱዳን ጠረፍ ላይ ቅዳሜ ግንቦት24 ቀን 2005 ዓ.ም በብሄር ምክንያት የተቀሰቀሰው ይኸው ግጭት በሁለት ቀናት ውስጥ የ12 ሰዎችን ህይወት መቅጠፉንፉን የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ጨምረው ገለፀዋል፡፡ በኢትዮጵያና ሱዳን ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው መቻች በረሃ በቀን ራያ የተሰማሩ ሰዎች በብሄር እየተቧደኑ መገዳደል ከጀመሩ ሶስት አመታት ማስቆጠራቸውን ያስታወሱት ምንጮቻችን መንግስት ችግሩን መፍታት ምንም አይነት ሚና ለመጫወት አለመፍቀዱ የሟቾቹንና የተጎጂዎቹን ቁጥር እንዲያሻቅብ አድርጓል፡፡
ሰራተኞቹ በወሎ፣በጎጃም፣በጎንደርና በራያ ተወላጅነት ተቧድነው በካራ፣በዱላና በእሳት በፈጠሩት ግጭት የሰው ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው አካባቢውን ጠሚያውቁ አስተያየት ሰጪዎች “መንግስት በኢትዮጵያ የብሄር ጥያቄ ተመልሷል በማለት የብሄር ብሄረሰቦችን በዓል በሚያከብርበት ወቅት በጎሳ ፖለቲካ እንዲህ አይነት ዘግኛኝ ድርጊቶች እየተፈጠሩ የሰው ህይወት መብላታቸው ጥያቄዎቹ በተገቢው መንገድ ላለመመለሳቸው ማሳያ ይሆናል” ብለዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በዚሁ በሁመራ በረከት ወረዳ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ለመዝረፍ የሚሞክሩ ሽምቅ ተዋጊዎች በተለያዩ ጊዜያት ድንገተኛ ወረራ በማድረግ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያስጨንቁ እንደነበር የጠቀሱት ምንጮቻችን በቅርቡ ታጣቂዎቹ አካባቢውን ከሚጠብቁ ሚልሺያዎች ጋር ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በሁለቱም ወገን ህይወት መጥፋቱን አጋልጠዋል፡፡ በተደጋሚ የማያባራ የተኩስ ልውውጥ መስማት በአካባቢው የተለመደ እንደሆነም የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በሁመራ ስለተከሰተው የግጭት ለማጣራት የአካባቢውን ባለስልጣናትና የፖሊስ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

Neymar Barcelona
Previous Story

Sport: ብራዚላዊው አጥቂ ኔማር ባርሴሎና ገባ

3948
Next Story

ለአርቲስት አበበ መለሰ ገቢ ማሰባሰቢያ 9 ዘፋኞች በአ.አ የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጁ፤ ኤፍሬም ታምሩ?

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop