December 19, 2023
2 mins read

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው “ዝማምነሽ ታወር” ሕንጻ ከወይዘሮ አፀደወይን በቀለ በሥጦታ ተበረከተለት

ታኅሣሥ 09/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ዩኒቨርስቲው የ60ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሲያከብር ሕዝቡ ተቋሙን ለመደገፍ ትብበር ሊያደርግ እንደሚገባ ያስተላለፈውን መልዕክት ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍሎች ድጋፋቸውን እያበረከቱለት ነው። ከደጋፊዎቹ መካከል ደግሞ ወይዘሮ አፀደወይን በቀለ እና ቤተሰቦቻቸውቀዳሚዎቹ ናቸው።411969850 748999773924616 8882494238832183547 nበባሕር ዳር ከተማ ተወልደው ያደጉት ወይዘሮ አፀደወይን በቀለ በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን እና ከእናታቸው ወይዘሮ ዝማምነሽ ወልደየሱስ በውርስ ያገኙትን ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመተውን ዙማምነሽ ታወር ለባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በስጦታ አበርክተዋል ፡፡411728922 748999930591267 8151955860955221168 n

ስጦታውን ለመስጠት ያነሳሳቸውም ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በጤናው ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት ለመደገፍ መኾኑን የወይዘሮ አፀደወይን ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡

411921383 748999790591281 3280424816043634075 n

ስጦታውን የተረከቡት የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ፍሬው ተገኝ (ዶ.ር) ዩኒቨርስቲው ትልቅ ኀላፊነት እንዳለበት በመገንዘብ ነው ብለዋል።

ማኅበረሰቡ ያለውን ሃብት ለሕዝብ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማት በማካፈል ተቋማት ሠፊ አገልግሎት እንዲሰጡ መደገፍ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

412291422 748999877257939 5302835896694733709 n

ከወይዘሮ አፀደወይን ቤተሰብ ትምህርት በመውሰድ ሁሉም ትብብሩን አጠንክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኝ ጠቅሰዋል።

412293933 748999800591280 7207302865882463409 n

የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የተሰጠውን የሕንጻ ስጦታ ለማኅበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጥ በማሰብ የእናቶች እና ሕጻናት የሕክምና ማዕከል እንደሚኾን ገልጸዋልዋል።

ዘጋቢ:- ራሄል ደምሰው

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

187720
Previous Story

ፋኖ ከባድ ማጥቃት ከፈተ | ባህርዳር ዙሪያ ዉጊያ ተከፈተ | አስደማሚ ጀብዱ ተሰራ

393727061 10230813036500235 143759728525390040 n 1 1
Next Story

ኦነግ፣ የሞተና የበሰበሰ ድርጅቱና፣ ጸያፍ፣ ናዚዛዊ ፣ አደገኛው አስተሳሰቡ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop