May 1, 2023
3 mins read

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር የሚከተለውን መልስ ሰጥቷል።

344546779 2034007546941136 4078334548667587036 n

ኦህዴድ መራሹ የዐቢይ አህመድ መንግሥት “የአማራ ሕዝብን እንደ ሕዝብ የምናደርስበትን መከራ ለምን ድምፅ ሆናችሁት” በሚል በርካቶችን እያሳደደ እና እያሰረ ይገኛል።
በዛሬው ዕለትም እኔን እና ወንድሞቼን “ሕገ – መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ” በሚል በሽብር ወንጀል እፈልጋቸዋለሁ እያለ ነው።
ወንድማችን ግርማ የሺጥላን የገደለው ኃይል ከያዛቸው ከወራት በላይ የሆናቸውን እንዲሁም ፍርድ ቤት የዋስ መብት የሰጣቸውን ግለሰቦች የዋስ መብታቸውን ነፈጎ በአዲስ ክስ ለመመሥረት አመቺ መንገድ መፍጠሩ ነው። የዐቢይ አህመድ ‘መንግሥት’ የጡት አባታቸውን ሕውሓትን ከምኒልክ ቤተ መንግሥት ከመባረር እንዳላዳናቸው ማወቅ ተሥኗቸዋል።
በወንድሜ ሻለቃ ምሬ ወዳጆ እና በፋኖ በለጠ ጋሻው የተቀነባበረው የድምፅ ልውውጥም በማን እንደተቀነባበረ እንኳን እንደ እኔ አይነቱ ጋዜጠኛ እና የሳይበር ደህንነት ስልጠና ለወሰደ ሰው ለተራ ግለሰብም ሀሰተኛ የድምፅ ቅንብር መሆኑ የሚሰወር አይደለም።
እኔ አንድ አማራ ነኝ፤ በአማራነቴ የመጣብኝን መከራ እቀበለዋለሁ። ነገር ግን ስንቱን ገድሎ እና አፈናቅሎ እንደሚጨርሰው አብረን የምናየው ይሆናል። እኔና ሌሎች ጓዶቼ የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ከፈጣሪ የተሰጠውን የመኖር መብት ቀምተን ከባሪያ ያነሰ አኗኗር እናኑራችሁ ለሚለን አካል እሺ እንደማንል ያደግንበት ሥሪትም ሆነ ሥነ – ልቦናዊ ውቅር እንደሌለ ልታውቁት ይገባል። ስለዚህ እንኳን የእስር ማደኛ አግኝታችሁ ብትሰቅሉኝም ከባሪያ ያነሰ ሕይወት ከምገፋ ለነጻነቴ እየታገልሁ ብሰቀል አይቆጨኝም።
የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ሁሉም ፋኖ መሆኑ እየታወቀ “ኢ – መደበኛ” ማቃለያ ሕዝብን እንደ ሕዝብ ፈርጆ ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ መሆኑ መላው የአማራ ሕዝብም ሆነ ሌላው ኢትዮጵያዊያን ብሎም ለሰብዓዊ መብት መከበር የቆሙ የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን በልዩ ትኩረት እንዲከታተሉት እና እየተፈፀመ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ እና የዘር ማጽዳት እንዲያስቆሙ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ።
በመጨረሻም፦
አማራ ግን የታወጀብትን የዘር ጭፍጨፋ እና የዘር ማጽዳት ግን ቀልብሶ እንደሚወጣ እርግጠኛ ነኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Abiy Gragn Mohamed 1 1
Previous Story

ግራኝ አህመድና አብይ አህመድ (እውነቱ ቢሆን)

182395
Next Story

ከባዱ ፈተና ከፊታችን ይጠብቀናል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop