March 18, 2023
4 mins read

አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ በህወሓት ተመረጡ

59ba71f0 c575 11ed 95f8 0154daa64c44 1 1የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አርብ መጋቢት 08/2015 ዓ.ም. ባካሄደው ምርጫ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳር ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ መምረጡ ተነገረ።

አቶ ጌታቸው ረዳ አዲስ የሚቋቋመው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳር ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ በህወሓት መመረጣቸውን የትግራይ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል።

በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል ከወራት በፊት በፕሪቶሪያ በተደረሰው ግጭትን በዘላቂነት ለማቆም በተደረሰው ስምምነት መሠረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመሰረት ተወስኗል።

ህወሃት የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር ካዋቀረ በኋላ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት በፌዴራል መንግሥት መጽደቅ አለበት።

በሚዋቀረው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የሚኖርን ውክልናን በተመለከተ 30 በመቶ ለህወሓት፣ 25 በመቶ ለትግራይ ሠራዊት፣ 15 በመቶ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ቀሪው ለምሁራንና ለሲቪክ ማህበራት እንደሚሰጥም ከዚህ ቀደም መገለጹ ይታወሳል።

ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ አንቶኒ ብሊንከን በሰላም ስምምነቱ ተደራዳሪ ከነበሩ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገራቸው የሚታወስ ነው።

የፌደራሉ መንግሥት ዋነኛ ተደራዳሪ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የህወሓት ተደራዳሪ እና ቃለ አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በተነጋገሩበትም ወቅት፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መመሥረት የስምምነቱ ቁልፍ ተግባር አድርገው ማየታቸው ተጠቅሷል።

በዚህ ውይይትም ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነቱ እንዴት እየሄደ እንደሆነ የተገመገመ ሲሆን፣ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እንደሚቀሩ መስማማታቸው ተገልጿል።

ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ጋር ስለነበራቸውም ቆይታ የተናገሩት አቶ ጌታቸው ረዳ “ለሰላም ያለንን የማያወላውል ቁርጠኝነት አረጋግጠናል። ሰላሙን ለማደፍረስ የተነሱ ኃይሎችን ጨምሮ በሕዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ያሉትን እንቅፋቶችን ለመፍታት ጊዜያዊ አስተዳደር መመሥረትን ጨምሮ የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን” በማለት በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል።

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት ምሥረታ ጋር ተያይዞ ምሥረታውን ለማካሄድ የተቋቋመው አስተባባሪ ኮሚቴ ከትግራይ ተቃዋሚዎች በኩል ተቃውሞ እንደተነሳበት መገለጹ ይታወሳል።

ሳልሳይ ወያነ፣ ባይቶና እና የትግራይ ነጻነት ፓርቲዎች በኮሚቴው ላይ የገለልተኝነት እና የአሳታፊነት ጥያቄ በማንሳት ከሂደቱ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታውቀዋል።

bbc

1 Comment

  1. ልክ ናቸው አማርኛ ተናጋሪና አማራ አንድ ብቻ ነው መምረጣቸው ትክክል ነው እሱን፡፡ ከዚያ አብይን ከአብረሃም በላይ ጋር ጆሮውን ብሎ እንደገና ወደ ላይኛው እርከን ይሸጋገራል ቆይቶ ማየት ነው፡፡ ኢሳይያስ ይህን ነገር እንዴት እያየው ነው? ነገ ወደሱ መሆኑን የሚዘነጋ አይመስልም፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

taye 1 1 1
Previous Story

ታዋቂው የታሪክ መምህርና አክቲቪስት ታዬ ቦጋለ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታፈኑ

abiy killer 1 1 1 1
Next Story

 መፀለይ አሁን ነው ! – አሸናፊ ዋቅቶላ፣ ሕ/ዶ -የውስጥ ሕክምና ባለሙያ 

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop