April 22, 2022
4 mins read

በአርባ ምንጭ የባልደራስ አመራሮች እገታን በተመለከተ የፓርቲው ድርጅታዊ መግለጫ

bALDERAS Hባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲን አገር አቀፍ የማድረግ ራዕይ ሰንቆ በትላንትናው ቀን ሚያዚያ 12/2014 ዓ.ም. አርባ ምንጭ ከተማ የገባው የባልደራስ የልዑካን ቡድን 1ኛ. አቶ እስክንድር ነጋ የፓርቲው ፕሬዘደንት፣ 2ኛ. አቶ ስንታየሁ ቸኮል የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ፣ 3. ጋዜጠኞቹ ጌጥዬ ያለው እና ወግደረስ ጤናው 4ኛ. የካሜራ ባለሙያ አቶ ሱራፌል አንዳርጌ ናቸው፡፡ የመጀመሪያው እቅድ፣ ባልደራስን አገራዊ ፓርቲ ለማድረግ የሚጀመረውን የፊርማ ማሰባሰብ ንቅናቄ በአርባምንጭ እና በወላይታ ሶዶ ከተማ ለማስጀመር የነበረ ሲሆን፣ በዚህ መሠረት ለሁለቱ ከተሞች አስተዳደሮች ጥያቄ ቀርቦ ከተፈቀደ በኋላ፣ “ከበላይ በመጣ ትዕዛዝ ” እንዲሻር ተደርጓል፡፡
ሆኖም፣ ህዝባዊ የአዳራሽ ስብሰባ ተከለከለ ማለት፣ የፊርማ ማሰባሰቡ ተከለከለ ማለት ስላልሆነ፣ የፓርቲው ልዑክ ቡድን ሚያዚያ 12/2014 ዓ.ም ወደ አርባ ምንጭ ተጉዞ፣ አገራዊውን የፊርማ ማሰባሰብ ሂደት በአርባምንጭ ከተማ አስጀምሯል፡፡ በዚህም መሠረት፣ የልዑካን ቡድኑ በከተማው ካሉ የድርጅቱ ደጋፊዎች ጋር በመሆን ከአዳራሽ ውጭ ፊርማ የማሰባሰብ ሥራውን አከናውኗል፡፡ አመሻሽ ላይ ግን፣ ፖሊስ የልዑካን ቡድኑ አባላት ያረፉበት ሆቴል ድረስ በመሄድ በቁጥጥር ስር አውሏቸው ወደ ሴቻ ፖሊስ ጣቢያ ወስዶ አስሯቸዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ታስረው ያደሩበት ጣቢያ የመኝታ ቦታ የሌለው በመሆኑ፣ በከፊል ያለ ፍራሽ መሬት ላይ፣ በከፊል ደግሞ ቁጭ ብለው ለማደር ተገደዋል፡፡
በነጋታው የሴቻ ፖሊስ ጣቢያ የታጋቾቹን ቃል በመቀበል ላይ እያለ፣ ከበላይ ስልክ ተደውሎ ቃል የመቀበል ሂደቱ እንዲቆም ከተደረገ በኋላ ወደ ጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ እንዲወሰዱ ተደርጓል፡፡ ከዚያም በፖሊስ አጀብ ወደ አርባ ምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ተሸኝተው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡
በኦሮሞ ብልጽግና የሚመራው ይህ አፈና፣ አገራችን ምንም ዓይነት እውነተኛ የፖለቲካ አማራጭ ኃይል እንዳኖራት ለማድረግ ታቅዶ እንደሆነ ፓርቲያችን ይረዳል፡፡ ከትላንት አሳሪዎች ውድቀት ያልተማረው ተረኛው የኦሮሞ ብልጽግና መንግሥት በሚወስደው አፋኝ እርምጃ ፓርቲያችን ሳይሸማቀቅ፣ የጀመረውን አገር አቀፍ የማድረግ እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም የአገሪቱ ክልሎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡ የኦሮሞ ብልጽግና መራሹ መንግሥት የሚፈፀመው አፈና ፓርቲያችን የተነሳንለትን ዓላማ ከማራመድ የማያስቀረው መሆኑን ተገንዝቦ፣ የሚፈጽመውን ሕገ-ወጥ ተግባር እንዲያቆም እንጠይቃለን፡፡
ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
ሚያዚያ 13 ቀን 2014 ዓ.ም

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Poem
Previous Story

አትሰቀል ይቅር !! እና ተጠየቅ ልጠየቅ !! (አሥራደው ከፈረንሳይ)

278899654 566894108125544 4771623955335057370 n
Next Story

‹‹ሀገር እንዲኖራቸዉ የሚፈልጉ ኢትዮጵያዉን ከአማራ ህዝብ ጋር ይሰለፉ ዘንድ የትግል አካሄዳችንን እንፈትሽ!››፡

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop