አጨብጫቢነት ዴምሕት/ለማ ወዘተ – የመርሕ ድህነት እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ

ዴምሕት የተባለ የትግራዊ ፖለቲካ ድርጅት ኤርትራ በነበረበት ጊዜ እንደተለመደው ብዙ አጨብጫቢ ለማግኘት ችሎ ነበር። እንዴው ህወሓትን ሊጥል የሚችል ኃይል በሚል ብዙ ዜና ይሰራለት እንደነበር አሁንም ከዩቲዩብ ያልተፋቁ ዜናወች ይመሰክራሉ። የዜናው አቅራቢወች ስለ ድርጅቱ ምንነትም ይሁን ማንነት ግድ አልነበራቸውም እናም የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ እያውለበለበ የሚያሳይ የሰለጠነ ወታደር ከኤርትራ መሬት ያሳዩን ነበር። ኮማንደሮቻቸውንም ያስደምጡን ነበር። እንዴውም ጥብቅ እና ዋነኛ የትግል አጋርነቱን ጨምሮ ስለሚገልጹ ብዙ ደጋፊ ነበረው ብል አልዋሸሁም። ነገርን ነገር ያነሳዋል ይባላል የጄኔራል ኃይሉ ጎንፋን እና የጄኔራል ከማል ገልቹን እማ ብዙ ተብሏል። የዴምሕት ዋና ኮማንደር ሞላ አስገዶም በከዳ ማግስት ተመሳሳይ ዜናም ቀርቦ እርሱን የተካው በሚል ብዙ ተብሎለታል። ሲጀመር የኤርትራን የትግል መግቢያነት የተቃወሙ ወገኖች ለምን በሚል ተሰድበዋል። አንዳንድ ጋዜጠኞች ከቦታው ድረስ በመሄድም የኤርትራን መኮንኖች መልካምነት እና ለኢትዮጵያ ደግ አሳቢነት ዘግበዋል። የፈረደበት አጨብጫቢም ስለመርህ ግዱ አይደለም እና ብዙ ብዙ ለግሷል።

ይህን ስል ሂሳብ ለማወራረድ አይደለም ግን መርህ የሚባል ሁነኛ ሰውነትን ከሌላ የሚለይ ቃል አለ። ከማጨብጨብ ይልቅ መጠየቅ ቢቀድም የሚያመዛዝን ፈጣሪ ለሰው ልጅ የሰጠው አመዛዛኝ ልቦና ስለአለን ከስህተት ያድነናል። በይበልጥም አሁን ሀገራችን ከገባችበት ቀውስ እንድትወጣ ያግዘናል። ከመጣ ከሄደው። ጥሩ ከተናገረው እና ከሰበከው ሁሉ ጋር ማጨብጨብ ትቶን ሲሄድ መደናገጥ ከመፍጠሩ በላይ ጠላቶቻችንን ደግፈን ወዳጅን የምናጠፋበት ሁኔታ ደጋግሞ ታይቷል።

የዛሬ አመት “ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው” ስላለው ሰው ብቻ እንደምሳሌ ብንወስድ በእርሱ የአንድ ቀን ንግግር በፍቅር ተቃጥለን ያለቀስንም አንጠፋም። በጀንበር ያፈቀርነውን በአንድ ጀንበር አክ ብለን እንደተፋነው ደግሞ አይተናል ታዝበናል። እዚህ ከምኖርበት ሀገር አሜሪካኖች አንድ ጥሩ እና ጠንካራ ባህርይ ካየሁባቸው ከማወደስ ቁጥብ መሆናቸው ነው። በይበልጥም ሁሉን ነገር የመጠየቅ ባህርያቸው ጠንካራው እና መልካሙን ጎዳና የመራቸው ይመስለኛል። ከንቱ ውዳሴን አለማወቅ፣ መርህን ተከትሎ ይሉኝታ የለሽ ባህርያቸው ሁልግዜ ይማርከኛል። አሜሪካኖች ሁሉን ለምን ብለው ይጠይቃሉ። ለብዙ ግዜ አዝኘ የምሳ እያልሁ እሰጠው የነበረ አንድ ሰው (አዝኘለት ማለት ነው) መጥፎ ስራ ከአይሁበት በኋላ በአንዱ ቀን እንደተለመደው የምሳውን ሊወስድ ሲመጣ የማልሰጠው መህኑን ስነግረው አፋጦ ለምን ብሎ የጠየቀኝን ቀን አልረሳውም። ለክፉም ሆነ ለደጉ አንድ ነገር ከማድረግ በፊት ለምን ብሎ መጠየቅ ጥሩ ነገር ነው ማለቴ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢሳት - በደረጀ ሀብተወልድ (ጋዜጠኛ)

በአንድ ወቅት ወይዘሪት ብርቱካን ሚዲቅሳ የቅንጅት መሪወች ከስር ተፈተው ወደዚህ ወደአሜሪካ የመጣች ቀን አውሮፕላን ሜዳ ሊቀበሉ ከሄዱት እየተንደረደሩ ከእግሯ ስር የወደቁት ሰወች ይታወሱኛል። ለምን ወደቁ ሳይሆን የመውደድ እና የመጥላት ልካችን ድንበር የለሽነቱ ከመስመር እንድንወጣ እያደረገን በማየቴ እና በመታዘቤ ነው። የሰርቬይ ጥያቄ ስትጠየቅ ከ 1 እስከ 10 ስምምነትህን ስጥ ይባላል። እንዳጋጣሚ የዘመናችን የእኛን የኢትዮጵያውያንን ሰው ከሌሎች በዚህ ምላሽ ብናወዳድር በእኛ ምላሽ ፣2፣ 3፣4፣ 5፣ 6፣ 7, 8 እና 9 የሚኖሩ አይመስለኝም። ለጠላነው 1 ለወደድነው 10 የምንሰጥ መስሎ ይሰማኛል።

ወደዋናው ነገር ስመለስ ህወሓት ትናንት ባወጣችው ዜና ዴምሕት የተባለው ትግራዊ ድርጅት። ያውም በኤርትራ ሜዳ ጠበንጃ ታጥቆ ለአመታት ወያኔን ላስወግድ ነው ያለ ድርጅት ሀገር ከገባ በኋላ ድምጹን ሰምቸው አላውቅም ነበር። በትናንትናው ዜና ድምሂት ከህወሓት ተዋሀደ የሚል በሰማሁ ግዜ የታየኝ ለዚህ ድርጅት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የገንዘብ እና ሌላም ድጋፍ ያደረጉ ወገኖቸ ታሪክ ነው። ከፍጥረቷ የምናውቃት ህወሓት በአድርባይ የፖለቲካ ፍልስፍናዋ ጠላቷን ሳይቀር ለእርሷ ግብ እንደምትጠቀምበት ያኔ 1969 ሻለቃ ገብረ ሕይወት የተባለ የመላኩ ተፈራ ምክትል እና የጎንደር አስተዳደር የደርግ ተወካይ የሆነ የህወሓት አባል የጎንደርን ወጣት አርሷደር እንዴት እንደጨረሰ ታሪካችን ነው። ከዚህ እና በቀዩ ሽብር ተሳታፊ የነበረችው የህወሓት ጥቁር ታሪክ እንደተማርሁት ዴምህት (የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያው ንቅናቄ) የህወሓት አገልጋይ እንደነበረ ጥርጥር አልነበረኝም። ይባስ ብሎ ያስፈራኝ የነበረው ገና ህወሓት በስልጣን ላይ በነበረችበት ግዜ ስብሀት ነጋ ወይንም አባይ ጸሀየ አለያም ጌታቸው አሰፋ ከህወሓት ተሳናበትን ብለው መጥተው ይህን ሕዝብ ገንዘቡን እንዳይሞሸልቁት ነበር። መቃወማችን ስለማይቀር እኛም እንዳንሰደብ ነበር። በፈጣሪ ድጋፍ አለፈ። ለዥህ አስተሳሰቤ ምክንያት የሆነኝ ዳዊት ከበደ የተባለ የአውራምባ ጋዜጠኛን ገንዘብ እየከፈሉ ከአገር ለአገር ያዞሩት የነበሩትን ስለአየሁ ነበር። ባጋጣሚ አንድ የታመመ ሰው ለመጠየቅ እቤቱ ስገባ ዳዊት ከማውቃቸው የከተማችን ተቃዋሚ ነን ይሉ የነበር ሰወች ጋር ተቀምጦ አገኘሁት እናም አስተዋውቀው የፖለቲካ አቋሜን ሲነግሩት (ለምን እንደነገሩት እስካሁን አይገባኝም) ዳዊት ግንባሩን እንደተመታ ሰላምታም በቅጡ ሳይሰጠን እንደቀረ ትዝ የለኛል። ይህን ለማለትም የፈለግሁ መርህ የሚሉት ነገር ከሀገራችን ተሟጦ የጠፋ ስለመሰለኝ ነው። ልሰሳት እችላለሁ ግን በአንድ የሰው ንግግር እንደቅርብ ወዳጅ ተሎ መጠምጠም እና በአንድ የአሉባልታ ወሬ መበርገግ የእኛ ስርአት ሆኖ እየታየኝ ተቸግሬአለሁ። በ1998 የህወሓትን ዜጎችን ኤርትራዊ ስለሆናችሁ ውጡ ስትል እና መለስ ዜናው ከህወሓግ አጋሰሶች ጋር ሆኖ አይናቸው ካላማረን ማባረር መብታችን ነው ሲለን ያጨበቸቡ እና ውስኪ የከፈቱ ልንታገር ኤርትራ ገባን ላለሉት ቀድመው አፋሽ አጎንባሽ እንደሆኑ የማልረሳው ተውኔት ሆኖብኝ ቆይቷል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ትዝብት ቁ.23- ልማት ሲሉ፣ ልማት ስንል (አገሬ አዲስ)

መርህ ከሌለን ሁሌም ድጋፋችን ለጠላት ብቻ እንጅ ሀገርን እና ወገንን ልናጠናክር አይቻለንም። እና ጥያቄ ምን ይሁን ምን ማድረግ ይገባናል? ነው። በበኩሌ ለመጣ ለሄደው አፋሽ አጎንባሽ መሆን ተገቢም አይደለም ሀገርን የበለጠ የሚጎዳ አጥፊ ጠላትን መተባበር ነው ባይ ነኝ። መርህ ስንል ሀገራችን ኢትዮጵያ ነጻ ሀገር ናት የዘር ፖለቲካ መወገድ አለበት ስንል ይህን ለማስወገድ ከምር ከሚሰሩት ጋር ማበር እና አምርሮ መታገል ይገባል ባይ ነኝ። የዘር ፖለቲካን እንቃወማለን ብለው ከኦነግ እና መስል ድርጅቶች ጋር የተለጠፉት በየትኛውም መልክ ነጻ ሊሆኑ አይችሉም።

ለአመታት ከጠላት ጎን ቆመው ሕዝብ የገደሉ ያስገደሉ ንስሀ ሳይቀበሉ በአንድ ጀንበር እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ መግባት ለሀገርም ሆነ ለግል ጎጅ ባህርይ ነው። “ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው” ያለው ሰው ምን ያሕል ሰውን እንዳሳበደ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው። የማታ ማታ “ሕዝቤ” ያለው ያው ተጠምቆ ያደገበቱን የዘር መንደሩን ሰው ብቻ ነው። ይህ ሰው ስለኢትዮጵያም ሆነ ስለሏላዊነታ ግዱ እንዳይደለ በሰሞኑ በሰጠው የአሜሪካ ድምጽ ቃለምልልስ አስረድቷል። የመንጋ ፖለቲካ ይብቃ። ለአመታት ሀገር በባንዳ ጠባብ ብሄርተኛ ስትታመስ አንገት ደፍቶ ይሰራ የነበር እና ፖለቲካ እና ኤሌትሪክ በሩቅ ያለ በአንድ ጀንበር ብቅ ብሎ አራጊ ፈጣሪ ሆኖ ሲገኝ እና ተደማጭ ሲሆን በእውነቱ ዋ እንድንል አስገድጎናል። እንዲህ አይነቱ መብዛት እና መበረታታት ደግሞ ሀገር እና ወገን መሪ አልባ እንዳደረገ ግልጽ ነው። በክፉ ቀን ይህን መሰል ሰወች ልክ እንደበረዶ ክምር ሟሙተው ድራሻቸው ስለሚጠፋ ማለት ነው። የፈሪ መንጋን ስለተናገረ ማጀገንም ሌላው ጎጅ ዘመን አመጣሹ ክፉ ባህርይ ነው። ጠላት ውስጥ ለውስጥ እየተደራጀ እያደራጀ፤ እያስተጠቀ እያሰለጠነ ባለበት በባዶ ሜዳ ሰባራ ክላሽን ይዞ መፎከር ለቁርጥ ቀን ልጆች የሚጎዳ ነው። ገንዘብ እየሰበሰቡ ለማይረባ እና ለምናውቀው ፈርጣጭ ማሸከም ለኋላ ክህደት እና ትዝብ ካልሆነ ፋይዳው ብዙ አይደለም። ስለሌሎች ከማውራት እራስን ማደራጀት፣ እና ለክፉም ሆነ ለደግ መጭ ዘመን ዝግጁ ሆኖ መገኘት ለሀገር ለወገን እና ለእራስም መመኪያነት ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ላይ ወያኔያዊ የክተት ዘመቻ (ነፃነት ዘለቀ)

ህወሓት ለኢትዮጵያ አትተኛም። ህወሓትን መከወን የወደፊት ከባዱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ስራ እና ተግባር ይመስለኛል የሀገሪቱን አንድነት በአስተማማኝ ለማስቀጠልም ሆነ ነጻ ሕዝባዊ መንግስት ለመመስረት። የህወሓት መሪወች ሸሽተው መቀሌ ስለገቡ ተወግደዋል ማለት ግን አለመሆኑን ልናውቅ ይገባል።፡የሀገሪቱ ደህንነት መዋቅር፣ የወታደራዊ እና የፖለቲካ ሰንሰለቱ ምን ያህል ከዚህች ጸረ ሕዝብ ድርጅት ነጻ ነው? Command post መቀሌ አድርጋስ ተዛዝ በእዝ ለማስተላለፍ አለመቻሏን እንዴት ልናውቅ እንችላለን። ይህ እና ብዙ መሰል ጉዳዮችን ማንሳት ይቻላል። ለሁሉም ከመንጋ ፖለቲካ መውጣት። እራስን ማደራጀት እና ከሚመስሉት ጋር ኃይል ሆኖ መውጣት ለነገ የማይባል የዚህ ትውልድ ግዴታ ነው። የያ ትውልድ እንቁወች እና ያልተንበረከኩ ዛሬም ስለአሉ ከነሱ ስህተት መማር። ጥንካሬአቸውን ደግሞ መውሰድ ይቻላል ይገባልም።

ከዚህ በተረፈ ለመጣ ለሄደ አፈኛ ማጨብጨቡን ትተን እራስ ግምገማ እና መደራጀት ላይ ብናተኩር ይገባል ባይ ነኝ። መርህ ይቅደም! ማጨብጨብ ይቁም!

Adios!

 

3 Comments

  1. የደምሂት ከህወሓት ጋር መዋሃድ ለምን ይገርምሃል? በፀረ ወያኔ ትግሉ አለም የሚያዉቀዉ ጀዋር ህወሓት ስትርራቴጂያዊ ወዳጅ ነዉ ሲል አልሰማህም እንዴ? እንዲይ አይነት መንሸራተትና መፈላለፍ አልጠብቅ እንደሆን የዋሁ አንተ ራስህ ነህ! ይህ የጥቅምና የፍላጎት ጉዳይ ነዉ- ዛሬ ያልተመሳሰለ ጥቅምና ፍላጎት ነገ ሲመሳሰል ዛሬ የተገዳደሉ ሃይሎች ነገ ጓደኛ ይሆናሉኮ

  2. EPRDF always gets many supporters over the years, some intimidated , some bribed , some fooled , some just because they were against DERG or against Shabiya and some for many other reasons, all of whom supported EPRDF one time or the other in the last 30 years, just only sooner or later eventually to end up getting their blood sucked dry by TPLF , TPLF finally murdered Legesse himself since it is their nature to kill nonstop, as Legesse himself killed the real Meles longtime ago and stole his identity of being TPLF EPRDF’s leader.In 1991 when Legesse showed his face on TV saying he is Meles many of the TPLF rebel fighters were saddened to see a stranger face saying he is their leader Meles, many diserted at that instance who went to form this army trying to oust this imposter Legesse who killed their real leader the real Meles. Now years later they rejoined TPLF.

    After Legesse got murdered Very few lived to show their faces around TPLF even Hailemariam resigned and Demeke declined just to get away from TPLF not knowing all of EPRDF is already infected with the ODP Continuing it’s vampire action it learnt from TPLF within the last two years.

    Since it’s inception in 1989 until 2019 for thirty years EPRDF used and abused many. One thing about EPRDF is, it cannot survive without sucking the blood out of fresh meat because without fresh meat they will suck each other’s blood dry, now many such as ODP kept their distances after years of getting their blood sucked dry. ODP got tired of getting it’s blood sucked, now ODP is sucking others blood in turn to replenish what TPLF sucked out of ODP. Ambachew , NAMA , Baladera ,Asaminew , Saere and the rest bloods is not on ODP’s hand their blood is inside ODP’s throat , they were fresh meat for ODP.
    Now with them out of the way the EPRDF vampire is recruiting young genocidal vampires by ODP recruiting Querro and TPLF recruiting the Tigray youth by eliminating the “opposition” one by one, ADP or what’s left of ADP , cheating Amara youth with this fairy tale Party called Prosperity. Ethiopia is fighting not to get their blood sucked by the vampire EPRDF too.

    Even you Call yourself different names as much as you want Meles Legesse Abyot Abiy EPRDF Prosperity OPDO ODP ANDM ADP Minase Woldegiorgis-ABA Dulla Gemeda Workneh Gebeyehu Woldekidan- Workneh Gebeyehu Negewo Kuma Demeksa-Taye Teklehaimanot ….we call you simply the vampires.

  3. አስተያየትህ ኣምንበታለሁ። ግን እውነት እንነጋገር ከተባለ የፓለቲካ ፕሮግራማቸው ቢመቸንም ባይመቸንም እንደ ህወሓት የመርህ ድርጅት አለ?ላመንክበት በፅናት መቆም በይትኛውም የፓለቲካ ፓርቲ በአገራችን ይስተዋለል?ሌላው ቀርቶ 27 ዓመት አብረው ሲወስኑ ሲያስወስኑ ሲፈፅሙ ሲያስፈፅሙ የነበሩ ሰዎች አይደለም እንዴ የፍትህ እና የዲሞክራሲ ሻምፕዮን እንደነበሩ እና እንደሆኑ የሚናገሩት እና እኛም የተቀበልናቸው? እንድያው እኛ ኢትዮጵያውያን በምክንያት ስንደግፍም ሆነ ስንቃወም እንታወቃልን? በፍፁም!

Comments are closed.

Share