በአዲስ አበባ የሩዋንዳ ኤምባሲ የጥበቃ ሰራተኛ ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ጥበቃ ላይ እያለ ተገደለ

የሩዋንዳ ኤምባሲ ጥበቃ የሆኑት አቶ ሸረፋ በጥበቃ ላይ እንዳሉ በተተኮሰ ጥይት ሞተዋል። የኤምባሲው የሴኩሪቲ ኃላፊ ሚስተር ጆን በነበረው ሁኔታ በማዘንና በመበሳጨት “እንዴት በስራ ላይ ያለን ሰው ተኩሳችሁ ትገላላችሁ? ኤምባሲውን ደፍራችኃል” በማለት ፖሊሶች ወደ ግቢው እንዳይገቡ ያደረገ ሲሆን የሟችን ሬሳ ከሌሊቱ 4 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት ድረስ ሳይነሳ ቆይቷል። በድናቸው ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅትም አባዲና ቦታው ላይ መጥቶ ምርመራ እያከናወነ ይገኛል። የአዲስ አበባ ፖሊስና የፌዴራል ፖሊስ በብዛት ቦታው ላይ ይገኛሉ።

ጋዜጠኛ ሀብታሙ ምናለ

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወልድያ ከተማ ነዋሪዎች የመንግሥትን አፋጣኝ እርምጃ ጠየቁ (ወልድያ ከተማ ኮሙኒኬሽን)

1 Comment

  1. This murder is very suspicious involving invasion of privacy at the embassy located near to where the imprisoned politician Bereket Simon’s previous mansion now sold for 42 Million birrs to the media mogul Jawar Mohammed who recently turned into a politician .

Comments are closed.

Share