አስቀያሚው የኢሕአዴግ ድራማ የሽፍጥ ፖለቲካ

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ላይ መፈንቅለ መንግስት ተደረገ የሚል የፌዴራል መንግስቱ ድራማ ሴራ የተቀላቀለባት መሆኗ ነጋሪ አያሻም። የክልሉ መንግስትና በባህር ዳር ያሉ ሚዲያዎች ሳይናገሩት የፌዴራል መንግስት ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረውን መግለጫ መስጠቱ የሽፍጥ ፖለቲካው አካል ለመሆኑ ምስክር አያሻውም። የመከላከያ ሰራዊት ዝግጁ ሆኖ በሰዓቱ በቦታው መገኘቱና ለተለያዩ ሃገራዊ ጉዳዮች መግለጫ ለመስተት አሻፈረኝ የሚሉ እነ ንጉሱ ጥላፉን በብርሃን ፍጥነት ስለመፈንቅለ መንግስት መደስኮራቸው የተሴረውን ተንኮል ፍንትው አድርጎ ያሳያል። መመታት መገደል መታሰር ያለባቸውን አፋፍሶ ለማሰር ያልተመቸው የፌዴራል መንግስቱ የወጠናት ሴራ መሆኑን ማንም የፖለቲካ ተንታኝ አያስፈልገውም። ኢሕአዴግ በእንዲህ አይነቱ የፖለቲካው ድራማ ይታወቃል። ይህንን ሴራ ተከትሎ በቁጥጥር ስር የሚውሉትን ኢሕአዴግ ጠላት ብሎ የፈረጃቸውን ሰዎች በመመልከት ብቻ በመፈንቅለ መንግስት ስም የጦዘውን ድራማ ውጤት ማረጋገጥ ይቻላል።

ምንሊክ ሳልሳዊ

ተጨማሪ ያንብቡ:  አረና ለአንድነት የውህደት ጥያቄ አቀረበ

5 Comments

  1. በዚህ እለት ይህንን ቅርሻት ስትለቀልቅ ትንሽ እንኳ አታፍርም:: ክርስቶስ ይታረቅህ:: ለአንተ ሚጢጢ ጭንቅላት የተገለጠው ለብዙዎቻችን አልተገለጠም ማለት ነው?

  2. ይህ የፖለቲካ ድራማ በሰውህይወት የቀለደ ሰፊውን ሀዘብ ለማሞኘት የተከወነ ግን በሃሰት የታጀለ የሴራ ፖለቲካ ውጢት ነው። ነገ ፀሃይ ትወጣለች እውነት ይገልጣል ሁሉም ፍርዱን ይቀበላል። የ አንድን ፓርቲ ሪፓርት ብቻ ሰምተን ለፍርድ የምንቸኩል ሞኞች ሙሆን የለብንም ምክንያትም ብዙ እውነት የማይመሰሉ ከስተቶቸ እያሰማን ስለሆነ ና በጣም ፈጣን ዜና የተሰራበት ነው።

Comments are closed.

Share