ትግራይ ማለት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ማለት ትግራይ ናት፡ – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

ኢትዮጵያ ትግራይ ትግራዋይ ኢትዮጵያ ነው
” በይ ደህና ሰንብቺ …አልተገናኘንም
ቻው!ቻው!  ደህና ሰንብቺ…ደብረ ፅዮንም፡፡
‘አልተገናኝቶም ‘ ባይ!ባይ! ነጋሽ መሥጂድ
ጠፍቷል በወያኔ ሰው ሆኖ ሰው መውደድ፡፡
ቋንቋ ናችሁ ብሎናል…ሰው ከቶ አይደላችሁም
አልነበረም እንዴ የሰው ሀገር…በዘመኑ አክሱም ?”
እያልን… ስንሞገት
ስንጮኽ… ለሰውነት
“ጉንደት ጉንዳጉንዴ…ዶጋሊ፣አባላጌ፣ ይቅሩና
የመቀሌው ተጋድሎ…የአደዋው ድል ይረሳና…
በኃይል እንገንጥላት…ትገራይን ከእናቷ
ጥቂቶቻችንን ከልጠቀመች ኢትዮጵያ ምን አባቷ !
ተፋቅረን፣ተዋደን፤ ተሻርከን ፣ከኤረትራ ጋር
እንሆናለን እኛ ወደብ ያለን – ሀብታም ሀገር፡፡…”
የሚለውን ዜና የሰማነው በህለማችን ይሆናል…
ኢትዮጵያዊው  ከኢትዮጵያ፣ ከቶስ እንዴት ይገነጠላል ?
“በሥመ አብ !” “ቢስሚላሂ !” ያሰኛል “ሆቸው ጉድ!”
“እገነጠላለሁ በል!” ህዝብ ሲባል በግድ ፡፡
ኩሩውን ኢትዮጵያዊ ፤”እንገንጠል!” ሲለው
ምንው አጣ ጎበዝ ፣አፉን የሚያሲዘው?
አኩሪ ታሪካችንን ፣በዋዛ ለመደምደም
የግል ሐሳቡን በአደባባይ ሲያወራ በህዝብ ሥም
ዝም ብለን አናዳምጥ ፣እውነቱን እንንገረው
ኢትዮጵያ ትግራይ፤ትግራዋይ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡
   ሰኔ 8/2011 ዓ/ም መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ
የትግራይ ህዝብ በእውኑ  በገሃዱ ዓለም ውስጥ ሆኖ ይቅርና በህልም እና  በቅዠት ዓለም ውስጥ ሆኖ  እንኳን ቢሆን የማይናገረው  የድፈረት ቃል ቢኖር ” ከኢትዮጵያ እንገነጠላለን ፡፡”የሚለው መሆኑን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡፡ይህንን ፀያፍ ቃል ፣ ለታሪክ ደንታ የሌላቸው ሀገርን ለማሰከበር ሳይሆን ኪሳቸውን ለማስከበር የሚኖሩ ግለሰቦች ሺ ጊዜ በመደጋገም ሊናገሩት እንደሚችሉ ግን ማንም አያስተባብልም፡፡
      የትግራይ ህዝብ ግን እንደ ህዝብ በህልሙም በእውኑም የሚያስበው ሥለ ኢትዮጵያ ታለቅነት እንጂ ኮሥሣነትና አቅመ ቢስነት ከቶም አይደለም፡፡
     ማንም ሀገር ወዳድ ፣ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ሥለ ኢትዮጵያ ብልፅግና ሲያወሳ ሥለ ትግራይ ህዝብም ብልፅግና እና ልማት ጭምር እያወሳ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ሥለ አትዮጵያ ህዝብ ጀግንነት እና ኩራት ሲያወሳም ሥለትግራይ ህዝብ ጀግንነትና የተጋድሎ ታሪክ ማውሰቱ እነደሆንም ማስተባበል አይቻልም።
  ያ የኢትዮጵያችን ክልል ለብዙ  ዓመታት የጦርነት ቀጠና ሆኖ እንደኖረ እና ኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንዳቸውን ጠላቶቻቸው ላይ በማሳረፍ ተደጋጋሚ ድልን የተጎናፀፉበት የጦር አውድማ እነደነበር መዘንጋት ከቶም የለበትም፡፡
     የትግራይ ህዝብ በግሉም፣ለዘመናት የባህር በር ጠባቂ በመሆን እንደኖረ ፣የጥንቱ ባህረ ነጋሽ (የአሁኑ የቀይ ባህር ስያሜ ነበር፡፡ ) ባለቤትም እንደነበር ማስታወስ ቅዠታሞቹን ከቅዠታቸው እንዲነቁ ያደርጋቸዋል ፡፡የትግራይን ህዝብም ሆነ የኢትየጵያን ህዝብ ከድህነት እነዳይወጣ ያንን የመበልፀጊያ ምነጩን ያሳጡት ለፍርፋሪ አድረው፣ ለነጭ ባንዳነት ተገዝተው፣ ያደሩ “ከራስ በላይ ነፋስ!” ባይ ፣ ሆድ አደር የሆኑት ወንድሞቻችን እነደሆኑ ከራሱ ፣ከትግራይ ህዝብ የተሰወረ ከቶም አይደለም፡፡ይህ ኩሩ እና ጀግና ህዝብ አሁን ያለችንንም ሀገር ያተረፈልን በየዘመናቱ ከባንዶች ጋር እየተናነቀ መሆኑንንም ወደኋላ ተመልሶ ከታሪክ መዛግብት መረዳት ተገቢ ይመስለኛል ፡፡ ይህንን ፈጽሞ  ባለመረዳት ፣እነሆ ዛሬም አንድ በህመም የናወዘ ትግራዋይ   ታሞ እነኳ በቅዠት ውስጥ  የማያስበውን “ከኢትዮጵያ የመንገጠል” ሃሰብ ፣ መሞታቸውን የዘነጉ ና ለታሪክና ለህዝብ ደነታ ቢስ የሆኑ የምቾት ና የድሎት አመላኪዎቹ “ልተገነጠል አስበሃል፡፡” በማለት ከቶም ያላሰበውን  እየነገሩት ነው፡፡ይገርማል፡፡     የሚገርመው ነገር የትግራይ ህዝብ “በወያኔ” አገዛዝ ጠብ ያለለት ነገር ሳይኖር፣ዛሬም አፈር መስሎ ከአፈር ጋራ እየታገለ መኖሩ እየታወቀ፣መሰረታዊ ፍላጎቱን እንኳ ያላሟሉለትን ምሥኪን ህዝብ ፣ ልክ እንደደላውና ሙቅ እንደሚያኝክ በመቁጠር፣ “ሊገነጠል አስቧል፡፡” መባሉ ነው።
      ዛሬም የትግራይ ህዝብ እንደተቀረው ወገኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ፣በከፋ ድህነት ውስጥ ነው እየኖረ ያለው፡፡መሰረታዊ ፍላጎቶቹ አልተሟሉለትም፡፡በቂ ፣ምግብ፣መጠለያ ና ልበስ የለውም፡፡ብዙሃኑ ደኸይቶ ጥቂቶች ስለተተረፈረፋቸው የትግራይ ህዝብ በወርቅ ፈራሽ ላይ እየተኛ ነው ብሎ ማውራት በቁም እንደ መቃዠት ይቆጠራል፡፡ በቅዠት ውሥጥም ሆኖ  ሥለመገንጠል ማውረት ፣በመላው ኢትዮጵያ ከተሞች ተፋቅሮ፣ተዋዶና፣ተጋብቶ ና ተዛምዶ የሚኖረውን የትገራይ ተወላጅ የሆነን ኢትዮጵያዊ ዜጋ ስጋት ውስጥ መጨመር ነው፡፡ትላንትና የኤርትራ ተወላጅ ወንድምና እህቶቻችን ከኢትዮጵያ ውጡ ሲባሉ ያነቡትን ደም እንባ ከቶም የምንዘነጋው አይደለምና ይህንን  ታማሚ ና ቅዠታም ሰው እንኳን የማያስበውን “የሴጣን ጆሮ አይስማው። የሚያሰኝን አፈራሽ ሃሰብ አንድ ኃላፊነት ያለበት ሰው መናገሩ በእጅጉ የሚሳፍር እና የሚሳዝን ነው፡፡
     ይህ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል ፡፡” በማለት ፣ለእኔ ያልተመቸችኝ ኢትዮጵያ ለምን 80 ሀገር በመሆን አትሸነሸንም በማለት፣ካለፉት ቅኝ ገዢዎቻችን በከፋ መልኩ ሥለኢትዮጵያ መበታተን አጥበቆ ወይም ተግቶ መስራት ነውና ልናወግዘው ይገባናል፡፡
    አባቶቻችን ህይወታቸውን ሳይሰስቱ ፣ለእኛ ክብርና፣ኩራት ፣በታለቅ የሀገር ፍቅር ሥሜት ተሰውተው ፣በደማቸው ያቆዩንን ሀገር፣እንደዋዛ ስትፈራርስ፣መመልከት እጅግ አሳፈሪ፣አስጠሊና አሳዛኝ ውርደት ነው፡፡ይህንን ውርደት ከምናይ ከባንዶች ጋር ተናንቀን መሞት ለእኛ ዘላለማዊ ክብር ነው፡፡
ይህቺ ሀገር እንደው እንደዋዛ እዚህ ደረጃ እንዳልደረሰችም የመናስመሰክረው ዛሬም ፣የትላንትናዎቹ ጀገኖች አባቶቻችን ደም በውስጣችን እንዳለ በተግባር ስናስመሰክር ብቻ ነው፡፡ይህቺ ሀገር እኮ እንዲሁ እንደዋዛ ኢትዮጵያ እየተበለች ለዛሬ አልበቃችም።
     ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እየተባለች ለዛሬ የበቃችው በትላንትና ልጆችዋ መሰዋትነት ነው፡፡ኢትዮጵያ የሚለውን ስያሜዋን ፣ከታሪክ ገፅ ለማጥፋት በሁሉም ዘመናት  የልተሸረበ ሤራ እነደልነበረ ታሪክ ይነግረናል፡፡ዛሬም በ 21ኛው ክ/ዘ ይህ የጠላቶቻችን ሴራ በረቀቀ መልኩ እየተከናወነ ነው፡፡ዓለም በስልጣኔ እየገሰገሰ በሚሄድበት ወቅት የእኛ እርስ በእርስ መነካከስ የሴራውን ተከታታይነት ያሣብቃል።
 ዓለም በሥልጣኔ በገሰገሰበት በ21ኛው ከ/ዘ እኛ ገና እንደ ጥንት ኃይማኖት አለባ ህዝቦች በቋንቋ ልዩነት ብቻ፣ጠመንጃ አንስተን በመገዳደል ላይ ነን፡፡ይህ ድርጊታችን ሰውን በሰውነቱ ብቻ ተቀብለው በሚኖሩ የዓለም ህዝቦች ዘንድ መሳለቅያ አድርጎናል፡፡ አንድ አንድ ወዳጆቻችንም “የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው፡፡” በሚል መርሃቸው መታለባችንን ብቻ ነው የሚፈልጉት፡፡ የእኛ መበላላትም ሰርግና ምላሻቸው የሆኑ እንዳሉ መዘንጋት የለብንም፡፡
    የጠበቀ ወዳጅነት ከቻይና ጋር ቢኖረንም ቅሉ፣የቻይናን ኮሚኒስት ፓርቲ ውሥጥ ያለው ከብረት የጠነከረ ዲሲፕሊን” በእኛ ፖለቲካ ውስጥ እነዲሰርፅ ባለማድረጋችን  እንደቻይና ህዝብ በአጭር ጊዜ ለመበልፀግ አልቻልንም፡፡
     የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ፣በማኦ ዘመን ያደረገውን ኩንን ተግባር ምዕራብውያኑ ቢያወግዙትም፤ ባራቀውም ጊዜ በቲያሚን አደባባይ የቻይና ወጣቶች እንደቅጠል ቢረግፉም ቅሉ … ቻይና  ዜጎቿ ሰው እና ቻይናዊ መሆናቸውን አውቀው ለሀገራቸው ጥቅም ሲሉ  ለመሰዋት ወደኋላ እንዳይሉ ከልጅነታቸው ጀምሮ በማሰተማር ሀገር አፍቃሪ ተውልድ መፍጠሯን ዓለም የመሰክርላታል፡፡እኛስ?
    እኛማ ዛሬም እንዳልሰለጠነ ህዝብ ሰውነታችንን በመካድ ፣ “እኔ ቅብርጥስዬ !አንተ ቅብርጥስዮ !ነህ።” እየተባባልን ፣ እንደ አውሬ እንበላላለን፡፡ (በአንድ ከተማ የሚኖር ድብልቅ ህዝብ ላይ አንድ ቋንቋ ተናጋሪ ፈላጭና ቆራጭ እንዲሆን በማድረግ የህግ የበላይነትን፣ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብትን ገደል እንከታቸዋለን፡፡ ከተሞች በኗሪዎቻቸው እንጂ በቋንቋ እንዴት ይስተዳደራሉ? ይህ አንዱን ቋንቋ አግዝፎ ሌሎቹን  ማንኳሰስ            አይደለም እንዴ? በዚህ ኢ ፍትሃዊ አሥተዳደርሥ የሚጎዳው አገልግሎት ፈላጊው ኗዋሪው ዜጋ መሆኑ መንግሥት አይገነዘብም ለማለት እንዴት ይቻላል???።)
 እርግጥ ነው። ነገ እኛ 80 ቦታ ብንሸነሸን ቻይና ጉዳዮ አይደለም ፡፡የኢኮኖሚ አቅም ስላላት ከ80 ዎቹ ጋር ተሸርካ ጥቅሞን ታስቀጥላለች።፡፡መጥኔ ለእኛ እና የታሪክ አተላ ላደረጉን ጥንባሳዎቻችን፡፡
     ዛሬ፣ዛሬ በየአቅጣጫው የታሪክ አተላ ለመሆን የሚሯሯጠው በዝቷል፡፡ጀግንነት ማለት እሰከ ህይወት መሰዋትነት ድረስ እነኳ ቢሆን ትልቅ ዋጋ በመክፈል ለሀገርና ለህዝብ ፋይዳ ያለው ቁም ነገር መስረት መሆኑ ተዘንግቷል፡፡በተገላቢጦሽ ሥንትና ሥንት ኢትዮጵያዊያን ታለቅ መስዋትነት ከፍለው ያቆዩልንን ሀገር፣ለማጥፋት ያለእረፍት የሜያሴሩ ጉዶች በጉያችን ተፈጥረዋል፡፡የህቺ ሀገር በጽዱ አጆቻቸው           በሚታወቁ፣ሌባ፣አጭበርባሪና ዘራፊ ባልሆኑ ፣በላብአቸው ፍሬ በሚደሰቱ ህዝቦቿ ትላንት እንደቆመች ሁሉ ዛሬም ያንን ማድረግ እነደማይሳነት ግን አለተገነዘቡም፡፡…ታሪክ እንደሚመሰክረው፣ “የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ፣ ሳይውል ሳያድር ፡፡…”
 እናም፣ዛሬም የትግራይ ኩሩ ና ጀግና ህዝብ እንኳን በእውኑ በህልሙ የማየስበውን የቁም ቅዠታቸውን በትግራይ ህዝብ ላይ ለማጋበት ወይም ለማላከክ ቀና ደፋ የሚሉትን ፣የኢትዮጵያ አምላክ ሳይውል ሳያድር እንደሚፈርድባቸው አትጠራጠሩ፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ:  የ"ደም ጠማኝ!" ባለ ሥልጣናት በአማራው ሕይወት መጫወት

9 Comments

  1. Tigray as an independent state had been one of the oldest free countries in the world. It had its own and ancient civilization and was a developed regional power with its ancient Axumite kingdom. The decline of Tigray as a regional power began with its unfortunate contact with the underdeveloped and poor regions in the south.
    This part of the Tigrayan history is a good proof that the interface and interaction between a developed and modern society on the one hand and the underdeveloped and primitive societies on the other one can negatively affect the former. This is what happened to Tigray as part of Ethiopia.

    • To be honest, it’s never too late. Tigreans never wished to be Ethiopians as much as naive Ethiopians want them to be. This change has come at a very good time before history made it too late for ethiopia to be looted completely dry. As you may know how many non tigreans like Amahras and Oroomos migrated to Tigray for opportunities and resided there? None at all!. Actually it makes a lot of sense to fulfill your wishes and for Tigrai to be completely cut off and become independent.

  2. ወያኔ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው። አሁን እንሆ በአዲስ አበባ ከትግራይ ለመጣ ቡድን የኳስ ደጋፊዎች የሚዘፍኑት በወያኔ ጊዜ ተወልደው በዚሁ ስርአት እነርሱና ወላጆቻቸው ተጠቅመው በህዝባችን ለ27 ዓመታት ሃበሳን ላደረሰ ቡድን እኔ ወያኔ ነኝ እኔ ጌታቸው አሰፋ ነኝ ማለቱ የቱን ያህል የተበረዘ ትውልድ እንደሆነ ያሳያል። አለማችን ወደ አንድነት ስትሄ እነዚህ በብሄር እና ባለፈ ጠማማ ታሪክ የሰከሩ ወጣቶች ከተማ እንደዚያ ሲያምሱ ማየት ያስጠላል።
    በመሰረቱ ወያኔ ከበረሃ ጀምሮ አላማው ትግራይን መገንጠል ነው። የሰፋ ዳቦ ሲመለከት ሃሳቡን ለውጦ በሃገሪቱ አንጡራ ሃብት ትግራይን አልምቶ ገሸሸ ለማለትና ራሱን የትግራይ ሪፕብሊክ ብሎ በመሰየም ለመገንጠል እቅድ እንዳለው የበረሃና የከተማ ተንኮሉ ያመላክታል። ለዛም ነው እኛ ከስልጣን ከወረድን ኢትዮጵያ ትፈርሳለች እያሉ የሚያስፈራሩን የነበሩት። ዶ/ር ደብረጽዪን የሂሊና በሽታ ያለባቸው ሰው ይመስላሉ። ለነገሩ የዛን ሁሉ ንጹሃን ሰው ደም በከንቱ ያፈሰሱ እንዴት የአእምሮ በሽተኛ መሆን ይነሳቸው? የውሽት የፓለቲካ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛው ወያኔ ሃርነት ትግራይ ዛሬም ሳያፍር የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ መገንጠል ይፈልጋል ይሉናል። እውነቱ ግን ወያኔ ነው መገንጠል የሚሻው እንጂ የትግራይ ህዝብ ሃገሩን ወዳድ እና የፈጣሪ ፈርሃ እግዚአብሄር ያለበት ህዝብ ነው። ወያኔ እስቲ ተገንጠሉ እና እንያችሁ። ምን ልታመጡ ነው ከረሃብና ከደም ማፋሰስ ሌላ? የተካናቹሁት በሴራና በደባ ነው። በአክሱም ዪንቭርስቲ ግድያና ወከባ የደረሰባቸው የአማራ ተማሪዎች በወያኔ አንሳሽነት እንደሆነ እየታወቀ ዶ/ር ደብረጽዮን አሳፋሪ ነገር ነው ይሉናል። በመሰረቱ ትግራይ ውስጥ የወያኔ የስለላ መረብ ሳያውቅ ሽንት መሽናት አይቻልም። ግን ግድያውና ወከባው የደብረማርቆሱን የጅምላ ፍርድ ለመበቀል እንደሆነ ምንም አያጠራጥርም። የአማራና የትግራይ ጠባብ ብሄርተኞች ሲፋለሙ በመካከል የድሃ ልጅ መሞቱ እጅግ ያሳዝናል። ተምረናል አውቀናል የሚሉ የትምህርት ተቋማት በዘር ፓለቲካ ሲታመሱ፤ እሳት በህንጻዎች ላይ ሲለቀቅ ይህ ትውልድ ተምሮ ለሃገር ይጠቅማል ማለት ጅልነት ነው። ዶ/ር ደብረጽዮንም የመገንጠል ሃሳብ ያለው የትግራይ ህዝብ ነው እኛ ተው እያለነው ነው መሮታል የሚሉት ከወያኔ ለመገንጠል ያሰበውን እንጂ ከኢትዮጵያ አይደለም። ግን እንደ ዶ/ር ደብረጽዮን ያለ ወላዋይና የአገኘውን አቅፎ፤ ሌላውን ነክሶ ሁለቱንም በጉድጓድ የሚጨምር መሰሪ ሰው በምድራችን የለም። ሳቃቸው መከራን ያዘለ፤ ቃላቸው የሚያምታታ፤ ማዘናቸው ፍሬ የለሽ (የስመኘውን ልጆችና ቤተሰቦች ለመርዳት የገቡትን ቃል) እንዲሁ እየነጋ የሚጨልምባቸው ፍጡር ናቸው። ሰው እንዴት በቃኝ ፓለቲካ። እስካሁን እየዘረፍኩ ያካበትኩት ሃብት ይበቃኛል በማለት ሥልጣን ለአዲሱ ትውልድ አይለቁም? ይህ አይታሰብም። አሁን ደግሞ የትግራይ ህዝብ መገንጠል ይፈልጋል ይሉናል። እሺ ተገንጠሉና እንይ። አድርጉት። ወያኔን የሚበላ እሳት እንደሚሆን ግን ከአሁኑ መገመት ይቻላል።

  3. TPLF is ready to pay reparations to Tigrayans only. To do that Tigray has to become independent to exclude other ethnicities from claiming reparations too.

  4. “ከባለቤቱ በላይ የሚያውቅ ጠንቋይ ነው” ይባላል:: ሰውዬ እና አንተ ከትግሬዎች የበለጠ ስለትግሬዎች ፍላጎትና ማንነት አቃለሁ እያልክ ነው? ትግሬዎች መገንጠል ፈልገዋል ተብሏል እኛም መሄድ በመፈለጋቸው ደስ ብሎናል:: ቶሎ ሄደው ሰላማችን እስክናገኝ ቸኩለናል::

  5. Tostaassaa hullaa! Min tamexaleh agame bihed? Giligil ayidel inde? Monyihin felig. Inesu ayihedum. Lemany yet yihedal. Yelemedew zerefa inkuwan biqer texabqo firifarii yileqmal injii yet yihedal????!!!!!!!

  6. “አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀቃል” እንዲሉ የመኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ ለመሰሪዎች ያለው ልዩ ፍቅር ይገርማል ። ምን ያድርግ እሱ የሚኖረው ባሜሪካ።

Comments are closed.

Share