የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዳይሰራ አስደርጎት የነበረው በዛሬው የቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ መታሰቢያ ሐውልት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ግቢ ውስጥ ተመረቀ።
https://www.youtube.com/watch?v=mk2qgm5fFUY&t=89s
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዳይሰራ አስደርጎት የነበረው በዛሬው የቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ መታሰቢያ ሐውልት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ግቢ ውስጥ ተመረቀ።
https://www.youtube.com/watch?v=mk2qgm5fFUY&t=89s
Comments are closed.
This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.
Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.
If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.
እናት የወለደው የኢትዮጵያ ጀግና ደግ ያስባል ያልማል የሰይጣን ቁራጭ ግን ሁሌም ጥፋትን ተንኮልን ባጠቃላይ ሰይጣናዊ ተልኮውን በምድር ሲያስፋፋ ያልፋል ይህም ማለት የሚያረካው ደም መምጠጥ እንጅ የሰው ልጅ በተᎂላ ህይወት እንዲኖር ሰለማይወድ
ሐውልት ቆመላቸው።
ቀ.ኃ.ሥ ንጉሠነገስት ናቸው፤
ጠላት ድብን ይበል፤
ሐውልት ቆመላቸው።
“ዕውነት አትሞትም፣”
ሲባል ካልሰማነው፤
የ”መስቀልን”በዓል፣
ምንኑስ አወቅነው።
ሰው ግን በችቦው ዕለት እየተምታታበት፤
የኢትዮጵያን”ዕውነት”ይረሳል ባለበት።
ታሪኩን ለምናውቅ ትውልዱ ያደለን፤
በዓለምላይ የሌለ መረጃውም አለን።
አጶሮጊዮን ሲባል ከጥንት ሹመታቸው፤
የኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ናቸው።
ይብላኝ እየጠሉ ለተበቀሏቸው፤
በእግዜር ሥራ ገብተው፤
በግፍ ለገደሏቸው።
አዎን አጥፍተዋል በትረ-ሥልጣን ይዘው፤
ግና እንዲገደሉ ማነው ያኔ ያዘዘው?
“በቀል የኔ ነው”ሲል እግዚአብሔር ሲናገር፤
“ደግሞ የምን ሐውልት!”ማነው ብሎ የነበር?
ወቸገል ዜናዊ አይደለም ወይ ያለው፤
ዛሬም በምድራችን
ሥሙ የሚቃጠለው።
ገና በእርሱ ተንኮል በፈፀመው የግፍ ጦስ፤
ይፈርሳል ሐውልቱ የዚያ አባ ጳውሎስ።
የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ወስኗል አይቀርም፤
ዕውነት እንደሆነች ተቀብራ አይቀርም።
የኃይለ ሥላሴ ገና መቼ ወጣ ሐቁ ባደባባይ፤
የግድብ ሕልማቸው እንዲያ ሲጀመር በአባይ፤
ጦርነት እየጫሩ ለመንግሥት ግልበጣ፤
በባንዳ ሽፍትነት ኢትዮጵያን
ሊወጓት ስንቱ ጀሌ ወጣ።
እናም ነፃ አውጪ በሚል ሽፋናቸው፤
ባደባባይ ታየ ያ ማንነታቸው።
ዛሬም ፀንተን እንቁም እኛ ዕድለኞች፤
ኢትዮጵያ አትፈርስም
ልብ ግዙ ሞኞች።
እንደው ሆዱ ንፁህ፣የእኔ የሚል ከናንተ፤
ሠገራ የሌለው አንጀቱ ያልበከተ።
ማንም ሰው አይኖርም ጥፋት የማይሰራ፤
ግና ዓይነት አለው እንደሰው የሚያራራ።
በኛው ዘመን ሆኖ ሲፈፀም አይተናል፤
እንኳንስ ሊደረግ መስማት ዘግንኖናል።
እናም ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገስት ናቸው፤
በ{መለስ/ወቸገል}መቃብር
ሐውልት የቆመላቸው።