October 26, 2018
3 mins read

በአዲስ አበባ በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ 15 ተማሪዎች ራሳቸውን ስተው ወደቁ

በአዲስ አበባ በሚገኘው ማጂክ ካርፔት ትምህርት ቤት ውስጥ በትላንትናው እለት 15 ተማሪዎች ራሳቸውን ስተው ወደቁ፡፡
ራሳቸውን የሳቱት የጓደኛቸውን ሞት በድንገት በመስማታቸው ምክንያት እንደነበር ትምህርት ቤቱ ተናግሯል።
በትምህርት ቤቱ የ10ኛ ክፍል ተማሪ የነበረ ወጣት ከትናንትና በስቲያ ባልታወቀ ሁኔታ በክፍል ውስጥ እንዳለ በጓደኛው ትከሻ ላይ መዝለፍለፉንለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የገለጹት ርዕሰ መምህሩ አቶ ወንድሙ እሸቱ አቶ ወንድሙ፤ በወቅቱም ከትምህርት ቤቱ አጠገብ በሚገኝ ጤና ጣቢያ ተወስዶ ህክምና ቢደረግለትም የልብ ምቱ በፍጥነት በመቆሙ ህይወቱ ማለፉን ተናግረዋል። የአሟሟት ሁኔታውን ለመረዳት እንዲቻልም የአስክሬን ምርመራ ተደርጎ ውጤቱ እየተጠበቀ መሆኑን አስረድተዋል።
እንደ አቶ ወንድሙ ገለጻ፤ በትምህርት ቤቱ የተገኙ ተማሪዎች ትላንትና የጓደኛቸውን ህልፈት ሲረዱ በግቢው ውስጥ ኀዘናቸውን በመግለጽ ላይ እያሉ የተደናገጡ ከሰባተኛ እስከ አስረኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች እራሳቸውን ስተው ወድቀዋል። በወቅቱ ግን በመገናኛ ብዙኃን ተማሪዎች እና መምህራን ጸብ ፈጥረው ጉዳት መድረሱን የሚገልጽ የተሳሳተ መረጃ በመተላለፉ ወላጆች ተደናግጠው ትምህርት ቤቱን አጨናንቀውት ነበር።
በትምህርት ቤቱ አጠገብ የሚገኘው የወረዳ ስምንት ጨፌ ጤና ጣቢያ ጤና መኮንን ሒሩት ተክለጻዲቅ እንደገለጹት፤ በተወሰነ መልኩ እራሳቸውን የሳቱ (ሰሚ ኮንሺየስ) ሆነው ወደ ጤና ጣቢያው የመጡ 15 የሚደርሱ ተማሪዎች ህክምና አግኝተው ተመልሰዋል። ‹‹በተማሪው ሞት ምክንያት እንግዳ የሆነ ነገር የተፈጠረባቸው በመሆኑ አሳሳቢ የህክምና ችግር አልታየባቸውም። በወቅቱም ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቢያጋጥም በሚል ሁለት አምቡላንሶች ዝግጁ ሆነው ነበር።›› ብለዋል የጤና መኮንኗ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=nwAe0H54xdQ

92150
Previous Story

ዶ/ር አብይ አህመድ የጋምቤላን ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው መስራታቸው የሚያስመሰግን ቢሆንም ሕወሓት ካሴረው የግንጠላ ሴራ ክልሉን እንዲጠብቁ ማሳሰቢያ ተሰጣቸው

92273
Next Story

ዶ/ር አብይ አህመድ “ኢትዮጵያ ማንም ትነስቶ እንደግል ቂጣ እንደፈለገው ጠፍጥፎ የሚጋግራት አይደለችም” አሉ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop