ለተስፋዬ ገ/አብና ለግንቦት ሰባት እንዲሁም ለኢሳት የሚያስጨንቀኝን ልጠይቅ

ግርማ በላይ – ኢትዮጵያ ፤ አዲስ አበባ (gb5214@gmail.com)

 

አውቃለሁ – ይህ አጭር ደብዳቤየ ደርሶት የማያስተናግደኝ ድረ-ገፅ ሞልቷል፡፡ እናም ከልቤ እንዲህ እላለሁ – ሆን ብሎ በትዕቢትም ይሁን በዕብሪት ወይም በሌላ ማንኛውም ምክንያት ይህን ጭንቀቴን መረዳት የማይፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ ሁሉ ጥቁር ውሻ ይውለድ፡፡ እምራገመው ከአንጀቴ ነው፡፡ በአሁኒቷ ቅጽት ማለትም በአቤቶኪቻው ድረገፅ አነሳሽነት የዚህን የተረገመ ሰውዬ ጽሑፍ ካነበብኩ በኋላ ስሜቴን መቆጣጠር ባቃተኝ ደረጃ ተናድጃለሁ፡፡ ይህን ጭንቀቴን ተረድቶ ሊያስታምመኝ የማይፈልግ ወገን – ማንም ይሁን ማን – የእምዬ ኢትዮጵያ አምላክ ከጊዜ መዝገብ በአጭርነቱ በሚታወቅ ቅጽበት ውስጥ የዶጋ ዐመድ ያድርገው – በቃ፡፡ ተስፋ ስትቆርጥ አይደለም መራገምና መሳደብ  ያገኘኸውን ነገር አንስተህ በመወርወር በእጅህ ሰው ታጠፋለህ፡፡ የዚህ ነቀርሣ ሰውዬ መርዝ ማርከሻ ካልተገኘ በጣም አደገኛ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል የምንረዳ ሰዎች በአሁኑ ወቅት እንይዘውንና እንጨብጠውን አጥተን የታሪክንና የፈጣሪን ፍርድ ብቻ በከፍተኛ ጉጉት መጠባበቅ ላይ ነን፡፡

ከአሣታሚው ድርጅት ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት ብዙ ገንዘብ እንደሚያገኝበት የጠበቀውን መጽሐፍ ክፍያውን እኛ በዓይነት እንድንከፍልለት ወስኖ በነጻ አድሎናል – ያ የዓይነት ክፍያም የኢትዮጵያውያን በተለይም የአማራና የኦሮሞ እርስ በርስ መጨራረስ ነው – ቸሩ መድሓኔዓለም ይህን የመከራ ድግስ ለራሱና ለመሰሎቹ ያዙርለት፡፡ መርዝ በነጻ ታደለ፤ እኛም ያገኘን መስሎን ተገኘን! ርህራሄ በሌለው ዱላም ተስፋዬ ለመቶኛ ጊዜ ይዠልጠን ገባ፡፡ ተባባሪዎችን እስካገኘ ድረስ ደግሞ እሱ ምን ቆርጦት ገና ብዙ ያዳክረናል፡፡ ከሚያገኘው ገንዘብ ይልቅ የተስፋዬ ቅርሻት በሕዝቡ ዘንድ የሚፈጥረው ግማትና ቀጣዩ ሁከት በልጦበት በነጻ አሰራጨው – የኛ altruist የ”ኪነ ጥበብ ሰው”፡፡

እንደሚታወቀው ይህ የሰባት አጋንንት ውላጅ ገብረ ዲያብሎስ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተ አይመስለኝም፤ በተፈጥሮውም ከነሂትለርና ሙሶሊኒ የከፋ አረመኔ እንጂ ለሰው አዛኝና ሩህሩህ አይደለም፤ ከመያዶች(NGOs) ድጎማ ስለመሰጠቱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ የኤርትራ መንግሥት ወጪውን ሸፍኖለትም ከሆነ አላውቅም፡፡ ስለዚህ ይህን ብዙ የደከመበትን አርቲ ቡርቲ በነጻ በድረገፅ መልቀቁ ከመነሻው የእልህና ኢትዮጵያን የማውደም ዓላማ አንግቦ እንጂ ለደግ ተግባር እንዳልሆነ መታወቅ ነበረበት፡፡ ቄንጥ እየመሰለን ብዙዎቻችን በምንሠራው አጉል ሥራ ይህን ሰውዬ የልብ ልብ እዬሰጠን በላያችን ላይ እንዲጸዳዳ እያደረግነው ነው ፡፡(ደግሞም “የሥነ ጽሑፍ አድባር የወረደችለት ዘመናዊ ደራሲ” እየተባለ ይሞካሽልኛል፡፡ የቱ ነው የተስፋዬ ሥነ ጽሑፍ? ሥነ ጽሑፍን ከአርቲ ቡርቲ የመንደር ወሬ መለየት የሚችል ሰው ከናካቴው ጠፋ ማለት ነው? እንዲያ ከሆነ አሳሳቢ ነው! ለምሳሌ የዚህ የ‹ስደተኛው ማስታወሻ› የሚል ዝባዝንኬ ጽሑፍ ታሪኩ የታል? ሤራው የታል? ግጭቱ የታል?  ጭብጡ የታል? ጡዘት ልቀቱ የታል? ለመሆኑ ልቦለድና ኢ-ልቦለድ ምንድነው አንድነታቸውና ልዩነታቸው? ለምን በሥነ ጽሑፍ ይቀለዳል? ተስፋዬን በአዲስ ጃነር “ጸሓፌ-መስተፃልዕ ወጸላኤ ፍቅር” ብሎ መፈረጅ ይቻል እንደሆነ እንጂ ከጽሑፎቹ የአማርኛ ሥነ ጽሑፋዊ ውበት ውጪ የተዋጣለት ደራሲ የሚል ቅጥያ ትከሻውን ያጎብጥበታልና ይቅርበት – ‹ባናርስ አጣምደናል› እባክህን!) በነጻ የለቀቀውን መርዝ በነጻነት እየተጎነጨን ልናብድ የደረስን ዜጎች ሞልተናልና የሚመለከታችሁ ወገኖች የእሪታ ድምጻችንን ስሙልን ፤ አሰሙልንም፡፡ እምቢ ብትሉ አሁንም ዕጣ-ፋንታችሁ የተስፋዬ እንዲሆን ከመጸለይ ውጪ ለጊዜው ምንም የምንለው ነገር የለም፡፡ ከአዲሱ የተስፋዬ መጽሐፍ ገጽ 89 ላይ የሚከተለውን ተመልከቱ፡፡ እያንዳንዷን ዐረፍተ ነገር ልብ ብላችሁ አስቧት፡፡ ልክ እንደቡርቃ ዝምታ መጽሀፉ ሆን ብሎና በዕቅድ አማራንና ኦሮሞን ለማጋጨት ያጠነጠነው የተንኮል ክር ነው፡፡ ይህ ጽሑፍ ከአርባና አምሳ ዓመታት በፊት ቢጻፍ ምናልባት ትርጉም ሊኖረው ይችል ነበር – አስተማሪነትም ላይጠፋበት ይችላል – አንዳንድ ደናቁርት አማሮችም አልነበሩም አይባልምና፡፡ አሁን ግን ላም ባልዋለበት ግጭት ለቀማ ካልሆነ ኩበት የለም፡፡ (ይህ የመጽሐፉ ክፍል የመጽሐፉ አንኳር ተልእኮ የሚተላለፍበት ዋና ቁም-ነገሩ ነው – ለተስፋዬ፡፡ የተቀረው ባብዛኛው ለዚህ በ‹ማን አባት ገደል ገባ› የልጆች ጨዋታ ዓይነት የማጣያ ድግምታዊ አንደርብ እንደመናጆ የሚውል ነው፡፡)

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች | ከክንፉ አሰፋ

 

ክፍላቸው ውስጥ ቶለሳ መገርሳ የሚባል ተማሪ ነበር። ስሙ በመምህሩ ሲጠራ ወይም እሱ ስሙን ሲናገር ተማሪዎቹ ይስቃሉ። ተማሪዎቹ በሳቁ ቁጥር ጫልቱ ኪሎዋ ይቀንሳል። ሄለን አለመሆኗ፣ ጫልቱ ሚደቅሳ መሆኗ የሚታወቅ እየመሰላት ላብ ያጠምቃታል። ቶለሳ በተመሳሳይ ሲሰቃይ ታየዋለች። ራቁቱን የሆነ ያህል እጁን የሚያስቀምጥበት ቦታ ይቸግረዋል። ጫልቱ አንድም ቀን ግን አዋርታው አታውቅም። በአጋጣሚ እንኳ ሲጠጋጉ ፈጥና ዘወር ትላለች። በስሙና በአማርኛው ቶለሳ ላይ ሲሳቅበት አብራ ስቃ አታውቅም። አቀርቅራ ዝም ትላለች። በተመሳሳይ ኤልሳ አበበ ጫላ የምትባል ሌላ ተማሪ ነበረች። አዲስ አበባ የተወለደች ናት። አማርኛዋ ችግር አልነበረበትም። ንቅሳትም የለባትም። የአያቷ ስም ጫላ በመሆኑ ብቻ የቀልድ ኢላማ ሆና ነበር። ተማሪዎቹ “ጫላ” እያሉ ይጠሯታል። ይህም ጫልቱን በጣም አስደንቆአት ነበር። ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንደ ቢንቢ ይወሯታል…

……..

ርግጥ ነው፣ በሁለተኛ ቋንቋ ስሜትን መግለፅ ያስቸግራል።በመሆኑም ጫልቱ ይህን መሰል ችግር ውስጥ መግባቷ ግድ ነበር።የዘመድ መርዶ መጥቶ በተነገራቸው ጊዜ ይህ ችግር ገጥሞአታል። በኦሮምኛ ማልቀስ በመጀመሯ፣ ከሳሎኑ ተነጥላ ጓዳ ገብታ እንድታለቅስ ተደረገች። አክስቷ፣ “አኒበዴ” የሚለው ቃል በጓደኞቿ እና በጎረቤቶቿ ፊት እንዲሰማ ሳትፈልግ ቀረች።

 

አሁን ወደ ጥያቄዎቼ ልሂድ፡፡

 

  1. ተስፋዬ የተባልከው ሰይጣን አማራንና ኦሮሞን ለማበጣበጥ ቆርጠህ መነሳትህ ግልጽ ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ምን አነሳሳህ? ሀሰትም ይሁን እውነት ያለፈን መጥፎ ታሪክ አሁን ከተቀበረበት እያወሱ አንዱን በአንዱ ላይ በማነሳሳት ሊፈጠር በሚችል ጠብና ሁከት ምን ዓይነት እርካታስ ነው የምታገኝ? ከዚህ የተሻለ የምትሠራው ነገር አጥተህ ነው ወይንስ የተፈጥሮ ጥሪህ የጥፋትና የጥፋት ብቻ ሆኖብህ አንተም ተቸግረህ ነው? እንዲህ ከሆነ ለምን ሀኪም አታማክርም ወይም ክፍልና ኮከብህን አስቆጥረህ ወደጠበል አትሄድም?  ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚጠቀሙት አማራ ሲጠፋ ብቻ ነው ብለህ ለማመን የተገደድከው በምን አመክንዮ ይሆን? ብንፋቀር እንጠቀማለን ወይንስ ብንጣላ? ተለያይተን ሞከርነው – ውጤቱ አንተም እንደምታውቀው ነው – ዛሩ እንዳልሰከነለት ባለውቃቢ ከሀገር ሀገር የሚያንከራትትህና ዜግነትህን ሳይቀር እንደሸሚዝ የሚያለዋውጥህ፣ ትዳርም ይዘህ የተረጋጋ ማኅበረሰብኣዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት እንዳይኖርህ ያደረገኽ ይሄው የእናትና ልጅ በመሠሪዎች ተገነጣጥነው ለየብቻቸው መኖር ነው፡፡ ታዲያ ዛሬ በ21ኛ መቶ ክፍለ ዘመን የሥልጣኔና የሰው ልጅ ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ላይ የደረሰበት የግሎባላይዜሽን ዘመን ላይ ሆነህ እንደጥነቱ የመንደርተኝነትና ጠጎጠኝነት አስጠሊታ ዘመን ‹የአባት ሀገር፤ የእናት ሀገር› እያልክ የምትቀባዥረው ይህ አስከፊ ሁኔታ እስከዘላለሙ እንዲቀጥል ትፈልጋለህ ማለት ነው? ከጥፋት መንገድህ በአፋጣኝ የማትመለስ ከሆነ እግዚአብሔር በጀመረህ መንገድ ሲያንቀዠቅዥህ ይኑር – በአንተ ቤት ሁሉን ነገር ዐውቀህና ከሁለንተናዊነት ይልቅ ጎጠኝነቱ ይሻለኛል ብለህ ሞተሃል፡፡ ይታይህ – አንድ ሰው ተነስቶ – በቃ ከመሬት ተነስቶ ልበልህ –  “የኤርትራ ዜጎች ከምድረ ገፅ ካልጠፉ መካከለኛው ምሥራቅም ሆነ የአፍሪካ ቀንድ ሰላም አያገኙም!” ቢልና ኤርትራ እንደኢራን በማዕቀብ ተወጥራ ልትፈነዳ ብትደርስ ወይም ኤርትራ እንደሦርያ የጦር ዐውድማ ብትሆን ትደሰታለህ ወይ? ይከፋሃል፤ ታለቅሳለህም – አውቃለሁ፡፡ አንተ የዲያብሎስ ውላጅ ሽል መንጣሪ ነህ፡፡ የበላህበትንም ወጪት የምትሰብር፣ የጠጣህበትንም ዋንጫ ወደገደል የምትወረውር ልዩ ፍጡር ነህ፡፡ ዋጋህን እግዜር ይክፈልህ፡፡ አንተ በኤርትራ መጎሰቆልና የጥቃት ዒላማ ውስጥ መግባት ከተከፋህና ካዘንህ ለእኛ ለምሥኪን ኢትዮጵያውያንስ ዕልቂት ለምን ትደግስልናለህ? አንተም ሆንክ አባትህ ሻዕቢያና አጎትህ ወያኔ እስካሁን የምታሰቃዩን አነሰን ወይ? እምነትህ ዋቄፈታ መሆኑንና የእሬቻ ባህላዊ ወግና ልማድ ደጋፊ መሆንክን በአዲሱ ጽሑፍህ በቀጥታም ባይሆን በተዛዋሪ ነግረኸናል፡፡ ስለዚህ ሃይማኖትህን አልጠይቅም፡፡ እንደኔ ግምት ግን ኤቲይስት መሆን አለብህ፡፡ ምክንያቱም በእሬቻም ሆነ በተለያዩ ሰማያዊም ይሁኑ ምድራዊ አማልክት የሚያምኑ ሰዎች እንዳንተ ጨካኝ አይደሉም፤ ምንም ይሁን ምን ሃይማኖት ያለው አንድ ሰው ያንተን ያህል ቀርቶ የሩብ እሩብህንም ያህል እንኳን በሰዎች ስቃይ አይደሰትም፡፡ብዙ የደጋግ መርህ ሰዎች የሆኑ ኤቲይስት ጓደኞች አሉኝ፡፡ አንተ ግን እንዲያውም ሴቴኒስት ሳትሆን አትቀርም፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ:  ኹራፋተ አምሳሉ ፡- መረጃና ማስረጃ አልባው እንቶፈንቶİ - ዲ/ን ዶክተር መሐሪ ወሰን /ከጅማ/

ስለዚህ አንተ ወይም አንተን በተልእኮ አስፈጻሚነት የላከ አካል ችግር አለባችሁ ማለት ነው፡፡ ያ ችግር የሚፈታው           ደግሞ እናንተ ስትጠፉ ወይም አስተሳሰባችሁን ስትቀይሩ ነው፡፡ በመሠረቱ ሰውን ‘በማጥፋት ለውጥ ስለማይመጣ           የአመለካከታችሁን መለወጥ ለብዙ ጊዜ ስንጠብቀው የነበረ ጉዳይ ነው – ግን አልተሳካልንም፡፡ የነገውን አላውቅም፡፡

 

  1. ግንቦት ሰባት ከዚህ ሰውዬ ምን አላችሁ? ከዚህ ሰውዬ ጋር አብራችሁ እየሠራችሁ ከሆነ ፈጣሪ “የልጅነት ጊዜያችሁን አያስጨርሳችሁ” ብዬ እንዳልረግማችሁ በውነት ለምን እንደሆነ … አይ … ንዴቴ ከመነሻው አሁን በረድ ስላለልኝ ይቅርብኝ፤ በአንድ ተስፋዬ ሳቢያ የብዙዎችን ቀና ልፋት ማጠየም ያለብኝ አይመስለኝምና እርግማኔን ለሌላ ጊዜ አስተላለፍኩት ፡፡ ጅምሩ ያላማረ መጨረሻውም አያምርምና ከዚህ ከሰይጣን ሰውዬ ለኢትዮጵያ ነጻነት የሚመጣ ነገር ባፍንጫችን ይውጣ፡፡ ይህ ሰው መጠቀሚያ እያደረጋችሁ እንደሆነ መገመት ይቻላል – ባለፈው የሰጠውን አንድ ቃለ ምልልስ ወደጽሑፍ ተገልብጦ ዘሀበሻ ድረገፅ ላይ  አንብቤያለሁ፡፡ ወደሰውነት የሚገባና ከሰውነት የሚወጣ አንድ አይደሉም፡፡ ለምንም ዓይነት ሥልት ይሁን ተስፋዬ ያለበት የነጻነት ትግል ለኢትዮጵያ ቀርቶ ለማንም አይጠቅምምና ግንቦት ሰባት ከዚህ ሰውዬ ጋር ግንኙነት ካለው ቁርጡን ነግሮን  እሱን አንጋጠን መጠበቃችንን እናቁም ዘንድ ይርዳን፤ ይህም ብቻም አይደለም ተስፋዬ ያለበትን ስብስብ ሕዝብ እንዲረዳውና የራሱን መውጫ ቀዳዳ እንዲያፈላልግ የበኩላችንን ጥረት እናድርግ – ሞኝነት ለእንዶድም አልበጃትምና ከዚህ አኳያ ሁሉም ይነጋገርበት፤ ይወቃቀስበት፤ መፍትሔም ይፈልግበት፡፡ ትግሉ ፈር እየያዘ የሚሄደው ጠላትንና ወዳጅን ለይቶ ከማወቅ ሲጀመር ነው፡፡ አማራን ለማስጨረስ ቆርጦ ከተነሣ ሰው ጋር ተባብሮ አማራንም ሆነ ሌላውን ወደሌላ የጭቆና አዙሪት ለመክተት ካልሆነ በስተቀር ለነጻነት የሚደረግ ትግል የለም፡፡ ስለዚህ ግንቦት ሰባትና ይህ ሰው ያላቸውን ግንኙነት አስረዱን – በኢትዮጵያ አምላክ እንለምናለን፡፡ እንዴ? የሰው ጭንቀት አይገባችሁም?  ዝም ባለ አፍ ተስፋዬ ሲገባበት ማየት ለማንወድ ዜጎች የግንቦት ሰባትን አጭር መልስ እንፈልጋለን፡፡

 

  1. ኢሳት ስለዚህ ሰውዬ ተንፍሶ አያውቅም፤ አለመተንፈሱ መብቱ ነው – “ለምን”ን ማስከተሉንና ለዚያ ተገቢ “ለምን” በምን ምክንት መልስ እንደተነፈገ የማስረዳት ግዴታ ግን አለበት – ኢሳት፡፡ (‹ማንም እንደፈለገው ይጩህ እኛ ግን ሥራችንን በርትተን እንሠራለን› ማለቱም በመሠረተ ሃሳቡ ትክክል ሆኖ እንዳካሄድ ግን የተወሰነ ህፀፅ አለበት – ‹ግመሎቹ ይጓዛሉ -ውሾቹም ይጮኻሉ› ከሚለው ነባር የወያኔ አሠራር ለመሻል ከአነጋገር ጀምሮ መጠንቀቅ ይገባልና፡፡ ‹በየት ዞረሽ ቀደምሽኝ?› አልነበር ያሉት አለቃ ገ/ሃና እቤታቸው አስጠልቷቸው ጓደኛቸው ቤት ምሣ ሊበሉ ሲሄዱ ለቀረበላቸው ሽሮ ይሁን ጎመን?) ወያኔን ሰርክ የሚያወግዝ የሕዝብ እስትንፋስ ለምንድነው ይህ ሰውዬ ላይ ሲደርስ ብዕሩና አንደበቱ የሚልፈሰፈሰው? ምን ዓይነት ሥልት ነው? የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያውውን ታጣቂዎችን መርዳቱ እስከተገለጠና ተስፋ እንዳለም እስከተገለጠ ድረስ የዚህ ሰውዬ እኩይ ተግባር የኤርትራው መንግሥት ሃይ እንዲለው “ወንድሞች! ይህ ሰውዬኣቺሁ ጥረታችንን አመኔታ በማሳጣት እያጠየመው ነው፤ ለተወሰነ ጊዜ አደብ እንዲገዛ ይደረግልን፡፡ ታጥቦ ጭቃ ሊያደርገን ነው፡፡” ብሎ ማሳሰብ አይቻልም ነበር ወይ? የምን መደባበቅ ነው? የምንስ ዕንቆቅልሽ ነው?ተስፋዬ እግዜር መሆኑ ነው እንዴ? ‹ስንት ሰዓት ነው እንዴ?› ይለኛል አንድ ትግሬ ጓደኛየ፡፡ ያልገባኝ ብዙ ነገር አለ፤ አውቃለሁ፡፡ ተስፋዬ በኢሳት እንዲፏልል መድረክ ያልተሰጠውን ያህል –  ይህን ያህል ስለእርሱ መጥፎ ዕቅድ አንዳችም ያለመወራቱ ምክንያት ግን ላውቅ ይገባኛል፤ ከመብቶቼ ትንሹ ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ:  በቅሎ ገመዱን በጠሰ ሲባል እንጀራው አሳጠረ ይባላል - ታጠቅ መ.ዙርጋ

 

  1. በመጨረሻም ከዚህ ሰውዬ ጋር – በኢትዮጵያ የኤርትራ ጉዳይ አስፈጻሚና በኢትዮጵያ የናዚ ኦሽትዊዝ ኢንደፈጠር ሌት ከቀን ከሚጥር ከዚህ በላኤሰብዕ ጋር ወግናችሁ የምትገኙ ወገኖች ሁሉ በቶሎ ከዚህ እርኩስ መንፈስ ካልተለያችሁ እናንተም ጥቁር ውሻ ውለዱ፡፡ ለየትኛውም የትግል ሥልት ይሁን ከዚህ ሰው ጋር ለኢትዮጵያ ብሎ የሚሠራ የተረገመ ይሁን፡፡ ሰይጣን የትኛውንም ሀገር ነጻ አውጥቶና ከጭቆናና ከመሪር አገዛዝ አላቅቆ አያውቅም፡፡ መጽሐፉን አንብቡና ተለዩት – በቃ፡፡ “በቃ!” ለተስፋዬ ሲሆን መስነፍ የለበትም – ገኣስ! የአክልና ተስፋዬ! ከአሁን በኋላ በተስፋዬ ፍቅር እንደተነደፈ የሚጸና ቢኖር እርሱ የኢትዮጵያ “ሕዝቦች” ቀንደኛ ጠላት ነው፡፡ ክፋትን ለማውገዝ በግድ ክህነት እንዲኖረን አይጠበቅብንም፡፡

 

  1. በሕዝብ ዘንድ ታዋቂነትና ሕዝባዊነትን ያተረፋችሁና እያተረፋችሁ የምትገኙ ዜጎች – እነታማኝ በየነ፣ እነገብረ መድህን አርአያ፣ እነአበበ ገላውና በለው፣ እነብርሃኑ ዳምጤ፣ እነእንትናና እነእንቶኔ ሁሉ — ስንቱ ተዘርዝሮ —- ብቻ ሁሉም የታወቀም ያልታወቀም ኢትዮጵያዊ ሁሉ የዚህን ሰው ብልግናና መሠሪ ተንኮል እያወቃችሁ በሆነ ምክንያት የማታጋልጡ ከሆነ እናንተም ሀገራችን ሁለንተናዊ ችግሮች እየተባባሰ መሄድ (ዐውቃችሁም ሆነ ሳታውቁ – ምናልባትም ሳታውቁና በ‹ትግስት›ም) ቢያንስ ከኔ በበለጠ አስተዋፅዖ እያደረጋችሁ ነውና እግዚአብሔር የሚገባችሁን ፍርድ አይንሳችሁ፡፡ ለሀገር ሲባል ልጭና አፍሮ የለም፡፡ ለሀገር ሲባል ጥሬና ብስል የለም፡፡ ትግል በተፈጥሮው መራራ ነው፡፡ እውነት በተፈጥሮዋ መራራ ናት፡፡ አንድ ነገር ለማግኘት ብለህ አንድ እንዲኖርህ የማትፈልገው ነገር እንዲኖርህ ከፈለግህ ምንም ነገር እንዳይኖርህ ብትሆን ይሻላል ( ቀላል ምሳሌ፤ -5+5= 0)፡፡ መጽሐፉ -“ቀኝ ዐይንህ ብታስትህ ካንተ አውልቀህ ጣላት፤ ከሁለት ዐይኖችህ ጋር ወደሲዖል ከምትወርድ አንድ ዐይና ሆነህ ወደገነት ብትገባ ይሻልሃል፡፡” ይላል፡፡ ከተስፋዬ ጋር አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ለመግባት የሚመኝ ቢኖር ካለተስፋዬ በለመደው ባርነት ቢኖር ይቀለዋል፡፡ አንድ ሞትና ዘጠኝ ሞት ያው ነው – ይህ የኔ እውነት፣ ውሸት መሆኑን የሚያስረዳኝ ሰው ባገኝ ግን እጅግ ደስ ይለኛል፡፡ ፈራሁ…. በጣም ያስፈራል፡፡ ነገሩ እንዲህ አስፈሪ ከሆነ ዘንዳ አዋጪ አማራጭ መፈለግ ሊኖርብን ነው፡፡ ሰውን እንደትንኝና እንደትቢያ ከምትቆጥሩ ወገኖች ምንም አልጠብቅም፡፡ የአንድ ዜጋችን ጭንቀት የኛም ጭንቀት ነው ከምትሉ ወገኖቼ ግን ብዙ አጽናኝ ቃላትን በጉጉት እጠብቃለሁ፡፡ በውነቱ ተስፋዬ ብዙ አስደንግጦኛል – ተወን ስል እንደአዲስ በመጀመሩ ፈራሁ፡፡

 

ልጨርስ ነው፡፡ ከአንዲት አክስቴ እውነተኛ ግለ-ታሪክ እንማር፡፡ አንዲት የጎረቤት ሴት ወደቤቷ ትመጣለች፡፡ አክስቴ ደግና የዋህ ነበረች፡፡ ብረት ምጣዷን ጎተት ታደርግና ቡና ልታፈላላት መንደፋደፍ ትይዛለች፡፡ እሳቱ እስኪጋጋምና ቡናው እስኪቆላም ከማጀቱ ሞሰብ እንጀራ ዘንጠፍ አድርጋ በሌማት ላይ አድርጋ ታቀርባለች – ጊዜው እንዳሁኑ ሙትቻ አልነበረም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ እንደዳቦ የሚገመጥ እርጎ ከላጋው አውጥታ አዋዜ እላዩ ላይ ጣል ታደርግበትና እንድትበላ ፈገግታ በተሞላበት ፊቷ ትጋብዛታለች፡፡ የሃሜት ሱሰኛ የነበረችው ያቺ ሴት እጇን ወደቀረበው ማዕድ ከመሰንዘሯ ጎን ለጎን፣ “አይ ወ/ሮ እገሊት፣ አንቺስ ጥሩ ሚስት ነበርሽ፤ ባልሽ ግን …” ብላ የነገር ኮረጆዋን ከፍታ የሃሜት ጥይት እሩምታዋን ለማስወንጨፍ ከመጀመሯ ቆፍጣናዋ አክስቴ ወደማዕዱ የተዘረጋውን የዚች ሴትዮ እጅ በንዴት እየከላች “አንቺ ሆድሽን በኔ እርጎ ልታርሽ፣ እኔ ባንቺ ሃሜት አንጀቴን ልበጥስ፤ እ… ? ይሄማ በጭራሽ አይደረግም! በይ ውጪልኝ አንቺ ሾካካ፤ የማን ናት አጓምዳ በዝጊሃር!” ብላ ቀልቧን ገፍፋ አስወጣቻት፡፡ አዎ፣ እኛም እነተስፋዬን እንደዚህች ሴት ነው ቆሌያቸውን እዬገፈፍን በመካከላችን እንደወተት ዝምብ ጥልቅ እያሉ እንዳያውኩን መጠንቀቅ ያለብን፡፡

25 Comments

  1. Betam yigermal, endante ayinet sewuch eyalu min selam yinoral. Ke amhara gar yimiyatalan yesfaye yetsafewu ewuneta sayihon endante ayinetu tena yegodelewu sew yemitsifew endezih yale atseyafi tsuhuf new. Shame on you the habasha to post such a trash article! How come that you publish such article which is full of insult? I will stop visiting your site at.

    Shame!

    • This is a piece of writing from a person who has gone completely controlled by a deadly rage. yes, it is absolutely anybody’s right to have her or his say . But, this kind of full of highly inflammable that is not helpful at all! If you are really and genuinely concerned , try to make your point and argument something is substantiated and come up with a solution how to deal with the problem . The more you behave and act that way, the more you lose your rational and desirable way of dealing with things you want to. I think we need to mitigate ,if not control this kind of inflammable rage . I am afraid that if we allow ourselves to be victims of this type extremely crazy emotion, the rage will kill us before tackle the problem we want to deal with show any sense of change.

  2. Amharas are missing the point. Tesfaye is not creating a non-existent history. He is only exposing the known stuff, but from a differnt perspective. He is a non-Oromo and he has credibility. The Oromo people’s exposition of the truth have always been treated as creations, false or poltically motivated. Added up with the mob activity of Ethiopianists, it created a cloud of uncertainity. Tesfaye is not an Oromo, but an Ethiopian who dared to publish already known historical facts. What is sad in this issue is the arrogance of the vast majority of Amhara elits and their mob mentality to underestimate the grievance of the oromo people. Books after books have been written but they did not want to listen. Oromos have by in alrge ignored the Amhara elites and are going their own way in shaping the future of Oromia. On the other hand Amharas sing to each others song with out even noticing the moving of the giant earth quake. They sing to each other and believe that they are still the shapers and decision makers of the Oromo people. They thought that Tesfaye is creating a problem. The fact is they do not know what is brewing. Leave Tesfaye alone. They talk of Tesfaye having an Eritrean passport. How many of them have foreign passports? Most of the present leaders of Ethiopia were on Somalia passports even after Somalia waged war on Ethiopia. Stop deluding yourselves.

  3. Bro the insult happened just last year at the University of Addis Abeba. Unless you are from another planet, insulting, belittling and Oromo is a common practice in Ethiopia. I think it came from the point that Oromo lost the independent struggle. Winners always brag. Nobody respect a looser. This time at the University it was not Amhara but Tigre are the one insulting and abusing an Oromo. We learned it and we will give a collective answer to that.

  4. sidebu eregemanuna sidebu bayebeza.. teyakew melekam new egnam .. keteteyekut akalat.. aseteyayetachewen enetebekalen…

  5. wondemi yemisemahe benor teru neber negeru betam asazay new Woyanina Shahabiya eskemeche sichawtuben endminoru alawkem. Esat hone Genbot 7 Woyanina Shabiya ande mhonachewen eskahun yalewku kentuwoche nachew nageru keled naw yehiw sewye Tesfay teleku ye Genbot 7 amakari new. becha enam endantew eytekatelku yalehu Ethiopyawye wodemhe nagne. betam betam yemiyaszen deram new be Ethiopia lay eyetesra yalew.

  6. ሃይሉ: ተሃፍዉና ዱረገቱ ምንአደረጉ? የራስህን ሃሳብ እንዶማተት ለምን ሌላ አንጃገራንጃ ውስት ትገባለህ? ተስፋየ ማለትኮ አንደሚባለዉ ከእባብም የበለተመረዘኛና ተንኮለና ነው:: አሁን ለዚህ ህዝብ የሚያባላ ሰው ይታዘናል? ትገርማለህ:: ወይ ሰዉ ከንቱ አሉ እማማ ዘርፌ:: ለነገሩ ዘሀበሻን ባታነብ ይሻልሃል: ለእነዳንተ ያለ የወያኔ አሽቃባች አትሆንም:

  7. አላዛኝ ዉሾች ሆይ! እናንተ ማላዘናችሁን ቀጥሉ:: ብትዘላብዱም እነሆ ለመቅበር የሞከራችሁት መጽሃፍ በፒዲኤፍ በነጻ ደርሶናል:: ፈጣሪ ለብልሁ ተስፋዬ ዕድሜና ጸጋውን በላይ በላዩ ይጨምርለት:: “ዉሾች ይጮሃሉ ግመሎች ጉዞ አቸውን ቀጥለዋል” ነው ነገሩ:: ተስፍሽ ተባረክ!!!

  8. Ye Ethiopian Hezebe EnQwan ando tesefaya teklala betewoch LELEYAYOUIT AYCHELUM segat yemasketl kefu serawochin makalelay sayehone Hezbuwochwa bebezu mekerana sekay YETFETENU werkochenachewna Nekew yetewtal. Bezhe LAY degemo EGZEABHER Betebebu yasetedaderatal.belo masebu yetshale yemseleghal..Telatenetoin Sayerasuu Meftehayewen weyem Yemrzuin marekesha mefelgulay Matekor yeshalale.

  9. Hi girma belay don’t worry we will find out the truth! any way thanks for your information you have given us ok!

  10. I find the understanding of many on the Tesfaye issue these days bizarre. I guess many people are not only disoriented but totally lost from the core theme. Tesfaye is writing a story based on his childhood experience about 30+ years ago. This was the same when I grew up. There was my classmate named Fikerte Madessa and our amhara teacher ridiculed her multiple times when many students laughed. The teacher made fun of her because of her name, which was from her tribe a proud Oromo but we the kids laughed at his jokes no matter who he disciplined or penalized. Though I am not certain, I don’t believe she understood it then as tribal conflict. What Tesfaye wrote happened multiple times and dozens and dozens have been offended and it brought us to the status quo. Our oromo brothers don’t want to be humiliated but rather get respect from other tribes and the feudalism opinion of Amhara has to be trimmed. Whenever Tesfaye writes his views, we cannot shout against him and make scene out of it.

    Let all of us get more wisdom and work on reconcilliation. To my knowledge noone has the right to take or give the responsibility of apology from this generation. But we have to work in the right direction admitting mistakes and not just ignoring facts that happened. When expansion policies of Atse Minilik humiliated the Oromos, this was the rule of the day where the powerful defeated the powerless. But no more should we continue this attitude of denial. We should accept by learning like South Africans.

    • This is what many people failed to understand. Nothing is new about Chaltu/Helen
      1. It is a very clear fact that any one regardless of his ethinicity used to be humiliated by those who speak amharic well (Amhara elites).

      2.Not only oromo but also people from south (wolayita, sidama) and even from north e.g. tigre suffered from disrespect and discrimination because of the fact that they do not speak amharic.

      3. I even remember, the native amharas, from the countryside have been humilited as ‘getere’ becuase they do not speak modern amharic.

      4.After all many of the comedian, still now, they are making most of their jokes based on people who do not speak amharic well.

      So let us stay calm, admit the reality and work on reconciliation. I also think no one is from the young generation is responsible for what happened in the past.

      • This is the truth, the conflict is between keteme and getere. But when it comes to Shabia and woyane through tesfaye it is oriented to Amhara and Oromo. It is in every country where there are differences between modern ones and culturals. Let shabia and woyanne are cursed for their greed and evil racist attitude disintegrate ethiopia

  11. TESFAYE KOBRA has so many supporters here and some of the comments are written by TSFAYE KORIT TESFAYE is sick inside he is filled with hate and he has no sleep he thinks AMHARAS are eternal enemies of ERITEA so that he wanted them to be hated by every Ethiopians especially by OROMOS and OLFites did not get his intention because OLFites also have one and one dream that is killing and presecuting AMHARAS however the result will be the dream of TESFAYE eternal internal conflict and that is when OLFites will wake up.
    AMHARA PEOPLE WILL NOT LET OLFITES to slit their throat like BEDENO, ARsi ETC

  12. To all Ethiopian, do not listen those comments b/c they r WEYANE, SHABIA & OLF. Now we Ethiopian r smarter than those killer. They r like mad dog, b/c they have identities problem. It’s look like to take revenge on Ethiopians. So Tesfaye g/SHABIA is pushing that to happend in Ethiopia, but we r better than before in many ways if they tried Ethiopians will show them once for all

  13. I am Oromo and in my elementary school I had experied similar story about Chaltu in Tesfaye’s new book. I wonder when I see some people blame Tesfaye for writing about such stories by stating that it will develop hate between Oromo and Amhara and challege to Ethiopian unity. But the stories are facts and realities on the ground and almost all Oromos know them and they realise that the oppression and the harsment were due to the backward political system and not associated with poor Amharas who were under similar problems. For instance, I have many best friends from Amhara Tribe and we discuss about bad side of our history openly and we know that the current generation is not accoutable for that. For me “hiding” such realities which are already known by many and very past can’t help for the unity of Ethiopia, instead openlly discussing on them and on many other wrong doings in the past and their causes will clear out some misunderstandings with some people and help to build trust among various ethinic groups and it will, finally, result in national consensus and guarantee Ethiopian Unity. Hence, let discuse about the issues not about persons that raised them.

  14. Great point, Tesfaye Gebreab has to be exposed. He is the most evil person and the one who are working to divide Ethiopians. Addis Ababa is the capital city and many kind of people are living but most of them speak Amharic, it is impossible to say that all of them are Amharas because of the language. Shame on this evel mind Tesfaye Gebreab, he is Eritrean and working on deviding us.

  15. wether Tesfaye wrote’s it or not we know as amharas are enemies of oromo ppls.so don’t blame him.enakachihualen.yihe ye federalism gize newu.hizbachihun be rehab endalcheresachihu zare wede diro enimeles tilalachihu.yediro sirat nafak hula.we need areal democracy now.ke ahun bewhala enkuan egnan 1 to 5 yemibalewun ye weyane aderejajet atastedadirum be kililachin.manim ayisemachihum.zarem men madreg endalebin atingerun we know what we gonna to do.Tesfaye is our hero.ke enante tamagn ye 20 amet were ena limena yetesfayeone book hayil alewu.pls Tesfaye here we are for u.
    dont give ashit abt zes beggers.yenante tebasa enji ye mind chigr endelelebin 2005 e.c kesekelut ye university temariwoch megenzeb tichilalachihu.gin atayum atisemum “enakilachihualen bayoch”enkuan sefiwu ye oromo hizb 32,000 ye hizb bizat yalewu shinasha ayisemachihum.shut ur mouth bitche’s.degmo satafru Dr Mulatu teshome doctor yehonewu belimena newu tilalachihu tadiya enanten belimena man yistekakelachihual lemen leminachihu doctor atihunum…

  16. Ante ahun min eyesereah new? ke tedfaye bemin teshalih? hulachum andi nachu. Endiawm esu yishalal, be adebabay tekawumo wota, ye felegewin tsafe. Ante degimo eza tedebikeh ye gedel mamito honik.

    Betam yikirta, le ene gin hulachum andi nachihu

  17. Now it is time for ESAT TV to make a decision to side with the Ethiopian people by having a strong stand against the stupid tesfaye and his God father Shabiya ,enemies of the Ethiopia and its people!! Now you are at crossing roads!! don’t worry about the money that comes from Eritrea. The source from Asmara is not sustainable,don’t lose the diaspora Ethiopia !! hurry up no time start doing some thing against this spy of Eritrea.Even forget G7 because it only until they all go to Asmara.one all the leaders like Dr. Birhanu, Andargachew and others enter Eritrea ,then they will remain there for ever enjoying life in Asmara prisons

  18. For Ezu, ur moron, u don’t know what u talking about. Man I’ll tell u if u try anything in Emama Ethiopia, we Ethiopians finish u. The time is not like befor. We knows our enemy, there is no any tolerance for Yebetachenete besheta lalebet. We will die for Emama Ethiopia

Comments are closed.

Share