ዝሆን ላይ የሚጮህ እብድ ውሻ ብቻ ነው!! (ገብረመድህን አርአያ)

(ገብረመድህን አረአያ ከፐርዝ አውስትራሊያ)

የኢትዮጵያ ሕዝብ ከህፃናት እስክ አዋቂዎች (የወያኔው) ፡ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ማንነት ካወቁ ብዙ ዓመታት አስቆጥረዋል። ህወሓት ከየት መጣ፣ አላማውስ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎች የሕዝብ መነጋገሪያ ክሆነ አመታት ያስቆጠረ ነው ።የኢትዮጵያ ህዝብ ፤የኢትዮጵያን ሏላዊነት ደሙ አፍስሦ አጥንቱን ከስክሶ አንዲት ሏላዊት ኢትዮጵያ ያደረገ ህዝብ ፤በቋንቋ በሃይማኖት በዘር ያልተነጣጠለ ያልተከፋፈለ ህዝባዊ አንድነቱ ተፋቅሮ ተዋዶ በጋብቻ ተጋብቶ ፍቅርና ሰላም ገንብቶ ለስንት ሺህ ዘመናት ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ ኢትዮጵያዊነት ጠብቆ ፤የመጣ ኩሩ ህዝብ ኢትዮጵያዊ ነው ። የኢትዮጵያ ህዝብ ፤ አረንጓዴ፤ብጫ ፤ ቀይ ፤ ሰንደቅ ዓላማው ከስንት ሺህ ዘመናት ተረክቦ የማንነቱ መግለጫ አርማው ፤ተንከባክቦ ሲጠብቃት ጠብቆም ከትውልድ ወደ ትውልድ እያሸጋገር ሰንደቅ አላማችን የሃገርና የህዝብ ኩራት ደማቅ መለይታችን ኩራታችን በመሆን የተስፋችን ሂወት ሆና ኑራለች ።

የውጭ ባእዳን ጠላቶ ኢትዮጵያን በመውረር ግብጽ፤ሱዳን ፤ ጣልያን ሊብያ ወ.ዘ.ተ. በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ለማጥቃትና ለመውረር ያደረጉት ብዙ ሙኮራዎች በህዝብዋ አንድነትና አኩሪ ጀግንነት ኢትዮጵያዊ የመጡበት ጠላቶች ፊት ለፊት በጦር ሜዳ ተዋግቶ አሸንፎ ወራሪ ገድሎ ቀሪዉም ወደ መጣበት እንዲሸሽ በማድረግ የሚታወቅ የማይበገር ህዝብ ነው ።ኢትዮጵያ በባእዳን ጠላቶች አትደፈርም ብሎ ዘብ የቆመው የኢትዮጵያ ህዝብ በታሪክ ማህደር ውስጥ በጠላት የማትደፈር እትዮጵያ ፤በዓለም ውስጥ ቀዳሚው መእራፍ ይዛለች ።

ኢትዮጵያ ብዙ ጠላቶች አልዋት ፤በመሬቱ ተፈጥራዊ አቀማመጥም በጠላቶችዋ የተከበበች ናት ፤በሆንም ቅሉ ጠላቶችዋ የኢትዮጵያ ህዝብ ጀግንነት በጦር የማይቀለበስ ህዝብ ፤ወራሪ ጠላት ቢመጣበትም በአንድነቱ ተሰባስቦ ለጠላት እሾህ ተዋጊ ደፋር ህዝብ መሆኑም በሚገባ ስለሚያውቁ ፤እንደ ድሮው ሠራዊታቸው አስከትለው ኢትዮጵያን ወረው የኢትዮጵያን አንድነት ለማናጋት ፤ችሎታና አቅም እንደሌላቸው በመገንዘብ ፤ ከምዕራባውያን በተለይ እንግሊዝና አሜሪካ በመተባበር እነ ሱዳን፤ግብጽ፤ኢራቅ፤ሶሪያ፤ ጣልያን ፤ሊብያ ሶማሊያ ( መቃድሾ )ወ.ዘ.ተ. ተባብረው ፤ኢትዮጵያን የምናፈርሳት የምንበታትናት በራስዋ ዜጎች በቻ ነው ፤ይህም አስታጥቀን በተለያዩ ዘዴዎች እየደገፍን የብሄር ጥያቄ ፤ እስከ ነፃነት ጥያቄ የሚታገሉ መፍጠር ብቻ ነው ያለው ፖሊሳቸው አማራጭ ብለው ባወጡት እቅድ ፤ማ.ገ.ብ.ት =====ማሕበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ === የዚሁ ፍሬ ነው ።ለዚሁም የመጀመሪያ ተማራኪው አረጋዊ በርሄ ሲሆን ጋሻ ጃግሬው ግደይ ዘራጽዮን አስከትሎ ነው ።

 

ህወሓት የትጥቅ ትግሉን ከመጀመሩ በፊት ተዘጋጅቶ ወደ ትጥቅ ትግሉ የገባበት ምክንያት አሉት ። 1ኛው የኢትዮጵያን አንድነትና ሏላዊነት ለማፍረስ ብሎም ለመበታተን ነው ። 2ኛው ሕዝብዋ በቋንቋው ሃይማናትና ዘርን መእከል በማድረግ የኢትዮጵያን አንድነት በሚያዘጋጀው ፖሊሲ ለመከፋፈል ለመበታተን ከዚሁ መነሻ ህዝft ለእርስበርስ ጦርነት ኢትዮጵያዊ ህብረተሰብ እርስበራሱ እንዲተላለቅ አመቺ ነው ብሎ ስላመነበት 3ኛው   ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. የተነሳለት ዓላማ የኢትዮጵያን ሏላዊነት አንድነት ከፈረስ ህዝብዋም እርስበራሱ ወደ ማያባራው ጦርነትና መተላለቅ ከገባ ነፃ የሆነች ትግራይ የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ሪftብሊክ መንግስት ለመመስረት አመቺና ጥሩ ሁኔታ ይፈጥራልብሎ ስለሚያም ፤ 4ኛው የህ.ወ.ሓ.ት መስራችና አመራር በትልቁ በአቋም ደረጃ የያዙት ኢትዮጵያን ለመበታተን ህዝftን መከፋፈል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የ አማራው ህልውና በማያዳግም ሁኔታ መመታትና ከመሬት መጥፋትና መደምሰስ አለበት፤ ከዚሁም ጎን ለጎን የእትዮጵያ ተዋህዶ ከርስትናም ሆነ የአማራው ቋንቋ የሆነው አማርኛ አብሮ እንዲከስም መቻል ማድረግም አለብን፤ የእስልምና ሃማኖትም አብሮ እንዲጠፋ ማድረግ ። ይህን በተግባር ስንጀምረው ኢትዮጵያዊነት የሚለው የአማራው

 

ካባውም አብሮ ይከስማል ይጠፋል ።/ስለሆነም በፕሮግራሙ ቀዳሚ ምእራፍ በመስጠት በጽሁፍ አስቀምጦታል።

 

ህወሓት የትጥቅ ትግሉ እንደጀመረም በሰሜን ኢትዮጵያ የሚገኘው ሕዝብ በተለይ የትግራይ ሕብረተሰብ በግልጽ በማያሻማ ከመነሻው ጀምሮ ተቃውሞታል። ህ.ወ.ሓ.ት የተባለው ድርጅትና ፕሮግራሙ አልተቀበለውም ነበር ።ከዚሁም የተነሳ የ ህ.ወ.ሓ.ት አመራር ቂም በቀል በመያዝ በሰነዘሩት የጥቃት እርምጃ የትግራይ ሕብረተሰft በጣም ብዙ የሒወት መስዋእትነትና ሃብት ንብረቱ በህ.ወ.ሓ፣ት. እየተዘረፈ ውርስ ሆነዋል ተብሎ የፈረሰው ቤት ከህ.ወ.ሓ.ት ግድያ ያመለጠ ትንሽ ቢሆንም ወደ ጎንደር ሸዋ ጎጃም ተበተነ ።

 

በየካቲት ወር 1968 የተዘረጋው ጸረ ኢትዮጵያና ጸረ-ሕዝብ ፕሮግራሙ በመጀመሪያ ተቃውሞ የገጠመው በትግራይ ሕዝብ ነበር። በዚሁም የተነሳ የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ የመስዋ’እትነት እዳ ከፍሎበታል። በህወሓት አመራር ሕዝft ከየቤቱ ከተገኘበት በህወሓት የሃለዋ ወያኔ አባላት እየተያዘ ተረሸነ፣ ንብረቱ ተወረሰ፣ ቤቱ ፈረሰ፣ ሕፃናት አሳዳጊና ወላጅ በማጣት ተበታትነዋል። ፕሮግራሙ እውቅና አንሰጥም፣ እናንተ አሁን በትጥቅ ትግል ተሰማርተናል የምትሉትን ማንነታችሁን አናውቅም፤ በግልጽ የሚታየው በፕሮግራም አቋማችሁ ጸረ- ኢትዮጵያ ሉአላዊነት መነሳታችሁ ይናገራል። እኛ የትግራይ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ ሃገራችን በተደጋጋሚ በግብጾች፣ ቱርኮች፣ የሱዳን ማህዲስቶች፣ በጣልያን ስትወረር ሃገራችንን ከጠላት ለመከላከል ሁላችን ኢትዮጵያውያ አማራ ኦሮሞው አፋሩ አሩሲው ወለጋው ትግሬው ወላይታው ሲዳማው ኦጋዴው ከምባታው    ወ.ዘ.ተ.ሁሉም ኢትዮጵያዊ አንድም ሳይቀር  በዘር በቋንቋ በሃይማኖት ሳንከፋፈ በአንድነት በኢትዮጵያዊነታችን ተባብረን ተደጋግፈን ሃገራችን ኢትዮጵያ በጠላት እንዳትወረር ደማችንን አፍሰን አጥንታችንን ከስክሰን ነፃነቷን የጠበቀች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን አስረክበናል።ተ.ሓ.ህ.ት. የምትሉት የምትናገራት ነጻነትዋ ታሪክዋ ገናናዋ እትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤት የቀይ ባህር ንግሥት ኢትዮጵያ ታሪዋን በመካድ ኢትዮጵያ የተፈጠረችው በዳግማዊ ምኒሊክ ፡ታሪክዋ ከ100 ዓመት ያነሰ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር እንዳልነበረች በየቦታው እየተዘዋወራችሁ ለትግራይ ህብረተሰብ ትሰብካላችሁ አማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት ደመኛ ጠላት የምትሉት ለኛ ጠላት ሳይሆን ወንድማችን ሥጋችን ኢትዮጵያዊ ወንድማችን ነው ።

 

ዛሬ ለትግራይ ሕዝብ ታግለን ትግራይን ነፃ አውጥተን የራስዋ መንግሥት ትመሰርታለች የምትሉት የተሓህት- ህወሓት መሪዎች ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ይህን በናንተ ፕሮግራም የተካተተውን ለአስተዳደሩ ለቅኝ ገዥነት እንዲመቸው ያስቀመጥው ሃገርና ሕዝብን ከፋፍሎት የነበረውን በጣልያን እቅድ የኢትዮጵያን አንድነት ለማጥፋትና ለመደምሰስ ነው። ታዲያስ እናንተ ከጣልያን የከፋችሁ እንጂ የተሻላችሁ አይደላችሁም፤ በማለቱና በግልጽ በመናገሩ ከሐምሌ 1968 ጀምሮ የህወሓት መሪዎች ሰፊ የመግደልና የማጥፋት እርምጃ  በትግራይ ሕብረተሰብ ላይ በማጠናከር ሕዝftን አጠፉት።ሃብት ንብረቱ ወረሱት ፤ ቤቱ ፈረሰ ።

 

በዚህ ወቅት የነበሩት ዋና አመራር፤ አረጋዊ በርሄ፣ የድርጅቱ ሊቀመንበርና ወታደራዊ አዛዥ፤ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ም/ሊቀመንበር፤ አባይ ፀሃየ፣ የፖለቲካ መሪ፤ ስብሃት ነጋ፣ የአረጋዊ በርሄ አማካሪና የሃለዋ ወያነ ሃላፊ፤ ስዩም መስፍን እና ተጨማሪ ዋና ተባባሪ መለስ ዜናዊ። እነዚህ ስድስቱ ታጋዮች በሕዝብ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ትመካክረው በአንድነት ተሰባስበው ይወስናሉ፣ በተግባርም ይፈጽማሉ። በ1969 ከፈጸሙት የግፍ ግፍ ጣልያን 1928 ኢትዮጵያን ዳግም በወረረበት ጊዜ ኢትዮጵያውያን ከተለያዩ የሃገሪቱ ክፍል ክተት በማለት ሃገራቸውን ከወራሪ ጠላት ለመከላከል በሞላው ሃገራችን በተለያዩ የጦርነት አውድማ ተሰልፈው ወራሪውን ጠላት በአምስት ዓመት የአርበኞች ታጋድሎ ተሸንፎ ጓዙን ሳይጠቀልል በውርደትና በሃፍረት ተሸንፎ ወደመጣበት ሃገሩ ጣልያን እንደሸሸ ከገድላዊ ታሪካችን ተምረናል። የትግራይ ሕዝብ ከወንድሞቹ ኢትዮጵያውያን ጎን ተሰልፎ ለሃገር ሉዓላዊነትና ክብር ሲል መስዋእትነት ከከፈሉት ኢትዮጵያውያን አንዱ ነው። የተሓህት-ህወሓት መሪዎች ይህ የሃገር ክብር የተቀደሰ ጀግንነት አልተቀበሉትም። ለምን የትግራይ ሕዝብ ጸረ-ጣልያን ሆኖ ተሰለፈ በማለት የተናደዱት በአረጋዊ በርሄ የሚመሩ የተሓህት-ህወሓት መሪዎች አርበኞች አዛውንቶችን ከየቤታቸው በመልቀም

 

ከየአሉበት በማሰር በቀን ከእርሻ ቦታው ለሊት ክቤቱ በማፈን ሃለዋ ወያነ አስገብተው ደብዛቸው እንድ ውሃ ሽታ ሆኖ ቀረ። ከነዚህ ከተገደሉት ብዛታቸው ባይታወቅም ለአብነት ከሚጠቀሱት መካከል ፊታውራሪ በጹእ ው/ጊዮርጊስ፤ የ82 ዓመት፣ ዳጃዝማች ዘገየ አዛውንት ከነልጆቻቸው፣ ባft ዘገየ፣ ፊታውራሪ እምብዛ፣ ፊታውራሪ አጽብሃ፣ አስር አለቃ ገብረሥላሴ፣ የ10 አለቃ ገብረዝጊ አለማዮህ እነዚህ ለአብነት ይበቃሉ። እነዚህ የኢትዮጵያ አርበኞች ከያሉበት እየተያዙ የተገደሉት ከጣልያን ጋር ለምን ጦርነት ገጠማችሁ ተብለው እንጂ አዛውንቶቹ ያጠፉት ጥፋት የለም። ይህ ሲሆን እውነት ተሓህት-ህወሓት ለትግራይ ሕዝብ የቆሞ ነው? መልሱ፣ አይደለም ነው። ተሓህት-ህወሓት በፀረ-ኢትዮጵያ ባእዳን የተመሰረተ ድርጅት ነው። ለስልጣን ያበቁትም እነሱ ናቸው። ተሓህት-ህወሓት በትግራይ ሕዝብ ላይ የፈጸመው ግፍ እጅግ ዘግናኝ ስለሆነ ሌላው ቀርቶ ፈዳያን ወይም አትፍቶ ጠፊterriorist ftድን በማቋቋም በየአውራጃ ያፈሰሰው ደም የትናንት ትዝታ ነው። የትግራይ ሕዝብ በተሓህት-ህወሓት ንብረቱ ተዘረፈ፣ መሬቱ ተነጠቀ፣ ቤቱ ፈረሰ፣ ለችግርና መከራ ተዳረግ፣ ተገደለ፣ ተሰደደ። ለዚህ ዋና ተጠያቂዎቹ የህወሓት አመራር፣ አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን እና መለስ ዜናዊ ናቸው። እነዚህም ቢሆኑ ተከታትለው የመጡ፤ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ገብሩ አስራት፣ ዘርአይ አስገዶም፣ ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ አስፍሃ ሃጎስ፣ አርከበ እቁባይ፣ ተወልድ ወ/ማርያም፣ እነዚህ ደግሞ በሕብረተስዉ ግድያውን በመፈጸም እና ጥረው ግረው ያፈሩትን ሃብት ንበረት ለህ.ወ.ሓ.ት ውርስ ተደርገዋል በማለት በመዝረፍ ተባባሪና አስተባባሪ በመሆን በትግራይ ሕዝብ ወንጀል ፈጽመዋል ። በታጋዩ ላይ በፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ ናቸው ፤። በፈፀሙት አሰቃቂ ተግባራቸው በወንጀሉ ይጠየቃሉ። በተለየ ደግሞ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት በተመለከተ ከላይ የተጠቀሱት ዋና መሪዎች የኢትዮጵያን አንድነት፣ ሉአላዊነት፣ መሬት አሳልፎ ለሱዳን በመሸጥ የወያኔ አመራር ቀዳሚ ተግባራቸው አደርገው ሲንቀሳቀሱ፣ እነዚህ የተጠቀሱት የማ/ኮሚቴ አባላት ተባባሪ በመሆን በኢትዮጵያና ሕዝቧ ላይ በርካታ የካሃዲነት ተግባራት ሲፈጽሙ የቆዩ ናቸው። የኤርትራን መገንጠልም ተባብረው ከነአረጋዊ በርሄ ጋር በመወገን ኤርትራን አስገነጠሉ በሃገር ላይ ጉዳት አድርሰዋል።ለጊዛዊ ጥቅም ብለው ከሱዳን መንግሥት በጀነራል ጃእፈር ኒሜሪ ፕረዚዳንት ነበር ጊዜ በወቅቱ የነበረው የገዳሪፍ ገዥ በ1975ዓ.ም  መስከረም  ወር ከላይ የተጠቀሱ የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች እና የሱዳን ባለሥልጣናት በቋጩት ውል መሰረት የኢትዮጵያ ለምና ታሪካዊ መሬት በጸረ ኢትዮጵያዊነት የተነሱት የወያኔ መሪዎች አሳልፈው ለባእድ ሃገር ለጊዜዊ ጥቅም ሽጠዋል ።ይህም ምንም  ህዝባዊ ውክልና ሳይኖራቸው ትግራይን ለማ ስገንጠል የተነሱ ከሃዲ ባንዳዎች ። ዛሬ ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ቅኝ ገዢ ወያኔ ህወሓት ለሱዳን ለመስጠት ደፋ ቀና እያሉ ይገኛሉ ። በዚሁስ የኢትዮጵያ ህዝብስ የሚወዳት የታሪክ ባለቤት ሃገሩ እየተሸራረፈች ለባዕድ ሃገር ለሱዳን እየተሸጠች ባለችበት ጊዜ ምን እያለ ነው ? የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር ድሮ የነበሩ አሁንም ያሉ የኢትዮጵያን ሏአልዊንት የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በአለም አቀፍ የተከበር ወሰን በወያኔ ባንዳ መሪዎች ለባእድ አሳልፎ መስጠት ከባድ ክህደት ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ህዝብ ሃገርና ህዝብ አሳልፎ መሸጥ ተፈጽሞበታል ።ወያኔው ህ.ወ.ሓ.ት ኢትዮጵያና ህዝብዋን አጠፋለሁ በማለት ከደደቢት በረሃ ይዞት በመጣ ጸረ ኢትዮጵያ አቋሙ ሥልጣን ከያዘበት ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛቱ ወስጥ ከተቆጣጠረ የኢትዮጵያን ሏላዊነት ያወደመ ያፈረሰ ስርዓት ነው ።በህ.ወ.ሓ.ት. የፖለቲካ ወይም የፖሊሲ ልዩነት ተፈጥሮ ወይም ታይቶ አያውቅም ፤የሚከተሉት ፖሊሲ ያው ነች ፤ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፀረ ህዝብ ከፋፋይ ፤ፀረ ዲሞክራሲ

አሁንም በሥልጣን ያሉትን ጨምረን አንድም የራእይ ልዩነት ያለው ግለሰብ አመራር የነበረው የለም። ችግራቸው የሥልጣን ሽኩቻ ነው ፤ይህም ገና ከትግሉ መነሻ ጀምሮ በማያቋርጥ እስከ አሁኑ ጊዜ በግልጽ የሚታየው ነው ።በአሁኑ ጊዜ አረጋዊ በርሄም ሆነ ሌሎቹ የተባረሩ የሚናገሩት ለኢትዮጵያ ህዝብን ለማታለል ፤ በትግሉ ጊዜ ብዙ ልዩነት ነበረን ሲሉ ይደመጣሉ ፤ልዩነታችሁ ምን ነበር ተብለው ቢጠየቁ ግን መልስ የላቸውም ፤በተለይ አረጋዊ በርሄ ፤ድርጅቱ እስከ ተባረረ ሓምሌ ወር 1977ዓ.ም. በዋናነት በበላይነት ሲመራው የነበረ እርሱ ነው ፤ፕሮግራሙን ተንከባክft ያቆየው እሱ ነው ፤የሚወጡ አዳዲስ ፖሊሲ በሱ ነው ፤በድርጅቱ ውስጥ አንድም አመራር የአረጋዊ በርሄ ሃሳብ የሚቃወም የለም ፤ሁሉ በእጁ ፤ስለሆነም ዛሬ የሚናገረው ውሸት መሆኑ መታወቅ አለበት ፤ይህ ሁሉ የሚዘባርቀው ፤ህ.ወ.ሓ.ት. ወንጀለኛ ድርጅት ነው በዘር ማጥፋት ወንጀል ይጠየቃል ፤ለወልቃይት ጠገዴ በጉልበቱ በመሪነት ፤ እንዲሁም የሰሜን ወሎ ወደ ትግራይ በማካለል የመሬት መስፋፋትና ወረራ የፈጸመው እሱ ስለሆነ

 

ከተጠያቂነት ለማምለጥ ባፈሰሰው የንፁሃን ዜጎች ደም ተጠያቂነት ለመሸሽ ፤የፈጠረው ዘዴ ህዝብ መታለል የለበትም ።

 

አረጋዊ በርሄ በህወሓት ወስጥ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ የመጣበት ማህበረ ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገበት) ከተመሰረተበት እለት መስከረም 1967 ጀምሮ ተሓህት – ህወሓት የትጥቅ ትግሉን ከጀመረበት የካቲት 11፣ 1967 አንስቶ እስከ 1977 መጨረሻ ህወሓትን የሚዘውረው የነበረ በዚሁ ፀረ-ኢትዮጵያ አንድነትና ፀረ-ሕዝብ ግለሰብ ነበር። በድርጅቱ የሚፈጸሙ ጉዳዮች የሱን ይሁንታ ማግኘት አለባቸው እሱ ካልፈቀደ ደግሞ ይሰረዛል።

 

አረጋዊ በርሄ ገና ትገሉ ሳይጀመር የድርጅቱን ፕሮግራም በዋና ሃላፊነት ያዘጋጀ ነው። ይህ ፕሮግራም ነው ዛሬ ኢትዮጵያ እያፈረስ እየበወዘ ሃገራችን ኢትዮጵያ በማትወጣው ችግር ዳርጓት ያለው ። የሰሜን ጎንደር ግዛቶችን አማራው የሚኖርበት ለብዙ ሺህ ዓመታት የአማራ መሬት ከዘር እስከ ዘር ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገር የመጣው የአማራው ባህልና ማንነት እየጠበቀ የመጣው የትግራይ መሬት በሚል አጉል የመስፋፋት ዘይቤ አማራውን ዘሩ በማጥፋት ያለቀው በህ.ወ.ሓ.ት. አመራር ታሪክ ዘግቦታል ለዚሁየሰው እልቂት ዘር ማጥፋት ተጠያቂው የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች ከ1967 ዓ.ም. እስከ ዛሬዋ እለት ያሉትን አመራር ተጠያቂ ናቸው ። ነብሱን አይማረውና ባለቀንዱ የባንዳ ዘር መለስ ዜናዊ እና ሌሎች የሞቱም በወንጀሉ ይጠየቃሉ ። ማለት ነው፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ወላቃይት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ፣ ህ.ወ.ሓ.ት በፕሮግራሙ ውስጥ የእጅ ጽሁፉ( የአቶ አረጋዊ በርሄ) ከሰሜን ወሎም ራያና ቆቦ፣ ወልዲያ፣ አፍላ ደራ ወዘተ አጠቃላይ አለውሃ ምላሽ ተብለው የሚታወቁት የወሎ ግዛት ወደ ትግራይ አጠቃሎ ካርታውን ያዘጋጀው፣ መልክአ ምድሩን የለወጠው አሁን በትግራይ ክልል የተጠቃለሉት በአረጋዊ በርሄ የተዘጋጀው ነው። ይህን ለማረጋገጥ መቅድም በሚለው ( v )ቁጥር ነው (ገጽ 5

)እንመልከት ፤።

 

ህወሓት ትግሉን እንደጀመረ የቅድሚያ ትኩረት የሰጠው ሰሜን ጎንደርን ነበር። ይህንን የሰሜን ጎንደር ለም መሬት ለመያዝና ወሮ ወደ ትግራይ ለማጠቃለለ በወቅቱ መጠሪያው ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) አስቀድሞ  በመዘጋጀት ከነዚህም የሚታዩት ከነበሩት ተጨባጭ ሁኔታዎች። ጊዜው በ መጀመሪያ 1969 ዓ.ም መጀመሪያ ጀምሮ።

 

  1. የዚህ ድርጀት የሕዝብ ግንኙነት አባላት ሰርገው በመግባት በየቦታው የሚኖሩትን አማራ ታላላቅ ሰዎች የቦታው ታሪካዊ ጥናት የሚያውቁ ፤ በህዝft ተቀባይነት ያላቸው ፤ተናግረው ህብረተሰft የሚቀበላቸው

፤ጥናት በማካሄድ፣

  1. የታጠቁ ሰዎች ብዛታቸውም ሆነ ስሜታቸውን ማጥናት፣ ያላቸውን ሃብትና ንብረት የአካባቢውን ኗሪ ብዛትም ጭምር ማጥናት፣ይህ የትግራይ መሬት ነው ቢባሉ የሚያስከትሉት ችግር ማወቅ ማጥናት በተናጠል ማነጋገር ወ.ዘ.ተ. የሚሉትን ተሸክመው መንቀሳቀስ ተጀመረ ።
  2. ይህንን የሰሜን ጎንደር ለም መሬት በጉልበትና በሃይል ለመውረር በአማራው ላይ ከባድ ጥቃት መፈጸም ግዴታ መሆኑ አስቀድሞ ተይዞ የትግራይን ሕዝብ ድጋፍ የሚፈልጉ የተሓህት አመራር በወቅቱ የነበሩ አመራር፣ አረጋዊ በርሄ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ በአራቱ መአዘን ተበታትነው አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት መሆኑን፣ የትግራይን መሬት ነጥቀው የትግራይን ሕዝብ ለችግርና መከራ የደረጉት ደመኛ ጠላቶችህ ሲሆኑ የነጠቁህን መሬትህ ወልቃይት ፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ቃፍታ ሁመራ፣ እንዲሁም በሰሜን ወሎ ከአለ ውሃ ምላሽ የተነጠቅነውን መሬታችንን ለማስመለስ የትግራይ ሕዝብ የፈጠርከው መሪ ድርጅትህ ተሓህት ድጋፍህን እና እርዳታህን እንፈልጋለን፣ እያሉ ሕዝብ እየሰበሰft ተቆርቋሪ በመምሰል እያለቀሱ የትግራይን ሕዝብ አስተሳሰብ ለመቀየር ከፍጠኛ እንቅስቃሴ አደረጉ። ቢሆንም ከትግራይ ሕዝብ ያገኙት መልስ የሚከተሉት ነበሩ።
  3. አማራ ጠላታችሁ ነው የምትሉን ከእውነት የራቀ ነው። አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት አይደለም፣ ሆኖም አያውቅም። በአንድነት ሁነን ኢትዮጵያን ከብዙ የውጭ ወራሪ ሃይል አድነናል ተከላክለናልም።

 

በዚህም አማራና ትግሬው ኢትዮጵያዊ ማተባችን በጋብቻና በባህል የተሳሰረ ሕዝብ ነው። ስለዚህ አማራ የኛ ወገን ትግሬውም የአማራ ወገን ነው።ልዩነት ጥላቻ ቅራኔ የለንም አንድ ኢትዮጵያዊ ህዝብ ነን ። ለወደፊቱ አይኖርም :አብረን እንኖራለን ።

  1. ስለመሬቱ የምትናገሩት የትግራይ አልነበረም ሆም አያውቅም። ስለሆነም የሰሜን ጎንደርና የሰሜን ወሎ የትግራይ መሬት አልነበርም አሁንም አይደለም ከትግራይ የተነጠቀ መሬት የለም። የራሳቸው መሬት ነው። የኛ የትግራይ አይደለም፣ አልነበረም። የትግራይ ሕዝብ በተናገረው እውነተኛ ሃሳft ቀጠለ። ከሃቀኛ ሃሳft ፍንክች ባለማለቱ የወያኔው አመራር ግራ ተጋባ ጸረ ትግራይ ህዝብም መንቀሳቀስ ተጀመረ
  2. ስለ ተሓህት የትግራይ ሕዝብ ድርጅት ነው የምትሉት፣ የታጠቀ ሃይል የትግራይ ሕዝብ ድረጅት አይደለም፣ አናውቀውም። የራሳችሁ የናንተው ነው። የትግራይ ሕዝብ ይህንን ድረጅት ከየት እንደመጣ፣ ማን እንደፈጠረው የምናውቀው ነገር የለም፣ እውቅናም አንሰጥም፣ በማለት የማያወላውል መልስ አግኝተው ራሳቸውን ደፉ፣ በዚሁ ጊዜ ግንቦት ወር 1968ዓ.ም አካባቢ የትግራይ ህዝብን በተናጠል ለማጥቃት የተነሱት ። እነ አረጋዊ በርሄ። እነዚህ የተህሓት መሪዎች በትግራይ ሕዝብ ላይ አጸፋዊ ጥቃት በተቀናጀ መልኩ እንዲፈጸም ፖሊት ቢሮ፣ ማለትም በአረጋዊ በርሄ በሚመራው ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን ተሰብስበው በሶስት እቅዶች ላይ ተሰማሙ፡

–    1 የከተማውንና የገጠር ሕዝብ ግንኙነት በሕዝft ሙሉ የጥናት ክትትል እያደረጉ ለግደይ ዘርአጽዮን አንዲያቀርft፤፤..

–     2 የከተማውን ኗሪ የሚያጠቃ ፈዳያን ‘አጥፍቶ ጠፊ” terrorist እንዲቋቋም፣ ስልጠናም እንዲያገኝ፣

–      3 ክብሪት የሚባል ጉጅሌ ገዳይና አፋኝ ftድን እንዲቋቋም ተስማሙ። ይህ ጉጅሌ 12 ሰዎች የያዘ ሲሆን 7 ታጋዮች 5 ሚሊሽያ ሆኖ ተመሰረተ። የሚሊሽያው ዋና ተግባሩ መንገድ መሪ የሚፈለጉ ሰዎች ጦቋሚ።ከተራ ቁጥር 1—እስከ 3 ተግባራዊ ም ተደረገ ።

በዚሁም ጊዜ የነበሩት (06) ሓለዋ ወያነ፣ ቀደም ሲል የነበሩት ሰፋፊ ቤቶች እየተፈለጉ ነዋሪውን በማባረር ሲጠቀሙበት የነበሩትን በመተው ሰው በማይንቀሳቀበት ቦታ በመምረጥ፤ ሽራሮ ወረዳ ሸሸቢት ftምበት፣ ሱር፣ ወርዲ፣ ፃኢና አዲበቅሎ፣ ዓዴት፣ ዓዲ ጨጓር፣ ፣ በለሳ፣ ማይሃምቶና ባኽላ ሳምረ። እነዚህን ሰፋፊ መግደያ ቦታዎች በአዲስ ዘዴ በመስራት ገነft ።፣ ይህም በግደይ ዘርአጽዮን መሪነት ከመሬት በታች       2 ሜትር ተቆፍረው እንዲሰሩ ክ200 ያላነስ እስረኛ የሚታሰርበት አንዲት ጠባብ መስኮት ያላት ሆኖ እንዲሰራ በህ.ወ.ሓ.ቱ ም/ሊቀመንበር በግደይ ዘራጽዮን ትእዛዝ መሰረት ከላይ በተጠቀሱ ቦታዎች ለመጀምሪያ ጊዜ ተሰሩ ። በተእዛዙ መሰረትም ሥራው ተጠናቀቀ። ይህ ጊዜ 1969ዓ.ም መጨረሻ  ነበር ።የትግራይ ህዝብም ያለቀው የተገደለው በእነዚህ ቦታ ነው ። በጠባብዋ መስኮት ዓየ ዛፍ በእርጥft እየተቆረጠ ተፈልጦ በእሳት በማቀጣጠል በጠባብዋ መስኮት በመልቀቅ የሰው ልጅ ፍጡር በጢሱ ታፍኖ ያለቀው አምላክ ይቁጠረው ። የዚች አሰቃቂ ግድያም የግደይ ዘራጽዮን ብልሃት ናት ።ለዚህ ክፉ የውንጀል ግድያም ይጠየቅበታ ።ይህ ክፉ አገዳደል በተለይ በአማራው ህዝብ በስፋት የወያኔ መሪዎች በመጠቀማቸው የአማራውን ዘር አጥፍተዋል ።

 

ክብሪት ተንቀሳቃሹ ጉጅሌ፡ ሆኖ     ሲመሰረቱ፣ 16 ጉጅሌ     ነበር የተመሰረተው የእነዚህ መሪዎችም በአርከበ እቁባይ፣ አሰፋ ማሞ፣ ሰአረ መኮንን፣ ሽሻይ በላይ (አመደ)፣ ታደስ ጋውናይ፣ ወዘተ በመደራጀት በየገጠሩና በየከተማው አካባቢ እንዲሁም በየወረዳው በሌሊት ተሽለኩልከው በመግባት የሚፈልጉትን ሰው ወንድ ፤ ሴት አፍነው በማውጣት ሃለዋ ወያነ ታስሮ ፤ታስራ በማስገባት እዛው እርምጃ ይወሰድበታል ( 06 ) ሓለዋ ወያኔ የገባ ሰው ሁሉ በሂወት ወደ ቤቱ አይመለስም ። ሕዝብ የሚገደልበት መግደያ የሲኦል ገሃነብ ነው ። በገጠሩ ነዋሪ በፈለጉት ስአት በመሄድ ኗሪውን ሰላማዊ ዜጋ ኢትዮጵያዊ በማሰር ንበረቱን በመውረስ እየታሰረ ሃለዋ ወያኔ ገብቶ ይገደላል ፣ ቤት ፈረሰ ልጆች ካለ አባትና እናት ተበታትነው ቀሩ፤ በጅምላ ፉድጓድ በጥይት ይረሸናሉ። መግደያ ጉድጓዳቸውም የሚቆፉራት ራሳቸው ተገዳዮቹ ናቸው ።

 

ፈዳያን የተባለው በብስራት አማረ የሚመራው አጥፍቶ ጠፊ ሽብርተኛው ክፍል በተመሰረተው ከሓምሌ ወር 1969 ዓ.ም ጀምሮ  በየከተማው አውራጃዎች አድዋ፤ መቀሌ ፤ሽሬ፤ አክሱም ፤አዲግራት፤ ውቅሮ ሁለት አውላእሎ ፤ ወዘተ እንዲሁም በወረዳዎች እየገባ በመቶዎች የሚቆጠሩ በየከተማውና በወረዳው በቀን ተመሳስሎ በመግባት በየመጠጥ ቤቱ ሻይ ቤት በማኸል ከተማ ቤተ ክርስትያን ውስጥ አጋጣሚው ሲመችለት አፍኖ በማስወጣት የስንቱን ንጹሃን ዜጎች በጠራራ ቀን ደማቸው ፈሰሰ ተገደሉ።

 

በዚሁ ፈዳያን የተሰማሩ አመራር፣ አረጋዊ በርሄ፣ አድዋ፣ አባይ ፀሃየ፣ አክሱም፣ አርከበ እቁባይ፣ አዲግራት፣ ስዩም መስፍን፣ ውቅሮ፣ ስብሃት ነጋ፣ ተምቤን፣ በሽብርተኝነት ተሰማርተው ሰዎች ገድለዋል። ግደይ ዘርአጽዮን እንትጮ፣ ሰለክላካ፣ ራማ፤ ኩሓ የስንት ሰው ሕይወት ከግብረአበሮቹ ፈዳያን ጋር አጠፋ። ይህ የወያኔ ጥቃት ከተሓህት-ህወሓት በትግራይ ሕዝብ የማጥቃት ዘመቻው በተለያየ መልኩ ቀጠለ።ግደይ ዘራጽዮን አክሱም ከተማ የጉጅሌ መሪ በመሆን ሁለት የአብርሃ ወአፅብሃ ሁለተኛ መለስተኛ ደረጃ አስተማሪዎች መም/አበበ ፤ መም/ መላኩ መንገሻ የተባሉ አስተማሪዎች በመግደሉ ተወገዘ ።ተመልሶ አክሱም የሚገባበት እድልም የለውም

።ይህ ሰው በተፈጠረው ውግዘት ለወላጆቹም ግደይ በፈጸመው ወንጀል ቁርሸው ትቶ አልፈዋል ። የግደይ ጣጣ በዙ ነው ፤ግደይ ዘራጽዮን ሱር ሓለዋ ወያኔ ታስረው የነብሩት በዙዎቹ አማራ ቀሪዎቹ የትግራይ ሰዎች በየታሰሩበት ከመሬት በታች የጉድጓድ እስር ቤቶች የዓየ እንጨት በማቀጣጠል እንጨቱ እይተቀጣጣለ በትንሽዋ ቀዳዳ መስኮት የገባው ጢስ እዛው ጉድጓዱ የታሰረው ንፁሃን ዜጎች በጢሱ ታፍነው ሲያልቁ የተመለከተው በህዝብ ግኙኝነት ክፍል የሚሰራ ታጋይ ዓለም ወልደገሪማ የሚባለው የቀ.ኃ.ሥ.ዩኒቨርሲትይ የ4ኛ ዓመት በኢኮነሚክስ ተማሪ የነበረው ፤ግደይ ዘራጽዮን ኢ-ሰአዊ አረሜናዊ ግድያ ህዝftን በመፍጀቱ በዓይኑ በማየቱ በድርጊቱ አወገዘው ፤ግደይ ቂሙን ቋጥሮ ቆይቶ ፤በስራ ምክንያት ዓለም ው/ገሪማ ወደ ርጅን 2 የሚሄድ መሆኑ ስላወቀ ዓዴት የሚገኘ ሓለዋ ወያኔ 06 ለብስራት አማረ ደብዳቤ ፅፎ ፤የውስጥ ይዘትዋ ዓለም ው/ገሪማ ይህች ደብዳቤ እንደሰጠ ተቀብለህ ወዲውኑ እሰረው ከዛ ረሽነህ ግደለው የምትል ፤ዓለም ው/ገሪም የመግደያው የፍርድ ወረቀቱ ተሽክሞ ሂዶ አዲበቅሎ ዓዴት ወዲያውኑ በጥይት ተደብድቦ ተገደለ ፡ይህች የግፍ ግድያ ብዙም ሳትቆይ እጃቸው ለደርግ የሰጡ የአክሱም ልጆች ታጋይ ነበር ፤ዓለም በግደይ ዘራጽዮን እንደተገደለ ለውላጅ አባቱ ነገርዋቸው ፤ምህረይ (ቄስ ) ወልደገሪማም የአክሱም ህዝበ አዳም በልጃቸው በህ.ወ.ሓ.ት. መሪው የተፈጸመው ገፍ በየቤተ ክርስትያኑ ከማጋለጥ ቀጠሉበት ።የዓለም ወንድሞች ደማቸው ለመበቀል ፤ጊዜያቸው እየጠበቁ ናቸው ። ወደ ዋናው አረእስታችን ስንመለስ ።

 

ወያኔዎች በትግራይ ህዝብ የጥቃት ዘመቻ የከፈቱበት ምክንያት የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ እምነቱ ከፋፋይና ዘረኛው ወያኔ ፤በእውቅና አለመቀበሉ ቀጥሎ ያለውን ዋና ምክንያቶች እንመልከት ።

  1. አማራ ደመኛ ጠላትህ ሲሉት አይደለም ወንድሜ ወገኔ ኢትዮጵያዊ ነው በማለቱ፣

2ተሓህት የትግራይን ሕዝብ አይወክልም አንውቃችሁን  በማለቱ፣

3   ተሓህት የነጠቀውን የሰሜን ጎንደርና የሰሜን ወሎ ለም መሬቶች አንቀበልም፣ የሰሜን ጎንደሩ የጎንደር ጠ/ግዛት ነው፣ የሰሜን ወሎ የወሎ ጠ/ግዛት ነው፣ ከትግራይ ግንኙነት የላቸውም በጎንደር በኩል የሚያዋስነን ተከዜ ወንዝ ነው ።በወሎ በኩል ማይ ጨው ችንኮማጂ ነው ፤ሲሆን በምን መልኩ ነው የትግራይ የሚሆነው በማለቱ፣ ከወንድሞቻችን ጥላቻና ቅራኔ አትፍጠሩብን ብሎ ጭሆ በመናገሩ ፤ ሸዋዊ የትግራይ አማራ ተብሎ የግድያ ኖህ የወረደበት ።

4   የተሓህትን ፕሮግራም አንቀበልም 1ኛ  ትግራይ የኢትዮጵያ  የታሪክ  አስኳል የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ የሚመካ ነው ፤ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ግዛት እንጂ ቅኝ ተገዢ አይደለችም

፤ አማራው ኢትዮጵያዊ ፤ ትግራይም ኢትዮጵያዊ ፤ ምንም ልዩነት        የለንም ። በማለቱ ጭሆ በመናገሩ

።በህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የታሪክ አዋቂዎች አዛውንት ሊቃውንት የአምስት ዓመት ከወራሪው ጣልያን የተዋጉ አርበኞች በመብራት እየፈለገ የወያኔው መሪዎች የገደልዋችው ያጠፍዋችው ፤ ተገድለም ሃብት ንብረታቸው       ህ.ወ.ሓ.ት ወረሰው ። እነዚህ የሃገርና የህዝብ አለኝታዋች ሙሉ በሙሉ በትግሉ ጊዜ አጠፉዋቸው ፤ ገደልዋቸው ። ፤ዛሬ ስለ ትግራይም ሆነ አጠቃላይ ስለ

 

ነበረው ጥንታዊ ታሪክ በትግራይ ውስጥ የሚያውቅ ተፈልጎ አንድም አይገኝም ።ትግራይ በ17ቱ የህ.ወ.ሓ.ት. የትግሉ ዘመን ወድማለች ። የታሪክ አዋቂ በኢትዮጵያዊነቱ የሚቆረቆር በትግሉ ዘመን ተመልሶ እንድያንሰራራ ተመልሶ እንዳይፈጠር አድርገው በመምታት አጥፍተዉታል ። በጣም የሚያስገርም ሁኔታም የተፈፀመው በወልቃይት ፤ጠለምት ፤ ጠገዴ ብቻ በሰሜን ጎንደር አማራው በተመሳሳይ ሁኔታ አዛውንቶች እየተፈለጉ በስውር እይታፈኑ የት እንደገft የማይታወቁ ማን ተያዘ ማን ተገደለ የሚለው በግልጽ ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም ብዙ የሰሜን ጎንደር አዋቂ ሽማግሌዎች የውሃ ሽታ ሆነው የቀሩ አሉ ፤ይህን ለማወቅ የሚችሉት የየአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው ።እነዚህ ግን የታሪክ አዋቂዎች ናቸው ።ታሪክ አዋቂ ሲጠፋም ተተኪው ትውልድ ይቸገራል ።የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ይህ እንደፖሊሳቸው የሚጠቀሙበትም የቆየው ታሪክ ለማጥፋትና ለማክሰም ነው  ።

 

በእነዚህ ንጹሃን የትግራይ እና የሰሜን ጎንደር ኢትዮጵያውያን የፈሰሰሰው ደም ትጠያቂው ማነው? ማነወስ ሃላፊነቱ የሚቀበለው ? ምንስ አጥፍተው ነው ? ወደ ትግራይ ስንመለስ ፤ የተናገሩት እውነት ነው ፡ትግራይ የአማራው ቅኝ ተገዢ አይደለችም ሰሜን ጎንደር ወልቃይት ፤ ጠገዴ ጠለምት ፤ቃፍታ ( ሰቲት ) ሁመራ የሰሜን ወሎን መሬቶች የትግራይ አይደሉም አልነበሩም ይህም ታሪክ የሚያውቀው ሃቅ ነው ።የትግራይ ህዝብ ምን አጠፋ ህ.ወ.ሓ.ት የገደለው የረሸነው ያጠፋው ። ማንኛው ህዝብ አስተዋይና አርቆም ሃሳቢ ነው የትግራይ ህዝብም ከዚሁ ተነስቶ ነብር እውነቱን የተናገርው ። ይህ ህ.ወ.ሓ.ት የጀመረው በትግራይ ህብረተሰብ ማጥቃትና መግደል የንጹሃን ዜጎችደም በከንቱ የፈሰሰው ይህ ደም አሁንም በእግዚአቢሄር ፊት እየጮኸ ይኖራል መሬትና ሰማይ የፈጠረ ጌታም ፍርዱ ይሰጣል የማይቀር ነው ። የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች የአማራው ጎንደሬው ለምና ሰፊ መሬት በሕገ ወጥ በጉልበት ለመንጠቅ የአማራው ደም የንጹን ኢትዮጵያወያን ዜጎች ደማቸው በትውልድ መንደራቸው እንደጎርፍ ፈሰሰ ካለምንም ጥፋትና ሃጥያት ፈሰዋል ዘራቸው አጥፍተዋል ህፃን አራስ እርጉዝ ሽማግሌ ወጣት ተገድለዋል በስዉር ጠፍተዋል የእንዚህ ንጹሃን ኢትዮጵያዊ ዜጎችም ፈጣሪ አምላክ ፊት ደማቸው እየጮኸ ነው ።ቀሪዎቹ በሂወት ያመለጡም በስደት እየተንከራተቱ ይኖራሉ ።ይህን አሳዛኝ ታሪክ ያነሳሁት የትግራይ ነፃ ህዝባዊ ወያኔ ፤ ህ.ወ.ሓ.ት. ማ.ገ.ብ.ት ተብሎ ሲፈጠር ቀጥሎም ደደቢት በርሃ ወርዶ ተ.ሓ.ህ.ት. ( ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ ) ከዛም ስሙን ለውጦ ህ.ወ.ሓ.ት. ( ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ) ቢልም እውቅና ያልሰጠው በአንጻሩ ግን የትግራይ ሕብረተስብ ፀረ ወያኔ አምርሮ የታገለው ህዝብ ነበር ፤ ፀረ ወያኔ ሆኖ መታገሉ ከባድ መስዋእትነት በሂወቱ በንብረቱ በሃብቱ ከፍሎ ያለፈው ። ሁሉ ኢትዮጵያዊም ይህን በእምነት ሁሉ ኢትዮጵያዊ ያምንበታል። ለዚሁም ተጠያዊቆቹ አረጋዊ በርሄ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስዩም መስፍን ፤መለስ ዜናዊ ሲሆኑ፣ እነዚህ በዋና የንፁሃን ደም በሰሜን ጎንደር በትግራይ በኢትዮጵያውያን ንፁህ ደም በፈጸሙት ወንጀል ግንባር ቀደም ተጠያቂ ናቸው ። ቀጥሎ ደግሞ፣፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ አርከበ ዕቁባይ ገብሩ አስራት በዋናነት ግንባር ቀደም ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ ህዝብ ክስ ሲመሰርትም መነሻው ከዚሁ ነው ።የህ.ወ.ሓ.ት. ፋሽሽት ድርጅት ለብዙ ዓመታት የምሩም እነዚህ ፤ተከታትለው ወደ ሥልጣን የመጡ እንመለክታለን ።

 

ይህ የትግራይ ሕዝብ በማጥፋት የተሰማራው የህወሓት አመራር ሕዝብ በመግደሉ በተሰማራበት ወቅት በተሓህት ውስጥ የነበርው ታጋይ በዝምታ አልተመለከተውም ነበር ከዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎች እና በህዝft እየተፈጽሙት ያሉትን ግፍን ሰቆቃ ድርጅቱ ከምን ተነስቶ በምን ምክንያት ሰላማዊ ህዝብ እያሰረና እያሰቃየ ሽማግሌዎች ወጣቱን ወንድ ሴት ይፈጃል የሚሉና ተዛማች ብዙ ጥያቄዎች ተነሱ ። አመራሩ በታጋዩ የተነሱ የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ተቀብሎ በሰላም ከመፍታት ይልቅ ታጋዩን በመወንጀል ። ይህ ፀረ ተ.ሓ.ህ.ት እንቅስቃሴ ነው በማለት ራሱ አመራሩ ለተነሱ የዲሞክራሲ ጥያቄ በመወንጀል    ሕንፍሽፍሽ የሚል ስም በምስጠት ፣ በበዙ ታጋዮችና ሰላማዊ ዜጋወም በሕንፍሽፍሽ ተመርዘዋል ተብሎ ሰላማዊ ዜጋው ከየቤቱ እየተለቀመ ታጋዩ ከትግል ሜዳው እየተለቀመ እየታፈነ በቶርቸርና በእሳት እየተቃጠለ በእሳት የጋለ ፍም ሳንጃ ሆድ እቃው እየገባ ተገደል፣ ጠፋ፣ የተገደሉት ሰላማዊ ዜጎችም ሙሉ      ንበረቱ ሃብቱም በህወሓት ተወረሰ።የስንቱን ቤት ፈረሰ ።

 

የትግራይ ሕብረተሰብ ለዚሁ ሁሉ መጥፎ ጥቃት የተዳረገበት ዋና ምክንያት ከላይ የተጠቀሱ ሲሆኑ ሌላው ደግሞ       ጣልያን  ኢትዮጵያ    በ1928 በወረረበት ጊዜ በአርበኝነት ጸረ ጣልያንን የተዋጉ  የተሓህት-ህወሓት አመራር ኮንነዉታ ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ መለስ ዜናዊ ያሳለፉት መመሪያ እንዚህ የትግራይ ሸዋ አማራ በአጭሩ አነጋገር ሸዋዊ ትግራዋይ በሙሉ በየትም ትግራይ መሬት የሚኖሩ በሕዝብ ግንኙነት እየተለቀሙ ታስረው ሃለዋ ወያኔ (06 ) በሚስጢር እንዲጋft በማለት በሰጡት የትእዛዝ መመሪያ ሁሉ ከያሉበት ተለቅመው ሃለዋ ወያኔ እየገft ተገድለዋል፣ ንብረታቸውን ተወርሰዋል። ዛሬ በትግራይ እንኳንስ ከጣልያን የተዋጋ በወቅቱ ሕጻናት የነበሩትም አንድም ሰው አይገኝም፣ ተገድለዋል። ዋና ምክንያቱ የተገደሉት 1 የህ.ወ.ሓ.ት የፖለቲካ አቋም ወይም ፕሮግራም አንቀበልም ብለው በማውገዛቸው 2 አማራ የትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ስለሆነ አብረን እንምታው እናጥቃው ሲሉትም የሰጠው መልስ አማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት አይደለም ሁላችን አንድ ኢትዮጵያ ወንድማሞች ነን አማራ የፈጸመብን በደል ጥቃት የለም አማራው የኛ፤ እኛም የሱ ነን ፤ 3 የሰሜን ጎንደር የሰሜን ወሎ መሬት የትግራይ ነው የምትሉን የትግራይ አይደለም በታሪክም አልነብረም የወንድሞቻችን በጉልበት የምትወሩት ያላችሁ ርስተ መሬት አንቀበልም በማለቱ          4 ጣልያን ጣልያን የምትሉት በየቦታ ከጣልያን የተዋጋነው ሃገራችን ኢትዮጵያ ለመውረር በቅኝ አገዛዝ ስርአቱ ሊገዛን የመጣው ወራሪ ቅኝ ገዢ ጠላት የሃገራችን ኢትዮጵያ አንድነትና ሏላዊነት አሳልፈን አንሰጥም በማለት ጣልያን መታነው አሸነፍነው ፤ ኢትዮጵያን ነፃ አወጣን ፤ በማለት ፀረ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት ባሳየው ጠንካራ አቋሙ ከላይ በተጠቀሱ የወያኔ መሪዎች ከባድ ጥቃት በመሰንዘር ህዝብ አለቀ ። ዛሬ ታሪክ ነጋሪ በትግራይ ፈጽሞ አይገኝም። የታሪክ ፈላስፋዎች የታሪክ አዋቂዎች የሆኑት የወያኔው መስራቶችና አሁንም በሥልጣን ያሉት ደንቆሮች የወያኔ መሪዎች በሥልጣን ኮረቻ የተንጠለጠሉ ቅኝ ገዢዎች የህ.ወ.ሓ.ት. ባንዳዎች ናቸው።

 

ይህ በዚሁ እንዳለ፣ የትሓህት-ህወሓት መሪዎች በትግራይ ሕብረተሰብ የጀመሩትን ጥቃት እንደቀጠለ ሁኖ የወልቃይት፤ ጠገዴ ፤ጠለምት ፤ሰቲት ሁመራን ፤ በጉልበትና በማን አለብኝነት በካርታቸው የተካተተው በፕሮግራማቸው ውስጥ የትግራይ መሬት ነው በማለት ሰፊዉን የጎንደር ክፍለ ሃገር መሬት የሰሜን ወሎ መሬት                                   በማካተት ( ፀሃፊና አዘጋጅ አረጋዊ በርሄ ) ሕገ ወጥ የለም ሰፊ መሬት ወረራ ፈጽመዋል ።ይህን ወረራ ለማስፈጸም የተካሄድ ቅድመ ዝግጅት  በሰሜን ቤገምድር ( ሰሜን ጎንደር)  ማለት ነው  ) 1ኛ  መኩንን ዘለለው የተባለው ነገር ግን አካባቢውን የማያውቀው በስመ ተወላጅ በአባቱ በኩል ተወላጅ የሆነወን ታጋይና በህዝብ ግኑኝነት ክፍል የተመደበ በሱ የሚመራ ftድን           በወልቃይት ፤በጠገዴ ፤በጠለምት ጥናት እንዲያካሂድ በ1969 ዓ.ም ውስጥ ተላከ ይህ ከሃዲ ግለሰብ ከግለ ሰው እስከ ftድን ከftድን  በየ በአላቱ እሁድ ወ.ዘ.ተ. በየቤት ክርስትያኑ እየተንቀሳቀሰ        ወልቃይት ፤ጠገዴ ፤ጠለምት ፤ ቃፍታ ሁመራ  የትግራይ መሬት መሆኑ የሰሜን ጎንደር ህዝብም ሁሉ ትግራዋይ መሆኑ የታርክ ሃቅነት በጎደለው ለማሳመን ባካሄደው መፍጨርጨር ሳይሳካለት በሙሉ የሰሜን ጎንደር ህዝብ በልበ ሙሉነት ወድቅ አደረገው ።በግልጽም እናንተ ወራሪ የጣልያን አሽከሮች ውላጅ ናችሁ በማለት አሸማቀቃችው ።ይህ የጎንደር ግዛት በማንም ያልተደፈረ በእናንተ ከሃዲዎች እይፈፈርም ብሎ ህዝft በግልጽ የተናገረበት ጊዜም ነው ። ተዋርዱ ተደብዶቦ፤ ህዝftም ወደ ማንም ቤት ዝር እንዳይሉ በማስጠንቀቅ በርሃብ ጠውልገው ወደ መጡበት እንዲመለሱ አደረጋቸው ። ነገር ግን መኮንን ዘለለውና ftዱኑ ሲያደርጉት የነበረው ሤራ ህዝft ሁሉ ቢቃወምም ትልልቅ ሰዎች የታሪክ አዋቂዎች የበሰሉ ጠንካራ ሰዎች በብዛት በሚስጢር እየመዘገft ፤ እነዚህ ሰዎች በሂወት ካሉ ነገሩ አይሳካም በማለት በድብቅ ስማቸው ወደ ወያኔ መሪዎች በየእለቱ በማስተላለፍ ለክፉ ሞት ዳረጉዋቸው ። የህ.ወ.ሓ.ት . መሪዎች አሁን የገጠማቸው ክሽፈትና ወርዴት አጠፋውን ለመመለስ ዝግጅታቸው አሰቀመጡ ፤ ቀደም በማለት

_በትግራይ ሕብረተሰብ የአፈና ዘዴ በመጠቀም አነስተኛ ሀይል አፋኝ ጉጅሌ በማደራጀት ክፉና አረመኔው ጨካኞች      አፋኝ ftድን ብሶስት አቅጥጫ ተሰማራ። ይህ ጊዜም በ1969 ዓ.ም. ወደ መጨረሻው አከባቢ በሶስት አቅጣጫ በማሰማራት     1. ወልቃይት ውስጥ፣ 2. ጠለምት፣ 3. ጠገዴ ውስጥ፤ ሲገft ፣ ጉጅሌቸው ይዘው በሶስቱ ቦታዎች ተሰማርተው ቀደም ሲል ከመኮነን ዘለለው የነበሩ የህዝብ ግኑኝነት መሪነት በድብቅ በዘዴ የተቃወሙት የሰሜን ጎንደር አማሮች አንድ በአንድ በተናጠል እያፈኑ ሰውን መልቀም ጀመራ የታፈነው

 

ሓለዋ ወያኔ ገብቶ ይገደላል ፣ ወንድ፣ ሴት ተገደሉ። ሃብት ንብረታቸውም እየተወረሰ ዝርፍያው ቀጠለ ቀስ በቀስም የጀመሩት ጥቃት ቀጠለ ።

ተ.ሓ.ህ.ት.ለ1ኛው ጉባኤ ይዘጋጅም ስለነበረ 1ኛ ጉባኤው የካቲት 5 ቀን  1971 ዓ.ም. ዓዲ ዳዕሮ አካባቢ ማይ አባይ በተባለው ቦታ ተካሂዶ የአመራር ቦታ ለውጥም ተደረገ በዚሁ መሰረት እንደሚከተለው ተደላደሉ ። በዚሁ ጉባኤ የተመረጡ አመራር ። አምስቱ የቆዩ ፖሊት ቢሮ ( ሥራ አስፈጻሚ ) እንዳሉ ተመልሰው ሥልጣናቸው ሲይዙ ቀሪዎቹም ዝርዝሩ እንመልከት ።

1ኛ    አረጋዊ በርሂ        ወታደራዊ አዛዥ                  ፖሊት ቢሮ

2ኛ ስብሃት ነጋ         የህ.ወ.ሓት ሊቀ መንበር           ፖሊት ቢሮ

3ኛ ግደይ ዘራፅዮን     የህ.ወ.ሓ.ት ም/ሊቀመንበር     ፖሊት ቢሮ

4ኛ አባይ ፀሃየ           የፕሮፓጋንዳ ክፍል ዋና ሃላፊ    ፖሊት ቢሮ

5ኛ ስዩም መስፍን     የውጭ ጉዳይ ዋና ሃላፊ            ፖሊት ቢሮ

6 ገብሩ አስራት                                              ማእከልይ ኮሚቴ

7 መለስ ዜናዊ          የፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ም/ሃላፊ        ማእከላይ ኮሚቴ

8 አስፍሃ ሓጎስ                                                 ማእከላይ ኮሚቴ

9 አርከበ (ዮሓንስ )እቁባይ                                   ማእከላይ ኮሚቴ

10 ፃድቃን ገብረተንሳይ                                         ማእከላይ ኮሚቴ

11 ስየ አብርሃ                                                    ማእከላይ ኮሚቴ

12 አታክልት ቀፀላ                          ማእከላይ ኮሚተ  ግንቦት ወር 1971 ዓ.ም በስብሃት ነጋ በአባይ ፀሃየ እንዲሁም በመለስ ዜናዊ የተገደለ ። ገዳይ ሳሞራ (መሓመድ ) የኑስ በሲሞኖቭ ባልር መነጽር ጠመንጃ ።

13 ዘርአይ አስገዶም                                               ማእከላይ ኮሚቴ

14 አውዓሎም ወልዱ                                                ማእከላይ ኮሚቴ

15 ተወልደ ወ/ማርያም                                              ማእከላይ ኮሚቴ ብዙም ሳይቆይ በህመም ምክንያት ሱዳን ሂዶ 1975 ዓ.ም የተመለሰው ።የነዚህን ስም ዝርዝር ያስቀመጥኩበት ካለ ምክንያት አይደለም ፤በአማራው በትግሬው ፤ በአማራው የዘር ማፅዳት ከባድ ወንጀል ፈፅመዋል ፤አማራው ያፈራው ሃብት ንብረት ወ.ዘ.ተ. መርፌም ሳትቀር ለህ.ወ.ሓ.ት ውርስ ብለው የህዝብ ሃብት ንብረት የዘረፉ የአማራው ህዝብ የገደሉ ፤ የግድያውም ቀንደኛ ተባባሪዎችን ፈፃሚዎች የነበሩ ናቸው ። እነዚህ ተሰባስበው ነው በንጹሃን ዜጎች ላይ እልቂትና ሶቆቃ እያደረሱ  የመጡ ፤ ስለዚህ ከአምስቱ ፖሊት ቢሮ ስድስተኛው መለስ ዜናዊ አብረው የሚጠየቁ የሚከሰሱ ናቸው ። የሰሜን ጎንደር ህዝብ በአረጋዊ በርሄ የሚመራው የህ.ወ.ሓ.ት ሰራዊት ቀሪው አራቱ ፖሊት ቢሮ በየቦታው ተሰማርተው ተዛዝና አመራር በምስጠት ማእከላ ኮሚቴውም የበልጥ በዘር ማጥፋቱ የተሰማሩ ፤ 1 አዋአሎም ወልዱ 2  ስየ አብርሃ  3 መለስ ዜናዊ ከስየ አብርሃ ተደራቢ በመሆን  4 ዘራይ አስገዶም 5  ፃድቃን ገብረ ተንሳይ      6 ገብሩ አስራት 7አርከብ እቁባይ     8  አስፍሃ ሓጎስ እነዚ ደግሞ በየተዋጊው ሰራዊት ተመድበው ተእዛዝ በመጠት በአማራው ላይ ጥቃት በመክፈት የአማራ የዘር ማጥፋት ከባድ እርምጃ ነዋሪው አማራ ሊቋቋመው በማችል ሁኔታ ሰላማዊው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ዘሩን ለማጥፋት ያለው የሌው ሃይላቸው አጠናክረው የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ማለት 1 አረጋዊ በርሄ 2        ግደይ ዘራጽዮን                                                   3 ስብሃት ነጋ                    4 አባይ ጸሃየ  5 ሥዩም መስፍን 6  መለስ ዜናዊ  በሰሜን ጎንደር አማራ በትንሹ ከ1969ዓ.ም. የጀመረው ጥቃት በክፉ መልኩ ተጠናክሮ ከታህሣስ ወ 1972 ዓ. ም.የተጀመረው የአማራ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እስከ 1977 ዓ .ም

.በዋናነት ወንጀሉ የዘር ማጥፋት በአማራው የፈጸሙ ዋናዎቹ እነዚህ ናቸው ። በዚሁ የወያኔ ጥቃት ከ2ሚልዮን በላይ ነብሰ ጡር አራስ ህፃናት ሽማግሌዎች ወጣቶች ወንድ ሴት ልዩነት በሌለው በወያኔ እጅ ተገድለዋል ፤ አገዳደሉም ንበተለያየ ዘዴ ተፈጽሞባቸውል ፤ቀሪው ለስደት ተዳረግ ፤የመጣ ይምጣ ክቤትየ ወጥቸ አልንገላታም ያለም አለ ።

ከማ.ገ.ብ.ት ምስረታ እስከ የካቲት ወር 1967 ዓ.ም. የማገብት ሊቀ መንበር ፤ ቀጥሎም በትግሉ ሜዳ ከየካቲት ወ ር 11ቀን  1967 ዓ.ም እስከ የካቲት ወር 1971ዓ፣ም ሊቀ መንበርና ወታደራዊ አዛዥ  የነበረው አረጋዊ በርሄ

 

ነው። በምን ምክንያት ሊቀ መንበርነቱን ለቀቀ ለሚል ጥያቄ አጭር መልስ ። አረጋዊ በርሄ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ ገና ጉባኤው ሳይገባ ሶስቱ እየተደበቁ ያደረጉት ስምምነት ነበራቸው ። ድርጅቱን በሞኖፖል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸው ሶስቱን የተስማሙበት አረጋዊ ሊቀመንበርነቱን ለስብሃት ነጋ ሊሰጠው አረጋዊ በወታደራዊ አዛዥነቱ እንዲወሰን መለስ ዜናዊ የማርክሲስት ሌኒንስት ፤ በሌኒናዊ መርሀ ግብር የካድሬዎች አሰልጣኝና አደራጅ ኮሚሽን እንዲሆን በተስማሙት መሰረት 1ኛው ጉባኤው ተካሂዶ 15 አመርር ተመርጠው የሥራአስፈፃሚው ምርጫ በሚመረጥበት ጊዜ በሁሉም በሙሉ ድምጽ የተመረጠው አረጋዊ በርሄ የህ.ወ.ሓኣዓ.ት ሊቀመንበር ሲመረጥ ብሞትም አልቀበልም ስብሃት ነጋ ነው ብቁ ለሱ ይስጠው ብሎ አንገቴን ለካር አለ፤ የተመረጡ አመራር ስብሃት ለዚሁ ብቃት የለውም እባክህ ተቀበለን ቢሉቱም በፍፁም አልቀበልም በማለቱ ለስብሃት ነጋ ሰጡት መለስ የተሰጠው ቦታ አደላድሎ ያዘ አረጋዊም ድሮም የራሱ የነበረው ወታደራዊ አዛዥነቱን ያዘ ፤ቀሪው በየቦታው ተደላደለ ።በአጭሩ ነው የገለፅኩት እንጂ ብዙ ታሪክ አለው ፤ለወደፊቱ ራሱን በቻለ አረእስት ለህዝብ አሳውቃለሁ ፤ለአሁኑ ይህ ይበቃል ። አረጋዊ በርሄ ደግሞ በታጋዩ እንዲጠላ እንዲናቅ ያደረገው ዋናው ይህ ነው ። ስብሃት ነጋ ማለት ኧምሮው የዞሮበት ደፍድፍ ደንቆሮ ገዳይ ጨካኝ አውሬ ነው ። ህወሓት ከኢህአፓ ጦርነት ስለአጋጠመው ደፍሮ ሰሜን ጎንደር ሕዝብ ለማጥቃት ሁኔታውና ጊዜው አልፈቀደለትም ነበር። ከኢህአፓ ጋር በተካሄደው ጦርነት ኢህአፓ ጥቃት ደርሶበት ሴሜን ጎንደርን ለቆ በመውጣቱ ምክያት ህወሓት በአረጋዊ በርሄ ወታደራዊ አዛዥ የሚመራው የወያኔ ሰራዊት ጠቅላላ ወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት( ‘ሰሜን ጎንደር’) በመውረር ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጸመ። ስብሃት ነጋ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀህየ፣ ስየ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን መለስ ዜናዊ እነዚህ አመራር ሰዎች የወያኔው ሰራዊት ተከፋፍለው በመያዝ ሰሜን ጎንደር የንጹሃን ዜጎች አማራ የሬሳ ክምር መሬት አደረጉት። እነዚህ ሁሉ አመራር በቀጥታ ትእዛዝ የሚቀበሉት፣ የሚንቀሳቀሱት፣ ጥቃት የሚፈጽሙበት ቦታዎች ከአረጋዊ በርሄ በሚሰጣቸው መመሪያ ነበር። በዚሁ ጊዜም ተጨማሪ (06) ሃለዋ ወያነ በስፋት እንዲዘጋጁ አመራሩ ስላመነበት በምክትል ሊቀመንበሩ ቁጥጥር እንዲዘጋጅ ፣ ምክትል ሊቀመንበሩ ግደይ ዘርአጽዮን ተጨማሪ                                                         ሃለዋ ወያን ከመሬት በታች1 2 ሜትር ጥልቀት ትንሽ ጠባብ መስኮት 150 እስከ 200 እስረኞች የሚይዙ ሆነው እንዲሰሩ ወስኖ የነበሩትም እንዲሰፉ አድርጎ አሰራው ። የሚሰሩበትም ቦታዎቹም ፣ ግህነብ ( ቃሌማ )፣ ፍየል ውሃ፣ ባኽላ ሳምረ፣ ሱር እስር ቤት ሲሆን፣ እንዲሰፋ አዲ በቅሎ፣ ወርዒን ፃኢ ጨምሮ በስፋትና በብዛት ከመሬት በታች ሃለዋ ወያኔ ተሰሩ። በዚሁ ጊዜ አማራዎች፣ ሽማግሌ፣ ወጣት፣ ህፃን፣ ሴት፣ ወንድ ሳይለዩ ወደነዚህ ሃለዋ ወያኔ እየታፈሱ ታጋዙ። እዛው እንደገበም በተለያዩ የጭካኔ ግፍ ተገደሉ። በጢስ እየታፈኑ የሞቱት አማራዎች ብዙ ናቸው። በጅላ ጉድጓድ በጥይት እየተደበደበ ያለቀው አማራ ብዙ ነው። ወህኒ ቤት በገባው ተላላፊ በሽታ፣ ኮሌራን ሌላ በሽታዎች በመተላለፍ ሕዝብ አለቀ። በቶርቸር በመርዝ በእሳት የጋለ በረት ወደ ሆዱ በመክተት አሰቃይተው ንጹህ ኢትዮጵያዊ ዜጋ አጠፉት ። የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች በአማራው ያልፈጸሙት ግፍ የለም ። እነዚ አረሜኔ ግፈኞች በአንድ ህዝብ ላይ አማራ ጠላታች ብለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ አካሂደዋል የሞተም በሂወት ያሉትና የሞቱትም እንደነ መለስ ዜናዊ በከባድ ወንጀል 1 ዘር በማጥፋት 2 ሃገር ለባእዳን መሸጥ (ለሱዳን ) 3 የመሬት ወረራ መፈጸም (ሰሜን ጎንደር ሰሜን ወሎ ) የታላቅዋን ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ የትግራይ መንግሥት ማስፋት የሌላው ክፍለ ሃገር ለምና ሰፊ መሬት በመንጠቅ የህዝft ማንነት ባህሉ ወጉ ፀረ ዲሞክራሲ ፀረ ህልውና በመሆኑ ከባድ የወንጀል ተግባር ነው ። አሁንም ህ.ወ.ሓ.ት በዚሁ እየቀጠለበት ሲሆን እንዲያውም በከፋ መልኩ በግማሹ ወደ ትግራይ በማካለል ግማሹ ለሱዳን መንግሥት በመሸጥ በአማራው ላይ የሚፈጸመው ግፍ ወያኔው አባብሶታል ። በአማራው እየተፈጸመ ያለው ግፍ አማራን ብቻ የሚመለክት አይደለም የሁሉ ኢትዮጵያዊ ጥቃት ነው ፤ አማራው ዘሩ ሲጠፋ አማራው ብቻ አይደለም ዘሩ የሚጠፋው ያለ ሁሉ ኢትዮጵያው ነው ዘሩ የሚጠፋ ያለው ፤የጎንደር ለምና ሰፊ መሬት ለሱዳን እየተሸጠ ያለው የጎንደር ብቻ አይደለም የሁሉ ኢትዮጵያዊ ነው የኢትዮጵያ ባለታሪክ ቦታዎች ቴድሮስ በመቅደላ ዮሃንስ በመተማ እምቢ ለጠላት ብለው የተሰዉበት መሬት ወያኔ ለኢትዮጵያ ዝህብ ጠላት ለሆነው የሱዳን መንግሥት አሳልፎ መሸጥ ታሪካችንም አሳልፎ እየሸጠው የገኛል ፤ስለሆነም የጎደር ህዝባዊ ትግል የሁሉ ኢትዮጵያዊ ተልም ነው ፤አብረን ተባብረን የምንታገልበትም ጊዜው አሁን ነው ። ጎንደርና ትግራይ ፤ጎንደርና ሲዳሞ ፤ ጎንደርና ሓረር ፤ ጎንደርና አፋር ፤ ዶንደርና አኦጋዴን ፤ ጎንደርና ጋምቤላ ፤ ወ.ዘ.ተ ምንም ልዩነት የለንም ፤ሁላችን የኢትዮጵያ

 

ልጆች ነን ፤ ኢትዮጵያ የሁላችን ሃገር መመክያ ናት ፤ሁላችን ሃገራችን ከወያኔው ፋሽሽት ስርአት ከሃዲ ባንዳ ተባብረን ኢትዮጵያን እናድን ።

የወልቃይት ፤ ጠገዴ ፤ጠለምት ፤ሌላውም አማራ በህ.ወ.ሓ.ት. ፤የወረደበት ከባድ የጥቃት ዘመቻ በዝምታ ወይም እየተገደለ አልቀረም ፤ተወልዶ ያደገበት የትውልድ ቦታው ስለሆነ መግቢያው መውጫው   ስለሚያውቀው

፤መሳሪያ ያለው ታጥቆ ፤የሌለው በቤቱ ያገኘው ጎራዴ ፤ፋስ ፤ ገጀራ ፤ወ.ዘ.ተ. እናቶች ወጣት ሴቶች ወንድም ሳይቀር በርበሬ በመያዝ ወያኔን በሚገባ በሁሉ አቅማቸው ገድለዉታል አጥቅተዋል ፤በአንዳንድ ቦታዎችም ሙሉ በሙሉ ለማለት የሚቻለው የወያኔ ሠራዊት ደምሠዉታል ፤የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በታሪክ የተመሰከረለት አርበኛ ተዋጊ ፤ሙሉ ወኔ ያለው ህዝብ ከመሆኑ የተነሳ ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት.እንደፈለገው ኢትዮጵያን እንዲያፈርስ ህዝብ ሊበታትን በደም ሊያቃባ እድል አልሰጠዉም ፤የወልቃይት፤ ጠገዴ ፤ጠለምት ህዝብ ቆለኛም ደገኛም ህዝብ ነው ፤የመሬቱ ነፋስ የተስማማ ከመሆኑ የተነሳ ወያኔ ይህ ህዝብ በቀላሉ ሊያጠቃው ጠራርጎ ሊያባርረው አልቻለም ።ሌላው አማራ ቶሎ ብሎ በመቻኮል ወደ በቀል አርምጃ አይሸጋገርም ፤ከተነሳ ግን ወደ ኋላ አይታጠፍም ፤በአማራ ጥርስ የገባ ጠላት የመጨረሻ እጣ ፈንታው ውድቀት ምርኮ ናት ።አማራ ለኢትዮጵያ አንድነት ለኢትዮጵያ ሏላዊነት ዋልታና ማገር ፤ ፤የሃገሩ ድንበር በመጠበቆ ፤ የእስልምና ፤የክርስትና ሃይማናት ባለቤት በመሆኑም እነዚህ ሁሉ ተዳምረው በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ህዝብ ፤ በባንዴራው አረንጓዴ ፤ብጫ፤ቀይ የሚኮራ ህዝብ ነው ፤ይህ አማራ የሚባለው ህዝብ ዘሩን ካልጣፋ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር በአፄ ምኒሊክ የተፈጠረች ከተፈጠረችም ከ100 ዓመት ያነሰ ዕድሜ ታሪክ አልባ ሃገር ከዓለም ካርታ ለመፋቅ አይቻልም ፤ብሎ የተነሳው የባእዳን ቅጥረኛ ባንዳ ወያኔ ፤የአማራው ወኔ ጥንካሬ ጀግንነት አይቶታል አሁን እያየው ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ት አማራውን ሲያጠቃ አብሮም የተጠቃው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ክርስትናም ነው ፤ ቀደም ሲል ብ1971 ዓ ም በአኩሱም አውራጃ እንዳባ ጴንጦሌን (ብዙ አክሱማዊም እንዳባ ፍሬሚናጦስ ) እያለ የሚጠራው ከአክሱም ከተማ የ5 ኪሎሜትር ርቀት ያለው አካባቢው የሚጠራበት ስም ደግሞ እንዳየሱስ በተባለው ቦታ ጥንታዊው ገዳም እንዳ አባ ጴንጦለን ብዙ ጥንታዊ ቅርሶች ብዙ ጥንታዊ የታሪክ መጻህፍት ጥንታዊ የብራና ጽሁፎች የሚገኝበት ገዳም ለመዝረፍ ህ.ወ.ሓ.ት በሰነዘረው ጥቃት ሳይሳካለት ቀረ ፤ቀጥሎም በአድዋ ውስጥ የሚገኘው እንዳሥላሴ ገዳም ቢሞክርም አልተሳካለትም ይህ ኦፐረሽን የተመራው በአረጋዊ በርሄ ነበር ፤ቀጥሎ ወያኔ የዘመተው ወደ ዋልድባ ገዳም ፤ በዚሁ ገዳም ተልእኮው ሙሉ ለሙሉ ተሳካለት በህ.ወ..ሓ.ቱ ሊቀ መንበር ስብሃት ነጋና በህ.ወ.ሓ.ቱ ም/ሊቀመንበር ግደይ ዘራጽዮን መሪነት ዋልድባ ገዳም ሙሉ በሙሉ ተዘርፈዋል በዙ ብጿአን ባህታውያን፤ ቀሳውስት፤ አባዎች ተገድለዋል ታሪካዊ ቅርሶች መጻህፍት ብራናዎች ሃብቱ ንብረቱ ወ.ዘ.ተ. ተዘርፈዋል አሁንም ዋልድባ ገዳም እየተጠቃ ይገኛል ባለታሪክ ጥንታዊ ገዳም እየወደመ ለህልፈቱም ገደል አፋፍ ነው ያለው ፤ ይህ ገዳም አማራን ብቻ አይመለከትም የሁሉ ኢትዮጵያዊ ነው

፤ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይና ዋልድባ ገዳም በሚል ርእስ ለሁሉ ኢትዮጵያዊ ስለ አሰራጨሁት የዚሁ ቅዱስ ዋልድባ ገዳም በህ.ወ.ሓ.ት. የደረሰበትና እየደረሰበት ያለው ጥቃት በዝርዝር ስለፃፍኩት ጽሁፉ በየዌብ ሳይቱ ስለሚገኝ እዛው ፈልገን እንመልከት ።

 

በአማራው የተፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ደግሞ ከሁሉ የከፋ በአርከበ እቁባይ፣ ዘርአይ አስገዶም፣ ሳሞራ የኑስ፣ ታደሰ ወረደ፣ ሃየሎም አርአያ ወዘተ የሚመሩ የገዳይ ftድን ሕዝftን እየሰበሰft በሳር ቤት ውስጥ በማስገብት ቤቱን በእሳት በማቃጠል ያለቅው ሰው ቁጥር ብዙ ነው። እኔ ራሴ ያየሁት አርከብ እቁባይ 12 ቤተሰቦችን ሰብስቦ በገዛ ቤታቸው፣ አባት፣ እናት፣ ልጆች፣ የተዳሩ ሴቶች ልጆቻቸውን ጨምሮ ከነህፃናቱ ሰብስቦ ሳር ቤት አዳራሽ አስገብቶና ቤቱን ዘግቶ እሳት ለቀቀባቸው። ሁሉም ቤተሰብ በእሳቱ አለቁ። በዚሁ በሰሜን ጎንደር የተካሄደው የዘር ማጥፋት ወንጀል በተጨማሪ ሁሉም ንብረታቸው ሃብታቸው፣ በሬ፣ ላም፣ ፍየል፣ በግ፣ አጋሰስ ጠቅላላ የቤት እንሣት ሁሉ በህወሓት ተዘርፈው ተወርሰው ተወሰደዋል ።

 

ከ1972 ዓ.ም. ታህሳስ ወር ይህ ሁሉ ጥቃት የተጀመረው አጠቃላይ የጠገዴ፣ ጠለምት፣ ወልቃይት አማራ ዘሩ ሲጠፋ ቀሪው ደግሞ ወደ ሱዳን ተሰደደ፤ ጫካ ውስጥ ገብቶ ፀረ ወያኔ በሽምቅ ውጊያም የተሰማራ ጥቂት

 

አልነበረም፤ ህዝብም ባገኘው መንገድ ሁሉ ወያኔን ከማጥቃት አላቆመም ፤ የወልቃይት ፤ጠገዴ ፤ ጠለምት ፤ ሴቶች በርበሬ በትንሽ ከረጢት ቋጥረው ከወገባቸው አትለይም በቤታቸው ውስጥም የተዘጋጀ አለ የወያኔ ታጋይ በመንገድ ሲገኙት አቁመው ለማነጋገር በመሰለ መልኩ ከያዝዋት በርበሬ ዘግነው በማውጣት አይኑ ላይ በመርጨት እዛው ሲደናበር መሣሪያ ማርከው ብዙ የወያኔ ታጋይ ገድለዋል፤ወደ ቤታቸው የሚመጣ ታጋይ ምበርበሬ በውሃ በጥብጠው የሚበላ የሚጠጣ አቅርበው ደህና ነው ብሎ ሆዱን ሲሞላ ፤የበጠበጡት በርበሬ አይኑ ላይ በመድፋት የታጠቀው መሳሪያ ማርከው ታጋዩም በድምፅ አልባ መሳሪያ ይገድሉታ በዚሁም ተገድሎ የጠፋ የወያኔ ታጋይ ብዙ ነው     ። በ1973 ዓ.ም . በተለያየ መንገድ የተገደሉ ከማስታውሳቸው ውስጥ ፤ በህዝብ ግኑኝነት የነበሩት ፤ አለማዮህ ፤ ብርሃነ ፤ ፍስሃ ፤ገብረተንሳይ ፤ ነጋሽ ፤ አማረ ፤ ደስታ ; ብዙ ተገድለዋል የጠቀስኩት ከማውቃቸው ነው ።በወያኔ ታጋይ ሰራዊትም በተለያዩ መንገዶች በህዝft የተገደሉም ብዙ ናቸው ከማስታውሳቸው ለመጥቀስ ገብረ ሥላሰ ፤በላይ ፤ ፍጹም ፤ካህሳይ ፤ ነጋሽ ፤ ገረግዚሄር ፤ አባይ ፤ አበበ ፤ ጸጋይ ፤ የሚባሉ ህዝftን ለመግደል በftድን በftድን ተከፋፍለው ሲንቀሳቀሱ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብም በየጫካው ተደብቆ በማድፈጥ የገደላቸው እነዚህን አስታውሳለሁ። የወልቃይት ፤ጠገዴ ፤ጠለምት ህዝብ የሚቻለው ሁሉ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ህ.ወ.ሓ.ት. ወያኔን ከማጥቃት ባለው መሣሪያ እየተጠቀመ ወደ ኋላ ሳይል ጀግንነቱን ያስመሰከረ ፤ያሳየ ህዝብ ነው ። እኔ ባለኝ እምነት ይህ ኩሩ ጀግና ህዝብ ከወያኔ ፋሽሽት ቅኝ ገዢ አረሜኔ ስርአት እየታገለ የመጣው ያለኘ እምነት እውነትም የኢትዮጵያ መድህን ጠባቂም ነው

። ተስፋ ሳቆርጥ ከ1972 ዓ ም . አንስቶ እስከ ዛሬዋ ዕለት የማንነት ጥያቄው አድማሱን በማስፋት ወያኔ በማጥቃት ተሰማርቶ ይገኛል። በመሬቴ ላይ እሞታለሁ እንጂ ትወልድ ቦታየ አለቀም ያለው በ1969 ግንቦት ወር የተጀመረው ጥቃት እስከ ዛሬ ድረስ ቀጥሏል። ይህ የሰሜን ጎንደር ህዝብ በወያኔ እየሞተ እየተገደለ ማንነቴን አሳልፌ አልሰጥም ብሎ 42 ዓመት ሙሉ ከተሓህት-ህወሓት ዘራችንም ብታጠፉ አንድ ሰወ እስኪ ቀር ማንነታችን አሳልፈን አንሰጥም እኛ አማራ ጎንደሬች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም ብሎ እስከ አሁን ድረስ በማንነቱ የማይደራደር ማንነቱን አሳልፎ የማይሰጥ ኩሩ ኢትዮጵያዊ አማራ ነው ። በምሬት እየታገለ የሚገኝ የጎንደሩ ህዝብ ከቀን ወደ ቀን ጥንካሬው በግልጽ እይታየ ነው ። የአማራው ህዝብ በየትም ቦታ የተገኘ አማራ እንዲ ገደል ያወጀው ህ.ወ.ሓ.ት. በ1969 ሲሆን፣ በትግራይ ውስጥ የሚኖሩ አማራዎችም ከየቦታው እየተለቀሙ እንዲገደሉ አምስቱ የተሓህት አመራሮች፣ አረጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፈን፣ ስብሃት ነጋ፣ ትግራይ የትግራዮች እንጂ የሌላው መጤ ቦታ አይደለችም፣ ስለሆነም ማንም የትግራይ ተወላጅ ያልሆነ ከትግራይ ይውጣ ተብሎ ታወጀ። በአዋጁ መሰረትም አማራው በነቂስ እየተፈለገ ተገደለ፣ እነዚህ ይህ ውሳኔ የተላለፈባቸው ከትግራይ ተጋብተው ልጆች ወልደው ያሳደጉም ናቸው ፤ ያመለጠውም ሂወቱና ቤተ ስቦቹን ይዞ የሸሸም ብዙ ነው ።ይህ የተመለከተና ያየ የትግራይ ህዝብም ፤ወያኔን አወገዘ ፤መሬታቸው ነው አይወጡም ይህ የኢትዮጵያ ቦታ ነው ፤ማነው ወጪ ማነውስ አስወጪ ፤ከፈለጋቹህ ወያኔዎች ውጡ እያለ ከአማራው ወንድሙ ቆመ ። በየቦትው ፀረ ወያኔ እንቅስቃሴ ተነሳ

፤ወያኔም በየ ቦታው ፤ ይህ እንቅስቃሴ የታዩባቸው በህዝብ ግኑኝነቱ በፀረ ወያኔ ፖሊሲ ተንቀሳቅሰዋል ያላቸው የትግራይ ሰዎች አንድ በአንድ እየለቀመ ሓለዋ ወያነ በማስገባት ደብዛቸው አጠፋቸው ፤ጠፍተዉም ቀሩ ።

 

ተሓህት-ህወሓት ይህን ሁሉ በሰሜን ጎንደር አማራው ህብርተሰብ ላይ ይህን ሁሉ ግፍ ሲፈጽም እጃቸውን ለወያኔ የሰጡ የኢህአፓ አባላት የነበሩ፤ ታምራት ላይኔ፣ አዲሱ ለገሰ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ በረከት ስምኦን፣ ዮሴፍ ረታ፣ መለሰ ጥላሁን፣ ህላዊ ዮሴፍ፣ ታደሰ ካሳ፣ ሙሉአለም አበበ፣ ወዘተ ይገኙበታል። ከወያኔ ህወሓት በመተባባር የሰሜን ጎንደር፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት ወዘተ።የቀድሞዎቹ ኢ.ህ.ዴ.ን በህ.ወ.ሓ.ት አምሳልና ftራኬ ተጠፍጥፈው የተሰሩ ተላላኪዎች የዛሬዎቹ ብአዴን አካባቢው ለብዙ ጊዜ የቆዩበትና የሚመሩበት ስለነበሩ ሕዝftን በነቂስ ስለሚያውቁት አካባቢ እየመሩ ለወያኔ ጥቃትና የዘር ማጥፋት ወንጀልም ተባባሪ ሆነዋል። ወያኔን እየመሩ የሰሜን ጎንደሬውን አማራ አጥቅተውታል። ስለሆነም በማራው ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ወንጀል በተለያዩ የጥቃት ዘዴዎች በህወሓት የተፈጸመው እነዚህ የብአዴን አመራር ከህወሓት አመራር ጋር አብረው ተጠያቂ ናቸው።

 

በሕዝብ ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ፤ሃብት ንብረት ዘረፋ ፤ለሚደርሰው ማንገላታትስላማዊ ዜጋው ተይዞ ለእስር የሚዳረገው በሕዝብ ግንኙነት በኩል ጥናትና ሪፖርት ነው ። መኮንን ዘለለው ለመጀመሬያ ጊዜ በህ.ወ.ሓ.ት በኩል ወደ ወልቃይት ጠገዴ የተሰማራው እሱ ነበር የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ግን አልተቀበለውም ሪፖርቱ ሲያስተላልፍም ሁሉም ፀረ ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት ናቸው በማለት ከነስም ዝርዝራቸው ለወያኔ ፖሊት ቢሮ ከ100 በላይ ሰዎች ሴቶችም አሉበት ቀስ በቀስ አንድ በአንድ ብስራት አማረ በሚመራው አፋኝ ftድን ተለቅመው በftምበትና ሱር ሓለዋ ወያነ ገብተው ጠፍተዋል ፤ንብረታቸውም ሙሉ በሙሉ በወያኔ ተዝርፎ ባዶ ቤት ቀረ ። የዚህ ሁሉ          ተጠያቂው ስንመለከት፣ መኮንን ዘለለው ነው፣በዚህም ላይ የሚጠየቁ መረሳ ረዳ፣ አጽብሃ ሃይለማሪያም፣ ፀጋይ በርሄ(ሃለቃ)፣ መኮንን የአዲረመጽ ሕዝብ ግንኙነት፣ አርአያ ወ/ቅነህ፣ ቅዱሳን ነጋ፣ ቀሺ ታደሰ፣ መሃሪ ግብርገርግስ ሃለቃ ታደለ አለምሰገድ ፤መብራት በየነ ፤ ወዘት። እነዚህም አንኳር ተጠያቂ ናቸው።

 

የህ.ወ.ሓ.ት.ፕሮግራም

ተሓህት-ህወሓት ገና ደደቢት በርሃ ከመውረዱ በፊት ማ.ገ.ብ.ት. ማሕበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ እየተባለ በሚጠራበት ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ ሆኖ ይጥቅሙኛል በሚላቸው ተግባራት ቢንቀሳቀስም ብዋናነት ሥራው ግን የትግሉ ፕሮግራም ወይም የትግል አቋሙን ፖሊሲ ማዘጋጀት ነበር ። ከማ.ገ.ብ.ት. መስራቶቹ ውስጥ በቂ እውቀትና ችሎታ በትምህርቱም ከፍተኛ ደረጃ በሳል እውቀትና ችሎታም ያለው አረጋዊ በርሄ ብቻ ነው። ስድስቱን ሰዎች ሰባተኛው ራሱ አሰባስቦ ማ.ገ.ብ.ት. የፈጠረም እሱ ነው ። በዚሁ የተሰባሰft ጓደኞቹ በእውቀትም በችሎታም አንፃራዊ ናቸው ፤ ሁሉም የማ.ገ.ብ.ት. ሥራን ሃላፊነትም እንዲመራ የመረጡት አረጋዊ በርሄን ነው ፤በዚሁ መሰረት 1 የፕሮግራሙ ንድፈ ሃሳብ ማዘጋጀት        2   የውጭ ሃገር መንግስታት  በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ኢምባሲም ይሁን ቆንስላ እየተገናኘ ድጋፍ ማሰባሰ እውቅናና ተቀባይነት ማግኘት የመሳሰሉ ስራዎች በሱ ብቻ ነበር የሚሰሩ ፤። የፕሮግራሙ ዝግጅት የተጀመረውን ገና ማህበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) ተብሎ መስከረም ወር  1967 እንደተመሰረተ። መስራቶቹም ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ም/ሊቀመንበር፣ አባይ ፀሃየ፣ ፣ ስዩም መስፍን፣ ፣ ዘርኡ ገሰሰ፣ አስፍሃ ሃጎስ፣ ሃይሉ መንገሻ. ተሰብስበው ማ.ገ.ብ.ት እንደመሰረቱ የሥራ ክፍፍልም አደረጉ ሲያደርጉ በዋና ሃላፊነት አረጋዊ በርሀ ፕሮግራሙን በማርቀቅና በማዘጋጀት ሥራውን ቀጠለ። በዚሁም ተጨማሪ በኢትዮጵያ የሚገኙ የጥንት ጠላቶች ኤምባሲም ሆነ ቆንስላ እየተንቀሳቀሰ የትግራይ ሕዝብ በቅኝ አገዛዝ በአማራው መንግሥት በአሰቃቂ ኑሮ ላይ ሰለሚገኝ ታግለን ትግራይን ከአማራው ቅኝ ( ኢትዮጵያ ) አገዛዝ በትግል ነፃነታችንን ካልተጎናጸፍን የትግራይ ሕዝብ የወደፊት እጣ ተበታትኖ መቅረት ስለሆነ የናንተን እርዳታ እንፈልጋለን ብሎ መማጸኑን ሥራየ ብሎ ተያያዘው። ይህ ሰው ከደረሰባቸው ኤምባሲዎች፣ ቆንስላ ውስጥ፣ ከሱዳን፣ ግብጽ፣ ጣልያን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ሶሪያ፤ሶማሊ ( መቃድሾ ) ጎልተው ከሚጠቀሱ                                                                  እየተዘዋወረ የተስፋ ይሁንታ በማግኘት ትንሽ ገንዘብ ሲለቅም በዋናነት ፕሮግራማችሁን አሳዩን፣ በረሃ ወርዳችሁም ትግል ስትጀምሩ እንከታተላለን፤ በዚያን ጊዜም በትጥቅና በገንዘብም ጭምር እንረዳለን እያሉ የቃላት ተስፋ         ሲገftላቸው እንደነበር ይታወቃል በትግሉ ጊዜም የህ.ወ.ሓ.ት. ተስፋ በነዚህ የዓረብ ሃገራት ነበር ትልቁ ተስፋው ከ1967 ዓ.ም የገftበት ቃልም አላጠፉም በድብቅ በግልፅም እየረዱ የመጡ ናቸው ።ይህ በዚህ እንዳለ ደደቢት በረሃ እንደገftም የተዘጋጀው ፕሮግራም አጠናክረው  በማዘጋጀት በመፃፍ፤  የካቲት ወር 1968 ተሓህት በዲማ በጠራው ዲማ ኮንፈረንስ እየተባለ የሚጠራው ፕሮግራሙ ለተስብሳቢው ቀርቦ ፤ የነበረው ታጋይ ፕሮግራሙን አውገዘው ይህ ፕሮግራም ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፀረ ህዝብ አንድነት ነው ፤ትግራይ ክ/ሃገር በአክሱም ዘመነ መንግሥት የኢትዮጵያ መናገሻ ዋና ከትማ ፤የኢትዮጵያ የታሪክ ማእክል ናት ከየት የመጣ በምን መልኩ ነው የኢትዮጵያ ቅኝ ተገዥ የሆነችው ፤ ስለ ኤርትራ የምትናገሩት ኤርትራ ም የኢትዮጵያ ግዛት ናት ፤ ወልቃይት ጠገዴ የጎንደር አልወሃ ምላሽ የወሎ ነው በማለት ይህ ፕሮግራም አንቀበለውም ሲል ታጋዩ ።ነገር ግን በትእቢትና በአምባገነናዊ ትምክህት በሊቀመንበሩ አረጋዊ በርሄና ጥቂት ተባባሪዎቹ ፀድቆዋል አልፈዋል በማለት                                                         ለሕዝብ በተነው። ዘሬ ይህ በአረጋዊ በርሄ የተዘጋጀው ፕሮግራም የኢትዮጵያ ሕገ፣መንግሥት በመሆን ኢትዮጵያ አንደነትዋ እየፈረሰ

 

የገኛል። ሕዝብም ኢትዮጵያዊነቱን ተነጥቆ በዘርና ብቋንቋ ተከፍሎ ክልል በሚል ሃረግ ተወስኖ እንዲቀር ቀሰ በቀስ ኢትዮጵያዊነቱን፣ አመለካከቱን፣ አስተሳሰftን ከማላላቱም በላይ፣ አንድነቱን ያዳክማል፣ በማለት ወያኔ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተብሎ ለብዙ ዘመናት ሲጠራበት የቆየውን ‘ሕዝቦች” በሚል የተለያየ ሕዝብ እንደሆነ ገና በማገብት ጊዜያቸው የተጀመረና በፕሮግራሙ ውስጥ የተካተተ መሆኑ በገጽ X (10) ይገኛል። ክልል የሚለውም በግልጽ ቃሉን ባያስቀምጠውም ብሄር ብሄረሰቦች ተገንጥለው ራሳቸውን በራሳቸው በመወሰን ተገንጥለው የራሳቸውን መንግሥት መመስረት አለባቸው በሚለው ጽንሰ ሃሳብ የተካተተ መሆኑ ለመገንዘብ ፕሮግራሙን እንመልከት። በአሁኑ ጊዜ የሚሰሙ ውሸቶች አሉ ፤በጣም የሚገርመው ግን የአረጋዊ ብርሄ ንግግር ነው ፤ የህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም አላዘጋጀሁም በደፈና ራሳቸው ነው ያዘጋጁት ይላል ራሱ በዋናነት ያዘጋጀው የራሱ የእጅ ሁፉ ያለበት ፕሮግራም እንዴት በግልፅ ለሚታየው ነገር ይካዳል ፤ ሌላው ትግሉን ከጀመርን በስድስት ወራችን እንዲታረም ተብሎ፤ በፅሁፍ ግን ያየነው ለውጥ የለም ይላል ፤የድርግቱ ሊቀመንበር እሱ ራሱ ነው ፤ ፕሮግራሙ ያዘጋጀው ያረቀቀው ራሱ፤ ያፀደቀውም እሱ ራሱ በሚመራው ስብሰባ ፤ፀድቀዋል ብሎ ያሳለፈው እሱ ራሱ ነው ፤ይታረም ከተባለም የድርጅቱ ሊቀ መንበር ሃላፊነት ወስዶ የፖሊት ቢሮ አባሎቹ ሰብስቦ እያወያየ ፕሮግራሙ ይታረማል ታርሞም እንዳዲስ ለጉባኤ ይቀርባል ፤የነበረው ስህተት ተገልፆ ጉባኤተኛውም አስተያየት ሰጦ ሃገርና ህዝብ የሚከላከል ሆኖ ከተገኛ ያፋል ፤ካልሆነም ውድቅ ይደረጋል መሆን ያለበትም ይህ ነው ፤ይህ ሁሉ የአረጋዊ በርሄ ሃላፊነት እንጂ የሌላ አይደለም ምክንያቱ የድርጅቱ መሪ ሊቀ መንበር እሱ ብቻ ነው ። ይህ የድርጅቱ ፕሮግራም ተራ ሰነድ አይደለም በአንድ ተራ ታጋይ ወይም ማእከላይ ኮሚቴ ወይም በተራ አባል ፖሊት ቢሮ የሚሰራ አይደለም ፤ የድርጅቱ መመሪያ ነው ።አረጋዊ በርሄ የሚናገረው የኢትዮጵያ ህዝብ ንቀት መናቅ ማሳነስ ገና ከልft አልተፋቀም ፤የት ይደርሳሉ ወያኒያዊ ትእቢቱ አላስወገደም ።ይህ ሁሉ ተግባርና ሥራ የራሱ ነው የሚያስተካክለው ሌላ የለም ። ትግሉ ከተመሰረተ ጀምሮ እስከ 1977 ዓ.ም ፈላጭ ቆራጭ የነበረው አረጋዊ በርሄ ነው ፤ በህ.ወ.ሓ.ት ድርጅት ውስጥ ካለ አረጋዊ በርሄ ፍቃድ የሚሰራ ነገር የለም ፤ ደፍሮ የሚሰራም የለም ። በማ.ለ.ሊ.ት ምስረታ የመፈንቀለ መንግሥት ባልታሰበው ሁኔታ የደረሰዉም የራሱ ታማኝ ሎሌዎቹ እነ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ ስየ አብርሃ አካሄዱበት እሱና አሽከሩ ግደይ ተባረሩ ። ሲባረሩም ምንም የፖሊሲ ልዩነት አልንበራቸውም ስብሃት ነጋም በጉባኤው በማያሻማ መንገድ በጉባኤው በመካከላቸው ልዩነት ሳይፈጠር አብረው መዝለቃቸው በንግግሩ ሲያረጋግጥ ፤ይህ ንግግርም አረጋዊ እና ግደይ ተቀብለዉታል የሰጡት የተቃውሞ ምላሽ የለም ።።፤ሁሉ የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ፀረ ኢይዮጵያ ፀረ አንድነት ፀረ ህዝብ ናቸው ። አረጋዊም ሆነ ሌሎቹ ህዝብን እያታለሉ ገበናቸው ወንጀላቸው ሊደብቁ ፈፅሞ አይችሉም ፤። የንፁሃን ደም እየጮኸ ነው ። የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህ ፀረ ሃገርና ፀረ ህዝብ ከሂዲዎች የጠላት መሳሪያ የወያኔ መሪዎች ይዞ ለፍርድ ማቅረብ ግዴታውም ሃላፊነትም የህዝft ነው ፤።

 

 የህወሓት ፕሮግራም በኢትዮጵያ ላይ የፈጠረው ችግር//    

 

ፕሮግራሙ ሙሉ በሙሉ ተዘጋጅቶ ይፋ የተደረገው በየካቲት ወር  1968 ነው። ለሕዝብም ተበተነ፣ በትግራይ ሕዝብ ተቀባይነት አላገኘም። የትግራይ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ ተቃውሞታል፣ በግልጽም ተናግሯል። ትግራይን ከቅኝ ገዢው አማራ (ኢትዮጵያ) እጅ አስወጥተን ነፃ የትግራይ መንግሥት እንመሰርታለን፣ ትግራይ የኢትዮጵያ አካል አይደለችም፣አፄ ዮሃንስ ከሞቱ ነፃነትዋ ተገፎ በአማራው (ኢትዮጵያ) ቅኝ አገዛዝ ስር የወደቀች ሃገር ናት ብሎ የተነሳው ተሓህት-ህወሓት። ከኢትዮጵያ ሕዝብም መሰረትም ግኑኝነት የለውም። ከዚህ ተነስተው በእነ አረጋዊ በርሄ የሚመራው ድርጅት ዋናው የምስረታ ዓላማው ጸረ-ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነትፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት የሆነውን ፕሮግራማቸውን ዘረጉት።የዚሁ ፕሮግራም ምሶሶ ፖሊሲ ትግራይን ገንጥለው የትግራይ መንግሥት ማቋቋም ነው ።ወያኔና የኢትዮጵያ ህዝብ አይገናኙም ።

 

ወያኔ ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛቴ ስር አስገባታለሁ የሚል ህልምም ሆነ ሃሳብ እስከ 1981 አልነበረውም። አጋጣሚ ሆኖ ግን በነበረው የደርግ መንግሥት ዳካማ ስርዓት ኢትዮጵያና ሕዝቧ በወያኔ ቅኝ አገዛዝ እጅ ወደቀች። በዚህ

 

ጊዜ ይከተሉት የነበረው ፕሮግራም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕገ መንግሥት ስርዓት ሆነ። ለዚህም በምሳሌነት የወያኔን እንኳር የሕገ መንግስት ልጥቀስ፤

 

  1. የመገንጠል መብት ያረጋገጠው በፕሮግራሙ ብሄራዊ ተጽእኖ ገጽ 7 እንመልከት፣
  2. ትግራይ ነፃ ሃገር ነበረች የሚለው በመቅድም 5 እንመልከት፤ የአረጋዊ በርሄ የእጅ ጽሑፍ ። ይህ ፕሮግራም በፀረ አማራ ከመነሻው እስከ መጨረሻው ፀረ አማራ ፕሮግራም ነው፣
  3. የኢትዮጵያን ጥንታዊ የባህር በር ያሳጣት ተሓህት-ህወሓት በፕሮግራሙ የኤርትራ ጥያቄ ለሚለው አርእስቱ ግዛቷን እና የበህር በርም የሰጣት በፕሮግራሙ በገጽ 32 እንመልከት፣አሰብን ሳይቀር ወደ ኤርትራ አጠቃለሉት ።አሰብ አውራጃ የኤርትራ ሳይሆን የወሎ ጠ/ግዛት ክፍልና አውራጃ ነው ፤ በኤትራም ሥር ገብቶ አያውቅም ፤ ይህን ያደረጉበት ዋናው ምክንያት ሆን ብለው ኢትዮጵያን ለሞጉዳትና የባህር በር አልባ እንድትሆን ከኢትዮጵያ ጠላት ባእዳን ሃገራት ተነጋግረው የፈፀሙት ፤ፀረ ኢትዮጵያ ተግባር ነው ።
  4. ሕዝቦችና ክልል የሚሉትም የዚህ ፕሮግራም ጽንሰ ሃሳብ ናቸው።

 

ስለሆነም የተሓህት-ህወሓት ፕሮግራም የኢትዮጵያን አንድነትና ሉአላዊነት፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ ፍቅርና ሰላም የሚንድ ጸረ-ኢትዮጵያ ነው። ለዚህም ተጠያቂዎቹ፣ አርጋዊ በርሄ፣ መለስ ዜናዊ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስየ አብርሃና አውአሎም ወልዱ ናቸው።

ህወሓት ሰሜን ጎንደርን ብ1972 በወረረበት ጊዜ፣ በጠቅላላ ለማለት ይቻላል፣ በሬ፣ ላም፣ ፍየል፣ በግ፣ በቅሎ፣ ፈረስ፣ አህያ ከወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት ወዘተ በመዝረፍና በመውረስ፣ ከ1973 ጀምሮ ህወሓት የእንስሳ ነጋዴ ሆኖ ነበር። ገበሬዎች እየመለመለ ነጋዴ በመሆን የተሰረቁትን የተዘረፉት እንስሳዎች በትግራይ አውራጃዎች በመሸጥ ገንዘft ይህ ነው ተብሎ ባይደነቅበትም ጊዜዊው ችግሩ ይሸፍንለት ነበር ። ሌላው የዚሁ የሰሜን ጎንደር ከሰደትና ከሞት የቀረው የሰበሰበውን እህል በመቀማት ህዝft ባዶ ቤት ይዞ የቀረበበት ነው ።

 

ህወሓት በአማራና በትግራይ ሕዝብ ላይ የፈጸመው ወንጀል በሕግ የሚጠየቅበት ነው። ተገድለዋል፣ ጠፍተዋል፣ ተሰደዋል፣ ንብረታቸው ውርስ ለህ.ወ.ሓ.ት. ተብሎ ተነጥቋል። ዛሬ በሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመ፣እየፈጸመ ያለው የ ህ.ወ.ሓ.ት ፋሽሽት መንግሥት ሕዝብ በአሰቃቂ መንገድ እያንገላታ፣ እየገደለ፣ አፍኖ  እያጠፋ፣ የሃገርን ሉአላዊነት እያፈረሰ፣ ከ1600 ኪ.ሜ. ርዝመትና 100 ኪ.ሜ. ጥልቀት በላይ ያለውን የኢትዮጵያን መሬት በ1975 ዓ/ም ለሱዳን የሸጠው ጊዝያዊ ጥቅምና እውቅና በሱዳኖች አገኝበታለሁ ብሎ የኢትዮጵያ ሏላዊነት በመፃረር ለምና ታሪካዊ የኢትዮጵያ መሸጥ በከፍተኛ ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው ። ምንም በህዝብ አሜኔታ ያልተሰጠው በህዝብ የማይታወቅ የህ.ወ.ሓ.ት የማፍያና የባንዳዎች ስብስብ ፤ የራሱን ፕሮግራም በ1968 የፃፈው ያዘጋጀው ፤ የትግራይ መንግሥት ለመመስረት

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቦይ ስብሃትን ፈቶ ፤ አርበኛ ዘመነ ካሴን ማሰር - አሰፋ በድሉ

ነው ፤ ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ሆኖ ይገኛል አድርጎታልም ። ህወሓት ገና ከትግሉ መጀመሪያ ጀምሮ በሕዝብ ላይ ያወረደው ግፍና መከራ ፤ሽብር አሁንም የሚወርደውን ግፈኛው አገዛዝ በባሰ መልኩ ቀጥሎበት ፤መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እያሰቃየ የሚገዛ ያለው በዚሁ ፕሮግራሙ ነው ፤ ስለሆነም ይህ ድርጅት ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ሽብርተኛ በሽብርተኛነቱ ተደራጅቶ በግልፅም በስዉር ህዝብ አጥቅተዋል ። ለዚሁ ምስክርነት የሚጠቅሙ አብነቶች ማንሳት እንችላለ ፤

1ኛ ከ1969 ዓ.ም ግንቦት ወር ጀምሮ ፈዳያን ይህ የአረብኛ ቃል ሲሆን ትርጉሙም አጥፍቶ ጠፊ ማለት ነው

፤ወደ እንግሊዝኛ ሲተሮጎም ደግሞ TERIORRIST ማለት ነው ፤የዚሁ የአጥፍቶ ጠፊ ftዱኝ መሪ ብስራት አማረ የተባለው ወኝጀለኛ ነው ፤የዚሁ ማስረጃም ፍኖተ ግድል › ብሎ ፀረ ኢትዮጵያ በጻፈው መፅሃፍ ፈዳያን በሱ የሚመራው አጥፍቶ ጠፊ በሰላማዊ ሰዎች የፈጸመው ጥቃት በገፅ 172፤ 173 ፤ በጽሁፍ ማስረጃ በማያሻማ ሁኔታ ገልፆታል ፤መፅሃፉን ፈልገን እንመልከት ።ይህ ደግሞ አንድ ድርጅት ሽብርተኛ የመሆኑ ቀዳሚ ማስረጃ በመሆኑ ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. ሽብርተኛ፡ድርጅት ነው ።

 

2ኛ ዘር ማጥፋት በአፈና ፤በግድያ ፤በጢስ አፍኖ መግደል ፤በጋለ ብረት ወደ ሆድ እቃው አስገብቶ መግደል

፤በመርዝ በሚጠጣው ውሃ ፤በሚበላው ምግብ ጨምሮ ሰላማዊ ዜጎች መግደል ፤እርቃኑን ወንድ ሴት ከግንድ አጣብቀህ ቀን በጽሃይ ለሊት በብርድ ለ48 ሳአት አስረህ የሰው ፍጡር ነብስ ማጥፋት ፤በብልቱ 10 ኪሎ ግራም አሸዋ አስረህ ማንጠልጠል ለረጅም ሳአታት በሴትም በጡቶችዋ ማንጠልጠል ፤ወ.ዘ.ተ. እነዚህ ሁሉ የአንድ ሽብርተኛ ተግባራት ናቸው ፤በዚሁ መሰረት ህ.ወ.ሓ.ት. ከአፈጣጠሩም ሸብርተኛ ነው ።እነዚህ የተገለጹ የሽብር ተግባራት በተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. የተጀመሩት ብ1969ዓ.ም. ftምበት (ሸላሎ )በነበረው ሓለዋ ወያነ በም/ሊቀ መንበሩ በግደይ ዘራጽዮን መሪነት ተግባራዊ የተደረጉ ሲሆኑ ም/ሊቀ መንበሩ ባለው ሃላፊነትና ሥልጣን መሰረት ጠቅላላ የተ.ሓ.ህ.ት.–ህ.ወ.ሓ ት. ሁሉ ሓለዋ ወያነ (06 ) የምርመራ ስራቸው በዚሁ እንዲሆንም ትእዛዙ በማስተላለፍ የህ.ወ.ሓ.ት. የምርመራ ቶርቸር በዚሁ ቀጠለበት ።

3ኛ ይህ በብዙ አማራዎች የተፈጸ ነው ፤በተገኘበት አጋጣሚ ስል በሆነ ገጀራ አንገቱን ቆርጠህ መጣል ፤ወይ በሳንጃ ሆድ እቃውን በጣጥሰ ገድለህ መጣል የጅብ እራት እንዲሆን ማድረግ ፤ይህ በብዛት የታየበት ቦታ ፍየል ውሃ ውስጥ የሚገኘው ሓለዋ ወያኔ አካባቢ ዓዲበቅሎ በሚገኘው ሓለዋ ወያኔ አካባቢ ሲሆን የዚሁ ዋና ሃላፊው አባይ ጸሃይ ሲሆን መክትሉ ክንፈ ገብረመድህን ነው ።

4ኛ ፋሽሽት ሽብርተኛው ህ.ወ.ሓ.ት. ግንቦት ወር 1983 ዓ.ም .ኢትዮጵያ ወሮ በቅኝ ግዛቱ ካስገባ ከበረሃ ይዞት በመጣው የአማራው ዘር ማጥፋት በስፋት በመቀጠል በተለያዩ የኢትዮጵያ ግዛት ይኖሩ የነበሩ አማሮች ተወልደው ባደጉበት መሬት ሰፊ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈጽም በገደል በመወርወር ፤ቤት ውስጥ ሰብስቦ ቤቱን በእሳት በማቀጣጠል ህዝብ የፈጀ ሴቶች ህፃናት እርግዞች እመጫት ሽማግሌዎች ሁሉ በአሰቃቂ መንገድ ገደላቸው ፤ይህ ድርጊትም የሽብርተኛው ተግባሩ፤ በዓለም ደረጃ ያጋለጠው የህ.ወ.ሓ.ት. ሽብርተኛነት ነው ።

5ኛ ህ.ወ.ሓ.ት. የአማራው ዘር ለማጥፋት ያልተጠቀመበት ዘዴ የለም ፤ወጣት ወንድ ሴት ሕክምና እያለ ሲፈልግ የአይን ትራኮማ ሲፈልግ የጆሮ የተለያዩ ምክንያቶች በመስጠት፤ልጅ እንዳይወልዱ የሚከለክል ማምከኛ መድሃኒት በመስጠት በርካታ መሃን ሁነው እንዲቀሩ አድርጎዋል ፤ይህ ከባድ የወንጀል ተግባርም የሽብርተኛ ሥራ ነው ፤በዓለም ደረጃ የተወገዘ ተግባር የሚፈጽም ሽብርተኛ ብቻ ነው ፤ይህም የወያኔ ሸብርተኛነቱን ያጋልጣል ።

6ኛ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ኢትዮጵያን በተቆጣጠረ እንኳን በአዲስ አበባና በጎንደር በወልይታ በተለያዩ ቦታዎች ንጹሃን ኢትዮጵያውያን በለሊት ከየቦታ በማፈን ግድሎ ወንዝ ውስጥ ገድሎ ድልድይ ውስጥ መጣል የተለመድ ሆኖ የመጣብት ጊዜ ነው ዛሬ ለምሳሌ ብንጠቅስ አዲስ አበባ ውስጥ እሪ በከንቱ ድልድይ ከስድስት ዓመት በፊት ስድስት ወጣቶች ተገድለው ደልድዩ ስር ተጥለው መገኘታቸው በዜና ሰምተናል ሽብር ማለትም ይህ ነው ፤እነዚህ ተገድለው በየቦታው ተጥለው የሚገኙ በደህንኖቶቹ የተገደሉ ናቸው ።

ስለዚህ ኢትዮጵያ የምትገዛው ያለች በሽብርተኛው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ነው ፤ይህ ድርጀትም ጊዜ ከመጠበቁ አንጻር ካልሆነ ፤ኢትዮጵያን በታትኖ ህዝftም ሃገር አልባ ከማድረግ እንደማይመለስ ካሁኑ ማወቅና መገንዘብ ለምናካሂድው መከላከል ይጠቅመናል ።

ይህም በየትኛውም ዓለም የማይደረግ ድርጊት ። የኢትዮጵያ ህዝብ ግን የዚሁ የህ.ወ.ሓ.ት. ፋሽሽት ስርአት ሰለባ ሆኖ እየተሰቃየ ይገኛል ። በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያነሳው ትልቅ ጥያቄ አለ፣ እሱም፤ በኢትዮጵያ ወስጥ ለተፈጠረው ችግር ተጠያዊው ማነው? እንዴትስ መጡብን ? የሚለው ነው። በ1960ዎቹ የተፈጠረው እንቅስቃሴ ለችግሩ ጥንስስ መሆኑን እንዳለ ለታሪክ ሊቀውንቶች ልተወው።–

ህወሓት የተፈጠረው በዚሁ የተማሪዎች ንቅናቄ ወቅት ነበር። በመጀመሪያ የነበረው ስም በተፈጠረበት በ1964 National Tigray Organization (NTO) ብሄረ ትግራይ ድርጅት  ሲሆን፣ ይህንን ድረጅት የመሰረተው አረጋዊ በርሄ ብቻው ነበር። ፣ ተሳታፊ አባላት አልነበሩትም። በዚህ ጊዜም ሌላ ድርጅት በጀብሃ ታጋድሎ ሃርነት ኤርትራ የተፈጠረም ነበር። እሱም Tigray Liberation Front (TLF) የሚባል

 

ወይም ግንባር ገድሊ ሃርነት ትግራይ (ግገሃት) ነው። ይህ ድርጅት ጸረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ጸረ- ዲሞክራሲ ነበር። ተእዛዞችን በሙሉ የሚቀበለው ከጀብሃ ነበር። የትጥቅ ትግሉን የጀመረው በ1964 ዓ.ም.

 

ነው። ይህ ድረጅት ትግራይ በአማራ መንግሥት (በኢትዮጵያ) ቅኝ ግዛት የወደቀችው ከአፄ ዮሃንስ 4ኛ ሞት በኋላ ነው ብሎ ያምናል። ትግራይ የኢትዮጵያ አካል አይደለችም ብሎ የሚያም ፅንፈኛ ድርጅትና ከሃድ ነው ፤ ህ.ወ.ሓ.ትም እምነቱ ይህ ነው ፤ ስለሆነም፣ለትግራይ ሃገራዊ ነፃነት እንዋጋለን ብሎ ነው የተነሳው። ጀብሃም ትግራይ የአማራው መንግሥት ቅኝ ግዛት ናት ብሎ አምኖ ተቀብሎታል። የአረጋዊ በርሄ ድረጅትም ከግ .ገ.ሓ.ት. መሪዎች ግኑኝነት ነበረው ፤በብዛትም ጓደኞቹ የነበሩ ናቸው ።የሁለቱ ድርጅቶች ማለት ግ.ገ.ሓ.ት. እና ብሄረ ትግራይ ድርጅት ቀጥሎ ማ.ገ.ብ.ት. ፕሮግራማቸው ምንም ልዩነት የለውም። ሁለቱም ትግራይ በአማራው በምኒሊክ ዘመነ መንግሥት ነፃነትዋ ተነጥቃ በቅኝ አገዛዝ በአማራው እጅ የወደቀች ሃገር ናት ፤ የአማራው መንግሥት ለትግራይ ህዝብ በሸዋዊ ዘዴዎቹ ከፍጡር ሁሉ ውጭ በማድረግ ለረሃብ በሽታ ድንሩርና ለስደት ለሽርሙጥና ዳርጎት ይገኛል ። ስለሆነም በትጥቅ ትግል የሃገራችን ነፃነት እናስመልሳለን ፤ በለው የሚያምኑ ሁለት ፅንፈኛ ድርጅቶች የተፈጠሩት በዚሁ የተማሪው ንቅናቄ ጊዜ ነው ። የፕሮግራማቸው ይዞታን አቀማመርም ልዩነት የለም ።ሁለት ድርጅቶች ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ናቸው ።ኢትዮጵታን ለማዳከም አዳክመው ለመበታተን የተፈጠሩ ናቸው ። ሁለቱም ድርጅቶች ግንባር ገሊ ሓርነት ትግራይና የትግራይ ብሔር ድርጅት (NTO ) መቆም የቻሉት በሱዳንና በግብፅ ውስጣዊ ድጋፍን መበረታታ ነው ፤ብዙም ሳይሆን ትንሽ የገንዘብ ድጋፍም ያገኙ ነበር ፤ ከዚሁ የተነሳ ሱዳኖች ከአረጋዊ በርሄ የቆየ ግንኝነታቸው ተጠቅመው ሱዳኖች በ1974 ዓ ም . ያነሱት ኢትዮጵያ መሬታችን ነጥቃናለች ይመለስልን ያቀረftት አቤቱታ የድርጅቱ ቁልፍ መሪ አረጋዊ በርሄም በመሆኑ ጥያቄው ተቀብሎ ያስተናገደው እሱ ስለነበረ የሱዳን መንግሥት ለጠየቀው አወንታዊ መልስ በ1975 ዓ .ም .መስከረም ወር ሱዳን መሬትዋ እንደምታገኝ በነበሩት አምስቱ ፖሊት ቢሮ እና ስድስተኛው መለስ ዜናዊ ፈርመው ያረጋገጡላቸው ። ጊዜው እየተራዘመ ሲሄድ የአረጋዊ በርሄ ድርጅት N.T.O. ( የትግራይ ብሄራዊ ድርጅት ) ጥቂት ሰዎች አሰባስቦ በመጀመሪያ መሰከረም ወር  1967 ዓ.ም. ፣ አረጋዊ በርሄ የመሰረተው ድርጅት ተጨማሪ አባላትን በማሰባሰብ አዲስ አበባ ውስጥ ማገብት ተመሰረተ። ማህበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ ፤ ( የትግራይ ብሄራዊ ድርጅት) ( N.T.O. ) የሚለው ስም በማ.ገ.ብ.ት. ተለወጠ ።

;።ይህ ድርጅት የመሰረቱት ሰባት ሰዎች ናቸው: እነሱም፣ አረጋዊ በርሄ፣ ዋና ሰብሳቢና ሊቀመንበር፣ ግደይ ዘርአጽዮን ም/ሊቀመንበር፣ አባይ ፀሃየ፣ የቅስቀሳና የፕሮፓጋንዳ ሃላፊ፣ ስዩም መስፍን፣ ዘርኡ ገሰሰ፣ አስፍሃ ሃጎስና አለምሰገድ መንገሻ (ሃይሌ ነጠቦ) ናቸው። ማገብት እንደተመሰረተ ስብሃት ነጋ፣ መለሰ ዜናዊ፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ አጽብሃ ዳኘውና ገሰሰው አየለ በፍጥነት ተቀላቅለው አባል ሆኑ።

 

ፕሮግራሙን በተመለከተ፣ በዲማ ኮንፈረንስ በየካቲት ወር  1968 ይፋ እንደተደረገ የተ.ሓ.ህ.ት. የተግል ፖሊሲ የአቋም ፕሮግራም ሆኖም ፀደቀ ።ፕሮግራሙም የድርጅቱ አቋም ሆኖ ቀጠለ ። ይህ ፕሮግራም ከደደቢት በረሃ ለትጥቅ ትግል ተ.ሓ ህ.ት. ከተነሳበት ጊዜ ጀምሮ በትጥቅ ትግሉ ጊዜ ምንም አይነት ለውጥ ያልተደረገበት ታስቦም ተሞኩሮም የማይታወቅ ትግሉ ከተጀመረ ክ6 ወር ቆይታችን በኋል የነበሩት ጉድለቶች አርመነዋል የሚል የሚናገሩት ፍፁም ውሸት ሲሆን የታረመው የትኛው ክፍል ነው ተብለው ቢጠየቁ መልስ የላቸውም ማስረጃም ሊያቀርftም አይችሉም ።የበሰበሰ አምባገነናዊ በታኝ ፀረ ህዝብና ፀረ ሃገር ፕሮግራም ። ሀወሓት ወያኔ ኢትዮጵያ ወሮ የቅኝ አገዛዝ ስርአቱ ስልጣኑን ካረጋገጠበት ግንቦት 20 1983 ዓ.ም. ሳይለወጥ እንዳለ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ሆኖ ሃገር እያፈረስ ሃገር እየሸጠ ህዝብ እየበተነ ያልው የፋሽሽቱ ወያኔ ፕሮግራም ነው ።            ። ይህ ፕሮግራም ከመነሻው ገጽ ጀምሮ ጸረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ጸረ-ኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ይህ ፕሮግራም በእነ አረጋዊ በርሄ የተዘጋጀና የተሳናዳ ሰነድ ከመነሻው ጀምሮ በትግራይ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕዝብ በአማራው ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት ወዘተ የአማራውን ዘር ያጠፋ ወንጀለኛ ሰነድ ነው። ይህ ብቻ አይደለም፣ ተሓህት-ህወሓት የአማራውን ግዛት፣ ጎንደሬዎች የሚኖሩበትን፣ ከትወልድ ትውልድ እየተላለፈ የመጣውን የአማራውን መሬት የትግራይ ቦታ ወይም ግዛት ነው በማለት መሬታቸውን ተነጥቀዋል። የአማራውን ሕዝብ ከትውልድ ቦታቸው ለማጥፋት፣ ዘራቸው የጠፋው ከዚህ የመሬት ነጠቃ ጋር የተያያዘ የግፍ ግፍ ተፈጸመባቸው። ይህ በዓለም አቀፍ ሕግ

 

የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው። በዚሁ ጊዜ ተዋናይ በመሆን ይህንን ግፍ ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ የነበሩትን በግልጽ ለማስቀመጥ፤ አረጋዊ በርሄ፤ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን እና መለስ ዜናዊ ናቸው። የመጀመሪያዎቹ አምስቱ የፖሊት ቢሮ አባል ሲሆኑ፣ መጨረሻ ላይ የተጠቀሰው በማንኛውም ውሳኔ ከነሱ የማይለይ  ማእከላይ ኮሚቴ የነበረ በ1975ዓ.ም ደግሞ ፖሊት ቢሮ የሆነ ነው                      ። በዘር ማጥፋቱ ወንጀልና በትግራይ በተፈጸመው ሕዝብ የመግደል፣ የማፈን እና ማጥፋት እንዲሁም ንብረትና ሃብት መንጠቅ ተለይቶ አያውቅም። ይህንን ሁሉ ግፍ የፈጸሙት አብረው ነው።

 

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት የህወሓት ከፍተኛ የአመራር አባላት የሚመሩት ድርጅት የፈጸመው ወንጀል የሚዘገንን ነው። ወንጀል የሚፈጽሙበትን አሠራር አስቀድመው አዘግጅተዋል። ዋና ዋናዎቹ፣ ሃለዋ ወያነ (06) ወህኒ ቤቶችን ከተሟላ አባላቱ ጋር በየቦታው መስርተዋል፤ ፈዳያን ( አጥፍቶ ጠፊ ) terrorist-አፍኖ የሚያጠፋና የሚገድል ftድን፣ ክብሪት ተብሎ የሚታወቀው በአንድ ጉጅሌ ከ10—እስከ 12 ታጋና ወያኒ ( ምልሻ ) ያካተተ ሁሉ የታጠቁ አደገኛ ነብስ አጥፊ በቀን በለሊት ሰውን እያፈን የሚገድል በማሰማራት ፣ ግለሰቦችን ባገኘበት ቦታ የሚገድል ftድን፣ የስለላ መርበብም አጠናከሩት ፣ የሕዝብ ግንኙነት ታጋዮች፣ሁሉ በስለላው ውስጥ የተካተቱ ናቸው ፤ እነዚህ ህብረተሰftን በማያውቀው የፖለቲካ ውጥንቅጥ በማስገባት ህዝብ ራሱ በራሱ እንዲጠራጠር እንዳይተማመን አንዱ ለአንዱ ተከታታይ ሰላይ አደረጉት እንደ ድሮው አብሮ መብላት መጫወት ቀረ ፤ ባል ከሚስቱ ፤ሚስት ከባልዋ መተማመን ቀረ ፤የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች የትግራይ ህዝብ ከፋፈሉት ፤ለሚጠሉት ለሚጠረትጥሩት ሁሉ ፤ ጸረ-ሀወሓት፣ ኢዲዩ፣ ኢህአፓ፣ ደርግ ወዘተ የሚል ስም እየለጠፉ ሕዝብ አስጨረሱት ፤ የአካባቢ ኗሪ ሰዎች ወንድ፣ ሴት እየመለመሉ ታማኝነታቸውን ለማስመስከር በውሸት ብዙ ሰዎች አጥፍተዋል። ለውለታቸውም ሰፊ መሬት ይሰጣቸዋል። እነዚህ ከየቦታው እየተመለመሉ ተባብረው የሚሰሩት ከሕዝብ ግንኙነት አባላት ጋር ነው። ከነዚህ መካከል ለስጋቸው ያደሩ ቄሶችና ካህናት ይገኙበታል። ቀሱም ካህኑም እግዚአብሄር የከዱበት ዘመን ህ.ወ.ሓ.ት ፈጠረ

።በአስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ግን ይህ አልታየም ፤በእምነታቸው እንደፀኑ ቀጠሉ ፤ፀረ እምነታቸው ሁነህ ፤ከመጣህም ይቃወሙሃል አይፈሩም አይንበረከኩም ።

 

መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ለስልጣን የበቁበት ምስጢር ስንመለከተው ምስጢሩ የሚያስገርም ነው። ገና የተሓህት 1ኛው ጉባኤ በእቅድ የተያዘው በ1969 መጨረሻው አካባቢ ነበር። ስብሃታ ነጋ በወቅቱ ፖሊት ቢሮ ሲሆን መለስ ዜናዊም እስከ 1ኛው ጉባኤ ድረስ ተለዋጭ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ነበር። የፕሮፖጋንዳው ክፍል ሁለተኛ ተጠሪ ከአባይ ፀሃየ በታች በመሆን በሥራም የሚታወቀው ግን መለስ አዛዥ አባይ ታዛዥ ሆነው ሲሰሩ ድብቅ ምስጢር አልነበረም። ምክንያቱም መለስ ዜናዊ የአረጋዊ በርሄ ታማኝ ነው። አረጋዊ በርሄም በመለስና በስብሃት የሚመጣ ነገር አያስችለውም።ፀር-መለስና ስብሃት ሆነው የተነሱ ታጋዮች አረጋዊ በርሄ ካለምንም ማቅማማት ያጠፋቸዋል፣ ይገድላቸዋል።የተገደሉም አሉ ስብሃትና መለስ አትመን ፀረ ሃገርና ፀረ ህዝብ ናቸው የባንዳ ልጆች ከመሆናቸው የተነሳ በትግራይ ህዝብ ቂም በቀል በሆዳቸው የቋጠሩ ችግር ይፈጥራሉ ፤ ሌላም እነዚህ የባንዳ ልጆች የትግራይን ህዝብ መምራት ማለት ለትግራይ ህዝብ ስድብና ውርዴትም ጭምር ነው ፤ብለው ብዙ ምክር ቢለጉስለት የራሱ የቅርብ ጓደቹ አረጋዊ ይህን አልሰማ ብሎ ይህ ቀና ምክር መጥፎ ትርጉም ስጥቶ ገልብጦ የሥልጣን ሥሰኞች በማለት ተረሽነው ተገድለዋ በጥቂቱም ለማንሳት               1 እቁባዝጊ በየነ 2 አሰፋ ገብረዋህድ 3 ዘወንጀል በየነ 4 ህንፃ ሽፈራው 5 ዓለም ወልደገሪማ ሌሎችም ብዙ ታጋዮች ተረሽነዋል ፤አመራሩ ሕንፍሽፍሽ ብሎ የሚጠራው

በድርጅቱ ታጋይ አምነት የዲሞክራሲ ጥያቄ ነው፤ ዋና ግንባር ቀደም ጥያቄ ስብሃት ነጋ እና መለስ ዜናዊ ፀረ ህዝብ የባንዳ ልጆች ይወግዱልን መለስ ፈሪ ከብዙ ጦርነት የሸሸ ይገደል በማለት ቀዳሚ ጥያቄ ሆኖ በተነሳ ለነ አረጋዊ ሊዋጥላቸው ስላልቻለ በስንት ሺህ የሚቀጠሩ ታጋዮች ተረሽነው ተገድለዋል ።

ሌላው አስገራሚ ነገር በ1969 ዓ.ም. መጀመሪያው አካባቢ በአረጋዊ በርሄ የሚመራ ftድን ስብሃት ነጋ ግደይ ዘራፅዮን ስዩም መስፍን ሆኖው ወደ ሻዕብያ ፤ሳሕል ድረስ ተጉዘው ነበር ፤ የጉዞው ዋና አንኳር ምክንያቱም ትግራይ ነፃ ሃገር ራስዋን ችላ ቀደም ሲል የአኩሱም መንግሥት መስርታ ለ900 መቶ

 

ዓመታት በነፃነትዋ የቆየች ሃገር ፤ በኋላም በአፄ ዮሃንስ መንግሥትነት እየተመራች የቆየች ነፃነትዋ አስከብራ የቆች ነፃ ሀገር ከአፄ ዮሃንስ ሞት በኋል በንጉሥ ምኒልክ ተወራ በአማራው የሸዋ መንግሥት በቅኝ ግዛት ሥር ወደቀች ። ትግራይ ነፃነትዋ ተገፋ የአማራ መንግሥት ቅኝ ግዛት ሆነች ። በአማራው ዘዴ ህዝብዋ ለመከራ ለችግር ለስደት ዜግነቱ ነፃነቱ ተነጥቆ ሁለተኛ ዜጋ ሆኖ ፤ ነፃ ሃገር ትግራይ ፤ በአማራው ቅኝ አገዛዝ ስርአት                                        መሆንዋን የሻዕብያ ድርጅት የአማራው ቅኝ ተገዥ መሆናችን እውቅና ሰጥቶ በእውቅና ይቀበለን የሚል ጥያቄን ልመና ይዘው ሳሕል ድረስ ሂደው አቀረft ።ይህን የእውቅና ልመና ይዘው የሄዱት የተ.ሓ.ህ.ት. መሪዎች               1ኛ  አረጋዊ በርሄ  2ኛ ግደይ ዘራጽዮን      3ኛ ስብሃት ነጋ                                4ኛ  አባይ ጸሃይ ናቸው

። የአቶ ኢሳያስ አፈወርቅ መልስ ፤ ይህን ጥያቄ ማቅረባችሁ በጣም አዝናለሁ ፤ትግራይና ኤርትራ የኢትዮጵያ የታሪክ እምብርት ናቸው ፤የኢትዮጵያም አካልና ግዛት ናቸው ፤በታሪክም በባልም በቋንቋም በሃይማኖትም አንድ ህዝብ ሆኖ የመጣ ህዝብ ነው ። እኛም በኤርትራ ውስጥ ትግል የጀመርነው ለኤርትራ በተባበሩት መንግሥታት የተሰጠን የኤርትራ ፈደረሽን በንጉሡ ተነጥቀን የነበረው መዋቅር አፍርሰው የተሰጠን መብት ተነጥቀን ነው ፤ በተባበሩ መንግሥታት የተሰጠን የፈደራሉ አገዛዝ ቢመለስልን ውጊያ አያስፈልገንም ነበር፤ የፈደራሉ ስርአቱን ይዘ ኢትዮጵያዊነታችን ይበጀን ነበር፤ ግን አልሆነም ። የአሁኑ የናንተ ጥያቄ የአማራ ቅኝ ተገዢ ነን ማለታችሁ ጤንነት የሌለው በመሆኑ አዝናለሁ ፤እኛ ለዚሁ አሳፋሪ ነገር ፀረ ኢትዮጵያ እውቅን አንሰጥም ። በእትዮጵያዊነታቹህ ልትኮሩ በተገባቹህ ነበር፤ መልሳችንም ይህ ነው ። ብለው አሰናበትዋቸው። እነዚህ የተ.ሓ.ህ.ት. መሪዎች የኤርትራው የሻዕብያው መሪ ኢሳያስ አፈወቂ የትግራይ የቅኝ ግዛት ጥያቂ አልቀበልም ፤ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ናት ስላለን ግኑኝነታችን ተበላሽትዋል ብለው ለተ.ሓ.ህ.ት.ታጋይ በአዋጅ በስብሰባ ተናገሩ ፤ሁሉ ታጋይ ሻዕብያን እንዲያወግዝ ቢያደርጉም ሰሚ አልተገኘም ።የህ.ወ.ሓቅ.ት. መሪዎች ጠባሳ ታሪክ አደራ አስቀምጠው ተመለሱ ፤ሻዕብያ ይህን በድምፅ ቀርፆ በሰነድ ፅሁፍ አዘጋጅቶ ነው የሚያስቀምጠው ።

 

የድረጅቱ ፋላጭ ቆራጭ፣ እስከ መባረሩ ጊዜ ድረስ ሆኖ የቆየው ፣ አረጋዊ በርሄ መሆኑና መኖሩ ሁሉ የህ.ወ.ሓ.ት ታጋይ በግልጽ የሚያውቀው ጉዳይ ነው ።እሱ ያልፈቀደው አንዲት ነገር አትሰራም ፤ይሁን ያለው ይሆናል አይሆንም ካለም አይሆንም ፤ የስብሃት ነጋ የመለስ ዚናዊ ከአረጋዊ በርሄ የነበራቸው ፍቅር የጠበቀ ግኑኝነት ልዩ ነበር ከዚሁ በመነሳትም መለስ ዜናዊ በጦርነት ፈሪ በመሆኑ ጥይት ስትቶኮስ መሬት ተከፍታ ብትውጠው ይመኛል ከብዙ ጦርነቶች የሸሸ ፈሪ ታጋይ ከህ.ወ.ሓ.ት. ውስጥ መለስ ነበር አንዱ ከብዙ የውግያ ቦታ የሸሸ ነው ሌላ በጦርነት ያፈገፈገ በቀጥታ ይገደላል መለስ ግን ከዓድዋ ኦፖረሽን ከዓዲዳእሮ ፤ ከማይቅነጣል ወ.ዘ.ተ ፈርቶ ሸሽቶ ሲጠፋ የተወሰደበት እርምጃ የለም እድሜ ለአረጋዊ የሚጠይቀውም የለም ። መለስ ከስልጣን ወደ ስልጣን እየተራመደ የመጣውም በአረጋዊ በርሄ ትክሻ ነው ፤ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ። ሶስቱ የነበራቸው ግኝኙነትና ጓደኝነት በጣም የጠበቀ የሚተማመኑ አመራር እነዚህ ሶስቱ ነበረ ሁሉም ታጋይ በአይነ ቁራኛ ይመለከታቸው ነበር። አረጋዊ በርሄም የድረጅቱ ስልጣን በዋናነት በሶስቱ እጅ እንዲወድቅ በነበረው ምኞት መሰረት ገና 1ኛው ጉባኤ ከመድረሱ በፊት ሶስቱ ባልታወቀ ቦታ ተገናኝተው የሚከተለውን እቅድ አወጡ፣የሃሳft ባለቤት አረጋዊ ሲሆን ፤በሚከተለው ሃሳብ ተስማሙ ፤

1ኛ. የድርጅቱ ሊቀመንበር ለስብሃት ነጋ፣

2ኛ. የድረጅቱ ወታደራዊ አዛዥ ለአረጋዊ በርሄ፣

3ኛ. በህወሓት ውስጥ ለሚመሰረተው ማርክስ ሌኒናዊ አስኳል በመለስ ዜናዊ እንዲመራ ኮምሽነር ሆኖም ሁሉ የካድሬ ሥልጠና በመለስ እንዲመራ       ተስማሙ።

ይህ በዚህ እንዳለ፣ ይህ የሶስቱ ሚስጢር ያገኘው ተክሉ ሃዋዝ የድርጅቱ የደህንነት ሃላፊ ነው ሚስጢሩም ያጫወተኝ ያገኘሁትም ከተክሉ ሃዋዝ ነው ። አረጋዊ በርሄ ከተለያዩ ታጋዮች ስብሃት ነጋ እና መለስ ዜናዊ ለድርጅቱም ሆነ ለትግራይ ሕዝብ አደገኞች መሆናቸው የተለያየ ሃሳብ ይሰጡት ነበር። ቢሆንም አረጋዊ በርሄ እነዚህ ታጋዮች የሚሰጡት ሃሳብና ምክር ሳይቀበል ቀርቶ ይህ ምክር የለገሱት ታጋዮች በጠላትነት እየፈረጀ የሥልጣን ሱሰኞች እያለ ከገደላቸው የተማሩና አብረውት ያደጉ ታጋዮች ለአብነት መጥቀስ አስፈላጊ ሆኖ ስለአገኘሁት ልጥቀስ፤ እቁባዝጊ በየነ፣ አሰፋ ገብረዋህድ፣ አባዲ ተምቤን፣ ዘወንጀል በየነ፣ ገብረዝጊ አለማየሁ፣

 

ይብራህ ገብረጊዮርጊስ፣ ዘሚካኤል ደስታ፣ ዓለም ወ/ገሪማ፣ አበራ ማንካ፣ ሃይለሥላሴ ገ/ሚካኤል፣ ሃዲሽ ዮሃንስ፣ ሃጎስ ሃይለሥላሴ፣ ዘርኡ በዛብህ፣ ባሻይ ሃንጣል፣ ዘርኡ ገሰሰ፣ ገሰሰ አየለ፣ አዘናው ገ/ጻዲቅ፣ ተስፋይ ዓድዋ፣ ህንጻ ሽፈራው ወዘተ መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ወደ አመራር መምጣት ከሚስጠው ጥቅም ለትግራይ ሕዝብ አደገኛ መሆናቸው በመጠቆም ሌላው ድርጅቱ በባንዳ ልጆች መሙላቱ አድጋውን አስቀድመው በመተንበይ ሲናገሩ በአረጋዊ በርሄ ደግሞ የሥልጣን ሲሰኞች ተብለው እነዚ ሁሉ ተገደሉ። በተሓህት-ህወሓት ውስጥ በዚሁ ወቅት የተለያዩ የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ታጋዩ ይስነሳበት ጊዜም ነው። እኛ የተሓህት-ህወሓት መብታችን ይከበር ድርጅቱ አምባገነን እና ፀረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት፣ ፀረ-ሕዝብ አንድነት፣ ፀረ-ሰላም ፀረ ዲሞክራሲ ነው ። መለስ ዜናዊ ከተለያዩ የጦርነት ቦታዎች በፍርሃት ሲያፈገፍግ የተወሰደበት እርምጃ የለም። እኛ ታጋዮች ግን በዚሁ ምክንያት በመቶዎች ታጋይ ሃለዋ ወያኔ (06) እያስገባችሁ ተረሽነን ተገድለናል ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል። የተሓህት-ህወሓት አመራር፤ አረጋዊ በርሄ፣ ስብሃት ነጋ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስዩም መስፈን፣ አባይ ፀሃየ፣ መለስ ዜናዊ ተሰባስባችሁ በድርጅታችን ሕንፍሽፍሽ ተነሳ በማለት የዴሞክራሲውን ጥያቄ ወደ ሕንፍሽፍሽ ለውጣችሁ ታጋዩን ፈጃችሁ፣ በጅምላ ጉድጓድ ቀበራችሁ። ሌላውም ሕንፍሽፍሽ ወደ ሰላማዊ ዜጋ ተዛመተ ተብሎ የገጠርና የከተማውን ሰው እያጠፋችሁ ነው። የገደላችሁትንም ንብረቱን በህወሓት ውርስ ተደርጓል። የንጹህ የትግራይ ሕዝብ መብት ይከበር በምንልበት ጊዜ፣ ሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ ብናነሳ መልኩን ለውጣችሁ ሕንፍሽፍሽ በማለት ተፈጀን፣ አለቅን። ለዚህ ሁሉ ግድያ በታጋዩ እና በሰላማዊ ዜጋ ላይ የተፈጸመው፣ እየተፈጸመም ያለው እልቂት ተጠያዊ የምትሆኑት 6 (ስደስት) የአመራር አባል ናችሁ። ከዚሁ በመነሳት ታጋዩ ባገኘበት መንገድ ወደ ደርግ የያዘው መሳሪያም ሆነ ሌላ የድርጅቱ ንብረት እየተሸከመ በብዛት ጎረፈ ለደርግ እጁን ሰጠ።

 

ከላይ የተጠቀሱትና የተገደሉት ታጋዮችና ያልጠቀስኳቸው ሌሎችም የአረጋዊ በርሄ አብሮ አደግና የቅርብ ጓደኞቹ ናቸው። ግን ለመለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ተቆርቋሪ በመሆኑ መሆን የለበትም ፤የድርጅቱ ሕግ በሁሉ ታጋይ እኩል መስራት አለበት ሌላው ሲገደል ሌላው አይጠየቅም ፍርድ እየተዛባ ነው በማለታቸው ገደላቸው። ይህም ተጠያቂ የሚያደርገው አረጋዊ በርሄን ነው ፤ የፈጸማቸው ወንጀሎች ብዙ ናቸው። ከኢዲዩ ጦርነት ህወሓት በሚካሄድበት ጊዜ የኢዲዩ አብላት ተሸንፈው እጃቸውን ሰጡ። በመስከርም አካባቢ 1969 ብዙ ምርኮኞች ናቸው አረጋዊ በርሄ ጨአ፣ መስከበት አካባቢ የጅምላ ጉድጓድ አስቆፍሮ ረሸናቸው። ከሱ ጋር የነበረው አልአሚን፣( የኋላሸት ገብረመድህን)፣ ተው አትግደላቸው አሁን ጠያቂ ባታገኝም ለኋላ ኋላ ግን ያስጠይቅሃል ብሎ ቢማጸነውም አልተቀበለውም። አልአሚን ያየውን ፋሽስታዊ ግፍ ለብዙ ሰዎች ተናግሯል። በሚያዚያ 1972 በለሳ ማይሓማት በነበረው ሃለዋ ወያነ በሃሰን ሹፋ የሚመራው ( 06 ) የነበሩትን እስረኞች የሞት ፍርድ ለመስጠት የሚያርፉበት ቦታ በ03 (ሕክምና ክፍል ) እንዲዘጋጅ በማድረግ ትንሽ ድንኳን ተዘርግቶ አርጋዊ በርሄና ስብሃት ነጋ ጨለማን ተገን በማድረግ ህክምና ክፍል በተዘጋጀላቸው ቦታ በመድረስ በጥዋቱ ወደ ሃለዋ ወያነ በመሄድ ቀኑን ሙሉ ሞት ሲፈርዱ ይውሉና፤ ማታ ደግሞ ህክምና ክፍል ወደሚገኘው ማረፊያ እየተመላለሱ በአምስት

ቀናት ውስጥ 385 ላይ የሞት ፍርድ ፈርደዋል። ከነዚህ መካከል 153 ንጹሃን ሲቪል ዜጎች ሲሆኑ፣ 232 ደግሞ ታጋዮች ናቸው ሁሉም ተረሽነው በአራት የጅምላ ጉድጓድ ተቀብረዋል። ከሰላማዊ ዜጎች መካከል አቶ አሰፋው ወልደአረጋይ፣ ግራዝማች ታደለ ማሩ አቶ ወርቀላኡል ግራ/በላይ ፣ ወዘተ ይገኙበታል። በዚሁ ተመሳሳይ፣ በ1973 ግንቦት ወር አካባቢ ፃኢ ሓለዋ ወያነ ህክምና ክፍል ተደብቀው አድረው ስብሃት ነጋና አራጋዊ በርሄ በጥዋቱ ጻኢ ሃለዋ ወያን በመሄድ እዛው ተደብቀው የሞት ፍርድ በመፍረድ ከ1500 በላይ ታጋዮችና ሰላማዊ ዘጎች በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ አድርገዋል። ጻኢ ሃለዋ ወያነ በብዛት እስረኞች የሚታጎሩበት በጣም ሰፊ ወህኒ ቤትና መግደያ ቦታ ነው። እነዚህ ለአብነት ያህል ተጠቀሱ እንጂ የህወሓት ሃለዋ ወያነ (06) በጣም ብዙና ሰፋፊ ወህኒ ቤቶች አሉት። ከሰፋፌሶቹ ሃለዋ ወያነ መካከል ለመጥቀስ፤ ሱሩ፣ ፍየል ወሃ፣ ገሃነብ፣ አዲ በቅሎ፣ ወርኢ፣ ባኽላ፣ አዲ ጨጓር፣ በለሳ ማይሃማቶ፣ ጻኢ፣ አዲ መሃመዳይ ወዘተ ሲሆኑ፣ በጣም ሰፊና ከመሬት በታች ተቆፍረው የተሰሩ ጨለማ ወህኒ በቶች ናቸው። በብዙ መቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ አማሮች እንዲሁም ትግሬዎች ያለቁበት መጥፎ ወህኒ ቤቶች ናቸው። እነዚህ ሃለዋ ወያነ በግደይ ዘርአጽዮን

 

ክትትል የተሰሩ ሲሆኑ፣ የወያኔ ህወሓት አመራር በወንጀል የሚጠየቁበት ይህም ነው። የወንጀል ተግባራቸው እየሰፋና እየጨመረ ሲሄድ ከላይ የተጠቀሱት የአመራር አባላት በተናጠል እየተንቀሳቀሱ ህዝftን ፈጅተዋል።

 

እነዚህ የህወሓት አመራር አባላት ዛሬ በየቦታው እየዞሩ እኔ ከደሙ ንጹህ ነኝ እያሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ እያወናበዱ ይገኛሉ። እነ አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስየ አብርሃ፣ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ ፤ አባይ ፀሃየ ስዩም መስፍን ፤አዋአሎም ወልዱ ፤ አርከበ ዕቁባይ ፃድቃን ገብረተንሳይ ፤አበበ ተክለሃይማኖት ፤ ብስራት አማረ

፤ ክንፈ ገብረመድህን ፤ሙሉጌታ አለምሰገድ       ወዘተ፣በብዙ ሞቶ ሺዎች የሚቆጠር አማራ በብዙ ሺዎች የሚቆጠ ትግሬው ህዝብ ገድለዋል ።በዚህም ይጠየቃሉ ፤ለፍርድም ይቀርባሉ ። በሓምሌ ወር 1977ዓ ም እነ አረጋዊ በርሄ ቢበረሩም በአማራው ግድያ አፍኖ ማጥፋት እንዳለችው ነው፤ እነ መለስ ዜናዊም የቀጠሉበት። አረጋዊ፤ስየ ግደይ ስብሃት ወ.ዘ.ተ. የኢትዮጵያን ህዝብ ለማደናገር የማቆፍሩት የለም፤ ሕዝft ግን በተገቢ ሁኔታ ማንነታቸውን የሚያውቃቸው በመሆኑ የፈጸሙት የግድያ ወንጀል ጥርት አድርጎ እንደሚያውቅ አልተገነዘftትም። በአማራ ብቻ እንኳን በንመለከት በ1985ዓ.ም        የህዝብ ቆጠራ ከ3 ሚልዮን አማራ ተገድሎ ደብዛው ያልተገኘ የቀረበ እስታክቲክስ የህዝብ ቆጠራ አለ ፤እንደገና በ2006 ዓ.ም አካባቢ በተካሄደ የህዝብ ቆጠራ ከ6 ሚልዮን በላይ አማራ የለም ፤ይህም በወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት.ተገድሎ የጠፋ ህዝብ ነው ። ህ.ወ.ሓ.ት በወሰደው የዘር ማጥፋት ዘመቻ     ንጹሃን ኢትዮጵያውያን ብዙው አማራው እና ትግሬው ደማቸው በከንቱ የፈሰሰው ደም በእግዚአብሄር ፊት እየጮኸ ይገኛል ftምበት ሃለዋ ወያነ (06) በግደይ ዘርአጽዮን በትግራይና በአማራ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያና ሰቆቃ አሰቃቂ ነው። በዚህ ስፍራ ከሰላሳ በላይ የጅምላ ግድያ የተፈጸመባቸው የጅምላ መቃብሮች ይገኛሉ። እነዚህም በግድይ ዘራጽዮን የተገደሉ ናቸው፤ ።

 

ተ.ሓ.ህ.ት-ህ.ወ.ሓ.ት. መንቀሳቀስ ከጀመረበት ከ1964 ስሙን እየለዋወጠ ነበር። ሃገርን እና ሕዝብን ማጥፋት ገና ሳይጀምር በ1964 የሚጠራበት ስም National Tigray Organization (NTO)፣ ብሄረ ትግራይ ድርጅት  ሲሆን፣ ቀጥሎ ማገብት ተባል። በ1967 የካቲት 1967 እስከ የካቲት 5፣ 1971 ደግሞ ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) እየተባለ ሲጠራ ነበር። በ1ኛው ጉባኤ፣ ከየካቲት 5፣ 1971 በተደረገው ጉባኤ ስሙን ልወጦ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እስከአሁን በሚጠራበት ስም ተሰየመ። ይህ ድርጅት በየወቅቱ ስሙን የሚለዋውጥበት ምክንያቶች ብዙ ናቸው። ዋናኛው ግን ኢትዮጵያን ለማፍረስና ብሎም አማራን እና የኦርቶዶክስ ክርስትናን ክርስትና እምነት ለመጥፋት ባለው እቅድ ነው ፤ይህም በተግባር ወያኔ እየፈጸምው ይገኛል ፤፤ እንዲሁም የእትዮጵያን ህዝብ በቋንቋን በዘር ከፋፍሎ ለማጋጨት የተነሳው ገና ከማ.ገ.ብ.ት. ጀምሮ ለመሆኑ በፕሮግራሙ በማያሻማ መንገድ ጽፎታል ፤ አሁን በኢትዮጵያ እየደረሰ ያለውም ይህ ነው ። እኛ አይደለንም፣ እኛ እስከተባረርን እስከ ማ.ለ.ሊ.ት. ጉባኤ ሓምሌ ወር 1977 ዓ.ም ድረስ ህ.ወ.ሓ.ት. ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ነበር የሚሉት እነ አረጋዊ በርሄ ግደይ ዘራፅዮን የፈጸሙት አሰቂ ወንጀል ለመሸፈን ከሆነ ይህን አያዋጣም ፤ህ.ወ.ሓ.ት. ፋሽሽት ናዚ እያለ ታጋዩ ሲጠራው ከ1968ዓ፣ም አጋማሽ ጀምሮ እኮ ፋሽሽት ናዚ ተባልን እያሉ ሲያለቅሱ የነበሩትን እንዴት ረሱት ? ክላሽናቸው ሽጉጣቸው ወልውለው የሰው ፍጡር ሲፈጁ ፤ የሰው ልጅ ከ200መቶ በላይ በሰሩት ከመሬት በታች 2ሜትር ጥልቀት ቆፍረው የሰሩት ሰፋፊ ወህኒ ቤቶች በጢስ እያፈኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠር የአማራው ሂወት አልቆ የሞተው ረሱት እንዴ?› ይህ ክፉ አረሜናዊ ወንጀ ይረሳል ብየ አላምንም ፤ እስቲ ፋሽሽቱ መሪ ግደይ ዘራጽዮን ተናገር ፤ይህ ወንጀልህ ትረሳለህ ፤ ሌሎች ናቸው ከማለት ከነ ስብሃት ነጋ አባይ ፀሃይ መለስ ዜናዊ ስዩም መስፍን ወ.ዘ.ተ ተባብረን በንጹሃን ዜጎች ኢትዮጵያውያ የዘር ማጥፋት ወንጀል በብዙ መቶ ሺዎች ሚልዮኖች አሰቃቂ ግድያ በመፈጸም በወንጀሉ እንጠየቃለ ብላቹህ ማመኑ ይሻላችኋል ፤ በሰፈርከው ቊና ትሰፈራል አትርሱ ህ.ወ.ሓ.ቶች ። በዚህ ማተለያ ዘዴ አልተጠቀሙም ማለት አይደለም፤ ማርክስ ሌኒናዊ ሊፍ ትግራይ (ማሌሊት) በ1977 እንደተመሰረተ፣ ያላሰftትና በስልጣን ሽኩታ የተባረሩት አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘርአጽዮን በ1969 በትንሹ የጀመሩት በከፋ መልኩ ደግሞ ከ1972 መነሻ ጀምሮ በተከታታይ አመታት የአማራውን ዘር በማጥፍት፣ የትግራይን ንጹሃን ዜጎችን በመግደልና በማሰቃየት 10 ዓመት ድርጅቱን የመሩ ከፍተኛ አባላት የተናገሩት ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያስታውሰው ነው። ማሌሊት ከተመሰረተ በኋላ፣ ድርጅቱ ህወሓት ማለት ነው፣ ጸረ-ዴሞክራሲ ሆኖ አማራውን የፈጁት የማሌሊት ባለስልጣናት ናቸው።

 

ከባለስልጣኖቹ መካከል ዋናዎቹ ፀረ አማራ ፀረ አኦርቶዶክስ ክርስትና መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ይገኙበታል። ነገር ግን በተደጋጋሚ እኛ ከደሙ ነፃ ነን እያሉ ደጋግመው ያወራሉ። ሌላው ቀርቶ የኢትዮጵያን ታሪካዊ የባሕር በር ያሳጧት ገና ትግሉ ሳይጀመር ነው። ትግሉ እንደተጀመረም ኤርትራ ነፃ ሃገር ነበረች፣ ነገር ግን በአማራው ገዥ መደብ ብቅኝ ግዛት ስር ወደቀች፤ እኛ የህወሓት አመራር በመሪ ድርጅታችን ስር ሆነን ኤርትራን ነፃ አውጥተን ያደገችና አገር እናደርጋታለን ስትሉ የነበራቹህ እኮ አረጋዊ ፤ ግደይ፤ ስብሃት፤ መለስ፤ አባይ፤ ሥዩም ናቹህ ። በተለይ አረጋዊ በርሄ እንቅልፍ ያጣበት ሥራው ይህ ነበር። ዛሬ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ በመምሰል፣ የማሌሊት አመራሮች የኢትዮጵያን ታሪካዊ የባሕር በር አሳጧት እያለ ሲናገር ይሰማል አረጋዊ ሃፍረት የሌለው ጅል ነው የተ.ሓ.ህ.ት. ፕሮግራም አዘጋጅና ለጉባኤው አቅርበህ ያፀደቀው አንተ ነህ ሌላው የኤርትራ ካርታአዘጋጅተህ የርትራ መልካ መሬት አቀማመጥ አሰብን ያጠቃለለ ያቀረብክ አንተው ራስህ ነህ ይህን ሁሉ አሳፋሪ ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ጉድ ተሸክመህ ፤አትዋሽ አታደናግር        ። ከዚህም አልፎ፣ አረጋዊ በርሄና ጓደኞቹ በቀይ ኮከብ ዘመቻ ኦፐሬሽን ጊዜ 120000 ከ(አንድመቶ ሃያ ሺህ ) በላይ የትግራይ ተወላጅ ወጣት ሴቶችና ወንዶች ወደ ኤርትራው ቀይ ኮከብ ዘመቻ በመላክ በጦር ውግያው በማሰለፍ አሰማርቷል ይህ ሁሉ ወጣትም በቅይ ኮከብ ዘመቻው አለቀ ። ከነዚህ መካከል አካለ ጎደሎ ሆነው የተመለሱት 1,345 ብቻ ናቸው። ለዚሁም ተጠያቂዎች ፤የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ሲሆኑ ።እነሱም ።

1ኛ ስብሃት ነጋ    2ኛ  አረጋዊ በርሄ    3ኛ  መለስ ዜናዊ    4ኛ  ግደይ ዘራፅዮን     5ኛ  አባይ ፀሃየ                              6ኛ ስዩም መስፍን እነዚህ በተፈጸመው ህገ ውጥ ወዶ ገብ ዘመቻ ተግባር በወንጀሉ ይጠየቁበታል ። ቀይ ባህርና የኢትዮጵያ የባህር ማሳጣት በተመለከተ ዋናው ተጠያዊው የህ.ወ.ሓ.ት አመራር ነው ።ኤርትራ የሸዋው አማራ መንግሥት ( ኢትዮጵያ ) ቅኝ ግዛት ሃገር ናት በማለት ቅስቀሳው የተጀመረው በ1964 ዓ.ም በወቅቱ ብሄረ ትግራይ ድርጅት እየተባለ በሚጠራበት በአረጋዊ በርሄ የሚመራ ፤የተጀመረ ቅስቀሳ ጊዜ ሲሆን ቅስቀሳውም እየተጠናከረ የመጣበት ጊዜም ነበር ፤ማ.ገ.በ.ት. እንደተፈጠረ ፤ከዛም ተ.ሓ.ህ.ት. ሲፈጠር በፕሮግራሙ ውስጥ አስቀምጦ ፤ለህዝብ ይፋ አድርጎታል ፤የዚሁ ሁሉ አዘጋጅ አረጋዊ በርሄም ነው ።ዋናው ። በካርታ የተደገፈ የኤርትራን ቅርፅ መሬት በመንደፍ አሰብን ያካተተ የኤርትራ መሬት ነው በማለት የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ኢትዮጵያን ለማጥቃት ለመጉዳት ከ1967ዓ.ም. መጀመሬያ አንስቶ በሙሉ አቅሙና ልft የተንቀሳቀሰበት ነው እስከ መጨረሻውም አደረሱት ፤በዚሁ ፀረ እትዮጵያ እኔ እጄ የለበትም የሚሉት የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ህዝብን ለማደናገር ነው ።በስማቸው ብንጠቅሳቸውም የሚበልጥ ይሁናል ። ዋናዋናዎቹ ።

1 ኧረጋዊ በርሄ 2 ስብሃት ነጋ 3 መለስ ዜናዊ 4 ግደይ ዘራፅዮን 5 አባይ ፀሃየ 6 ስዩም መስፍን 7 አርከበ ዕቁባይ 8 ስየ አብርሃ 9 ገብሩ አስራት 10 ፃድቃን ገብረተንሳይ     11 አረጋሽ አዳነ እነዚ የተዘረዘሩት የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ የደረሰውና እየደረሰ ያለው ችግር ተሸክሞዉት የመጡ ለተተኪዎቻቸውም ያስተላለፉት ፀረ እትዮጵያ አቋም እና ፖሊሲ ኢትዮጵያን ከህልውና ውጭ እያድረጋት ነው ።ዛሬ ኢትዮጵያ የባህር በር አልባ ዝግ ሃገር ሆናለች ። ከድርጅቱ የተባረሩት በ1977ዓ.ም. እና በ1993 ዓ.ም. መሪዎች ሆን በለው ኢትዮጵያና ህዝብዋን ለመጉዳትና ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ያደረግዋት ዛሬ ሳይሆን ትግሉን እንደተጀመረ በዙ የተንቀሳቀሱበት አሰብ የኤርትራ እንጂ የኢትዮጵያ አይደለም በማለት ፤ቀደም ሲል ብሄረ ትግራይ ድርጅት በኋላም ማ.ገ.ብ.ት. ተ.ሃ.ሓ.ት ህ.ወ.ሓ.ት. በወይን (ልሳናቸው ) መፅሄት የኤርትራን ካርታ በመፂሄቱ እየተሳለ አሰብን ያካተተ ፤ መፂሄቱ ለህዝብ በማሰራጨት ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ያደረግዋት ገና ከ967ዓ.ም. ነው ።ዛሬ እነዚህ በመለስ ዜናዊና በስብሃት ነጋ ከስልጣናቸው የተወገዱ ለኢትዮጵያና ለህዝብዋ ተቆርቋሪ በመምሰል እሥስቶች አሰብ የኢትዮጵያ ነው በማለት ይናገራሉ ።ይህን የሚዘላበዱበት ያፈሰሱት የንፁሃን ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ወንጀል ገና ስለሚጠየቁበት ይህን አረሜኔ ድርጊታቸው ለመሸፈን እንጂ ለኢትዮጵያና ህዝብዋ ተቆርቁረው አይደሉም ። ለምን ድሮ በከፍተኛ ስልጣን ወያኔ በሚመሩበት ወቅት አሰብ የኢትዮጵያ ነው ወደ ኤርትራ መቀላቀል የለበትም አላሉም ፤በዛን ሰዓት ቢሉ ኖሮ ፤ዛሬ አስብ በኢትዮጵያ እጅ ይገኝ ነበር።የወያኔ መሪዎች ይህን አይቀበሉትም በአደራ የተቀበሉት                       ተልእኳቸው ፀረ ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያን አዳክመው ለመበታተን ፤ከዓለም ካርታ ኢትዮጵያ ተፍቃ እንድትወጣ ነው ፤የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ድርጅት የተሰጠው የግዳጅ ሃላፊነትም ይህ ነው

። ከሸጡት ከ44 ዓመታት አልፎታል ፤በመሰረቱም ማንም የወያኔ መሪ ስለ እትዮጵያ ለመናገር ማን መብቱ ስጠው ፤ ፀረ ኢትዮጵያ ስለ ሃገር ለመናገር አይችልም ።አሰብንም ሆነ አጠቃላይ በኤርትራ ጉዳይ የሚናገርው

 

የሚደራደረው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ተምስርቶ በህዝብ የተመረጠ ሥርአተ መንግሥት ሲቋቋም በዚሁ የሚፈፀም ብቻ ይሆናል ። ወያኔዎች እድሚያቸውን ለማራዘም የሚጠቀሙበት ዘዴ በስብሶ ሻግቶ ኋላ ቀር ውዳቂ ከሆነው ረጅም ጊዜ አስቆጠረ ፤እንደዚሁ የወያኔ መሪዎች ደጋፊዎች ተግባራቹህን ስራቹህ ተጋልጦ ዘራፊ ሽብርተኞች ፀረ ሃገርና ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ መሆናቹ ተረጋግጦ ከታወቀ በዙ ዓመታት አስቆጥረዋል ፤ ስለሆነም ማንም የወያኔ መሪ የነበረ አሁንም ያሉት፤ በኢትዮጵያ ጉዳይ ለመናገር ለመደራደርም ሆነ ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ መናገር መብት የላችሁም ፤ ቅኝ ገዢ ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ናቹህ ። የኢትዮጵያ ህዝብ በንቃተ ሂሊናው እናንተን አልፎ ከናንተ በርቀት እየመራ ነው ፤አትደርሱቱም፤ በናንተ ውሸትና ማደናገሪያ የሚታለል እትዮጵያዊ የለም ።ማንነታቹን   ታውቀዋል።

ወያኔዎች በ1969 ዓ.ም የሱማሊው  መሪ መቃድሾ የነበረው መሪ ፕረዚዳንት  ዛይድ ባሬ ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የተ.ሓ.ህ.ት. መሪዎች 1 አረጋዊ በርሄ የድርጅቱ ሊቀ መንበር 2 ግደይ ዘራፅዮን 3 ስብሃት ነጋ 4 አባይ ፀሃየ          5 ስዩም መስፍን                               6 መለስ ዜናዊ 7 ስየ አብርሃ አዋአሎም ወልዱ በማስተባበር ለሱማሊያ መንግሥት ድጋፍ በመስጠት ከጠላት ጋር በመተባበር ከነበራቹ ታጋይ ሁለት ሃይል ( ሁለት ሻምበል )ልካቹህ እነዚህን የሚመራ ስየ አብርሃ ከሱማሊው ወራሪ ጠላት ጎን ተሰልፋቹህ ኢትዮጵያን የወጋቹህ የወያኔ መሪዎች ከጠላት ጎን ተሰልፋቹህ የኢትዮጵያ የሃገር መከላከያ ሠራዊት የወጋችሁት የገደላችሁ እናንተ ናቹህ የሱማሊው መሪ ዘይድ ባሬም ለፈጸማችሁት ታማኝነት ብዙ ካላሽን ኮፍ መሳሪያ ከነ ጥይቱ ፤ የእጅ ቦምብ ፤ፀረ መኪና በመንገድ የሚቅርበር ፈንጅ ፤የእጅ ቦምብ ቦምጠቃቹህ ።ባ ቻይና ተብሎ የሚጠራ መትረየስ ከነ ጥይቱ ዛይድ ባሬ አሳጠቃቹህ ።ከጠላት የታጠቃችሁት መሳሪያና ጥይት የኢትዮጵያን ህዝብ ገደላችሁበት ለሰላማዊ ዜጋ ማጥቅያ ዋለ ። የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ያልፈጸሙት ወንጀል የለም ፤ሁሉ አድርገዋል የአንዲት ሏላዊት ሃገር ኢትዮጵያ ፤በማንም ውክልናም ሁነ እውቅና ያላገኛቹህ ተራ ወረበላ ዘራፊዎችና ሽብርተኞች ሁናችህ ስትንቀሳቀሱ በነበራቹህ ወቅት ለመሰረታችሁት ድርጅት ፤ለራሳቹህ ጊዚያዊ ጥቀ ለማግኘት ብላችሁ ምንም ማንነታቹህ እንኳን በማይታወቀበት ጊዜን ወቅት የአንዲት ሏላዊት ኢትዮጵያ ሕገ ወጥ በሆነ የወንጀል ድርጊት በ1975 ዓ.ም. ለሱዳን መንግሥት ለጊዚያዊ ጥቅም ስትሉ ሏላዊነት በመፃረር በጣም ሰፊ ፤ረጅም ፤ታሪካዊ ፤ ለም መሬት፤ ለሱዳን መንግሥት የሸጣቹህ ፤እናንተ የወያኔ መሪዎች ናችሁ ፤ይህ ነገር ዛሬ የሱዳን መንግሥት የራሴ መሬት ነው በማለት ከወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. በመተባበር በአማራው ህዝብ                           በመተማ በላይ አርማጮህ በታች አርማጮህ ወ.ዘ.ተ. እይደረሰ ያለው ግፍና መከራ ሁሉ ኢትዮጵያዊ የሚከታተለው ነው ። ለዚሁ የሃገርና የህዝብ ከህደት ፈፃሚዎች በወቅቱ የነበሩ አመራር ይህም ከሱዳን መንግሥት ተባብረው ለፍጻሜ ያደረሱት ፤ የሱድን መንግሥት የጠየቀው የመሬት ይገባኛል ትክክል መሆኑ አምነን የትግራይ መንግሥት ከተቋቋመ ተግባራዊ እናደርጋለን ፤በለው የፈረሙት የወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት.መሪዎች ።

1ኛ አረጋዊ በርሄ ዋናው አስተባባሪ 2ኛ ግደይ ዘርአጽዮን       3ኛ ስብሃት ነጋ  4ኛ አባይ ጸሃየ  5ኛ መለስ ዜናዊ

6ኛ ሥዩም መስፈን ናቸው ።እነዚህም ሁሉ በወያኔ የተፈጸሙ ወንጀሎች ፤እየተፈጸመ ያለው ወንጀል ግንባር ቀደም ወንጀለኞች ሆነው ተጠያቂ ናቸው ።

ሌሎችም በ1993 ህወሓት ለሁለት የተሰነጠቀበት ዋና ምክንያት በሥልጣን ሽኩታ እንጂ ለሃገርና ህዝብ ተቆርቋሪ ሆነው አይደሉም ፤ ኢትዮጵያን ያፈረሱ የህዝብ አንድነት የበተኑ ናቸው ። እነ ስየ አብርሃ፣ ገብሩ አስራት አረጋሽ አደነ አውዓሎም ወልዱ ፃድቃን ገ/ተንሳይ አበበ ተክለሃይማኖት ወዘተ ማገብት-ትሓህት- ህወሓት አባሪና ተባባሪ በመሆን የተዘጋጀውን አገርና ሕዝብ በታኝ ፕሮግራም በማጠናከርን በማዘጋጀት ሰፊ ሚና ያበረከቱ መሪዎች ናቸው። ዛሬ ተመልስው ሕዝብ ለማደናገር፣ እኛ የተባረርነው ለኢትዮጵያ ሉአላዊነት፣ ለሕዝብ አንድነት በመቆማችን ነው እያሉ በመደጋገም ይዋሻሉ። በመሰረቱ ተሓህት-ህወሓት ሲመሰረት ትግራይን ለመገንጠል ነው። ይህን መሰረት በማድረግ እስከ 1981 ድረስ የሰሩት ለኢትዮጵያ ሳይሆን ትግራይን ለመገንጠል ነው። ይህ በዚህ እንዳለ፣ ብ1982 መጀመሪያ አሜሪካና ምእራባውያን የደርግ ስርዓት መወገድ አለበት በሚለው ፖሊሲያቸው፣ ህወሓትን በሰፊው በወታደራዊ አማካሪነትና በገንዘብ በወታደራዊ ትጥቅ በመርዳትና በማገዝ ህወሓት ወደ ‘የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) የሚል የውሸት የስም ለውጥ አድርጎ በአሜሪካና በእንግሊዝ መንግስታት ሙኡ ድጋፍ አገኘ፤ ህወሓት ከግንቦት 20፣ 1983 ጀምሮ ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት እንዲቆጣጠራት አደረጉ።

 

ህወሓት ገና ትግሉም ሳይጀመርን ከተጀመረም በኋላም በኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ሀገሪቷን ለመበታተን እንዲሁም ሕዝቧን ተከፋፍሎ እርስ በርሱ ደም መፋሰሱ እንደማይቀር በወቅቱ የነበሩ አመራር አረጋዊ በርሄና ጓደኞቹ ባወጡት ፕሮግራማቸው በግልጽ አስቀምጠዋል። በዚሁ መሰረትም በየካቲት 1968 ይፋ ያደረጉት በግልጽ አስቀምጠውታል። ይህ የህወሓት ፕሮግራም ዛሬም የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት ሆኖ መቀጠሉ በኢትዮጵያ ሏላዊነት ፤በህዝft አንድነት እያደረሰ ያለው ሶቆቃ እስራት የድህነት ችግር ሰላም ጠፍቶ ወረራና ርሃብ የኑሮ ጉስቁልና መኖሪያ አጥነት ኢትዮጵያዊ ዜግነቱ ተገፎ ኢትዮጵያዊ ማንነት ተነጥቆ ፤ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ በፋሽሽቱ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ስርአት በብረት ሰንሰለት ታስሮ የቁም ስቃዩ እያየ ያች ለምለም ኢትዮጵያ አጠገft የለችም ።

 

በህወሓት አመራርነት ለረጅም ጊዜ ስልጣን ጨብጠው የነበሩ በሥልጣን ሽኩታ የተባረሩ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን በማለሊት ምስረታ ጉባኤ ሳያስftት ድንገተኛ ዱብ እዳ ሲወርድባቸው የመለስ ዜናዊና፣ ስብሃት ነጋና ተባባሪዎቻቸው እነዚህ ሁለት ግለሰቦችን አባረሩ። ቀጥሎም በቀሩት የህወሓት አመራር በውስጣቸው ሲቀጣጠል የቆየው የሥልጣን ሽኩቻ በ1993፣ ስየ አብርሃ፣ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ተወልደ ወ/ማርያም፣ አውአሎም ወልዱና አለምሰገድ ገብረአምላክ እነዚህ ሁሉ የህወሓት ፖሊት ቢሮ የነበሩትም በመለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋና ሎሎች የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት በማሰባሰብ ተባረሩ። ከላይ የተጠቀሱት እነ አረጋዊ በርሄና የነ ስየ አብራህ ftድን በድርጅቱም ሆነ ድርጅቱ የሚፈጽመው ፀረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ከነ መለስ ዜናዊ ልዩነት ቅንጣት ታህል አልነበረባቸውም አሁንም ፀረ ኢትይዮጵያ ናቸው ። ልዩነታቸው ግለሰብ ከግለሰብ ጥላቻ ሊኖራቸው ይችል ይሆናል ። ይህ ጥላቻም የስልጣን ሽኩቻ ነው። አረጋዊ በርሄ፣ ሰየ ወዘተ ተባራሪዎች ትልቁ ፍርሃትና ስጋት የህወሓት ቅኝ አገዛዝ ስርአት ከኢትዮጵያ እንዲወገድና እንዲባረር አይፈፍልጉም። በእነዚህ ከድርጅቱ የተባረሩ አንጋፋ አመራር የነበሩ ትልቁ ጽንሰ ሃሳባቸው ህወሓት ከኢትዮጵያ ሥልጣን እንደያዘ ለረጅም ዓመታት ሳይሆን ለዘመናት መምራት አለበት ይላሉ። ከሚያቀርftት ምክንያት ኤርትራ ጨምሮ፤

  1. ኢትዮጵያ ነፃ ያወጣናት እኛ የህወሓት አመራርና ነን ፣
  2. የብሄር ብሄረሰብ መብት አስከብረናል፣ ማንም ብሄር ብሄረሰ ከፈለግ ከኢትዮጵያ ይኑር አልኖርም ካለም የመገንጠል መብቱን አጎናጽፈናል፤ በቋንቋው እንዲካለል ፤በቋንቋ እንዲናገርና እንዲጽፍ አድርገናል፣በኢትዮጵያ ከነበረው ባርነት ነፃ አውጥተነዋል ፤
  3. ከላይ የተጠቀሱትና አሁንም በአመራር ላይ ያሉት የህወሓት አመራር አሁን የሚጠቀሙበት ሕገ መንግሥት በሌላ መተካት የለበትም የሚል እምነት አላቸው። ይህ ህወሓት ያወጣው ሕገ ሕገ መንግሥት ከተቀየረ እኛ መስዋእትነት ከፍለን ያመጣነው ነፃነት ይወድቃል። ስለዚህ ሕገ መንግሥቱን መከላከል አልብን የሚል እምነት አላቸው። ዋናው ምክንያት ለሕገ መንግስቱ መቆየት የሚከራከሩት ትልቁ ሃሳባቸው የፈጸሙት የሰሜን ጎንደር የስሜን ወሎ የመሬት ወረራ ሌላ ስርአት ሲመጣ ወደ ቀድሞ ይዞታው ስለሚመለስ ፤፟ በሕዝብ ላይ የፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጄል ተይዘው ለፍርድ እንደሚቀርft ፤ ይህ ብቻ ሳይሆን በስንት መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ዜጎች በተለያዩ አሰቃቂ ዘዴዎች፤ በጢስ አፍኖ መግደል፤ በመርዝ፤ በጋለ ብረት ሆድ እቃው ውስጥ በምስገባት እጅና እግሩ ከግንድ አጣብቀው  በማሰር ለ48 ስአታትበማሰቃየት ፤ ደም ተፍቶ እዛው በታሰረበት ግንድ ሞቶ ደርቆ የቀረ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ፤ ውጭ በማሰር በብርድና ፀሃይ አስቃይቶ መግደል ፤ በውሃ ጥም በአስርቦ መግደል ሰው ጨርሰዋል ፤ አስቁመው በሳንጃ ከሚቀበርበት ጉድጓድ አስጠግቶ መግደል ስንት የሰው ፍጡር ገድለዋል፤ በዓለም ህዝብ ፊት የወያኔ መሪዎች የሚያጋልጡ ብዙ ናቸው ፤ ከ1968ዓ.ም. የወያኔ መሪዎች የፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ማለቂያ የለዉም እንደሚጋለጡም እነሱም ያውቃሉ ጥርጥር የሌለው ሃቅ         ነው። ከዚህ በመነሳት የወያኔ ሀወሓት ስርዓት ከወደቀ መሪዎቹ ሁሉ ታፈሰው የታሰራሉ፣ ከባድ እርምጃም ይወሰድባቸዋል። በሰፈሩት ቁና ስለሚሰፈሩ ሕይወታቸውን ለማዳን የሚያደርጉት የጭንቀት ሃሳብ ነው፣ ዛሬ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ ማስለው እነ አረጋዊ

 

በርሄ ፤በየስብሰባው ይናገራሉ ፤አልሞትኩም ብየ አልዋሽም የሚል ህሊና የላቸውም ፤ የሚልዮኖች ህዝብ ኢትዮጵያውያን የፈሰሰው ደም ግን በእግዚአቢሄር ፊት እየጮህ ነው ያለው ፤ከነ አረጋዊ በርሄ ስየ አብርሃ ግደይ ዘራጽዮን ለስብሰባ የሚቀመጡ ሰዎች ግን ያሳዝናሉ እነሱ ባይገደሉም በእነ አረጋዊ የፈሰሰው ደም ገን ፤የራሳቸው ወገን ኢትዮጵያዊ ነው ።

  1. ኢትዮጵያን ወደ መፈራረሰዋ በምትሄድበት ወቅት ህወሓት በፍጥነት ደርሶ ከአደጋው አድኗታል ብለው ያቅራራሉ ይናገራሉ ፤ ኢትዮጵያን ያፈረሳት ግን ይኸ ደመኛ ጠላት ቅኝ ገዢ፣ፋሽሽት ስርአት ወያኔ ነው ።እትዮጵያ አልፈረሰችም ነበር፤ ኤርትራን አስገነጠለ የቀይ ባህር ባለቤትነትዋ የባህር በርዋን ያሳጣት ወያኔ ነው ።ከዚህም ለጊዚያዊ ጥቅም ብሎ የኢትዮጵያ ለምና የታሪክ ቦታዎች ለሱዳን መንግሥት አሳልፎ በመስጠት ዛሬ ኢትዮጵያ ለከፍተኛ ውዝግብና ወረራ ተዳርጋለች ።
  2. ኢትዮጵያን ለከፍተኛ ልማትና ለሰፊ ዲሞክራሲ ያደረሳት ህወሓት ነው ብለው ይመጻደቃሉ። ይህ አባባል ከወያኔ ደናቁርት ቢሰማ ብዙም አያስደንቅም ።ልማት ካለህዝብ ተሳትፎና ካለዲሞክራሲ ሊመነጭ አይችልም ፤ወያኔ በተፈጥሪያዊ ባህሪው ፀረ ዲሞክራሲ ፀረ ህዝብ ነው

።ኢትዮጵያዊ ህዝብ ሁሉ መሬቱ ተነጥቆ መኖሪያ ቤቱ ተነጥቆ አርሶ የሚበላበት መሬት የሌለው የሚኖርበት ቤት የሌለው በመንከራተት በጉስቁልና በረሃብ የሚኖር ህዝብ ነው ፤ካለ ህዝብ ተሳትፎም ልማት ማሳደግ መበልፀግ ዘበት ነው ፤ስለዚህም ወያኔ ልማት ሊያመጣ ወይ ልማት ለማሳደግ አይችልም ። ከህዝብ እየነጠቀ ለባእዳን እና ለደጋፊዎቹ እየሸጠ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ለልመና የዳረገ የወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት የወረበሎች አገዛዝ ኢትዮጵያን ለውድቀት አሳልፎ የሰጠ ፋሽሽት ስርአት ለልማት አይበቃም ።

  1. ስለ አሰብ ጉዳይና ስለ ቀይ ባህሩ ትንሽ ልጨምርበት ከላይ በተለያዩ ቦታዎች በስፋት ተገልፀዋል ይህን የኢትዮጵያ ግዛት ከእናት አካሉ ተገንጥሎ እንዲሄድ ያደርገው በዋናነት ተጠያቂው የህ.ወ.ሓ.ት አመራር ነው ፤በግንቦት ወር 1983 ዓ .ም . መጀመሪያ 1 ሻዕብያ 2 ህ.ወ.ሓ.ት. 3 ኦ.ነ.ግ 4 ደርግ ፤ሶስቱ ድርጅቶች ከደርግ ለሰላም ውይይት ታስቦ የነበረው ፤በእንግሊዝና በአሜሪካ ወያኔ ወደ ኢትዮጵያ ሻዕብያ ወደ አስመራ ኤርትራ ስልጣን እንዲይዙ ሁለቱ ሃገራት ማለት አሜሪካና እንግሊዝ ሲወስኑ ፤አስቀድሞ ያዩት አሰብ የኢትዮጵያ ግዛት የነበረው በወሎ ግዛት ሲተዳደር የነበረ መሆኑ ከኤርትራ የማይገናኝ ፤ስለሆነም የኢትዮጵያ የባህር በር ነው ተብሎ ሲወሰን ሻዕብያዎች ካለ ምንም ተቃውሞ ሲቀበሉት ፤የወያኔው መሪ መለስ ዜናዊ ይህን በሰማ ጊዜ ተናዶ አሰብ የኤርትራ ነው ፤የኢትዮጵያ አይደለም ፤ይህን የምትሉ ከሆናችሁ ስብሰባውን ረግጠን እንወጣለ ፤ብሎ ከሱ ጋር የነበሩት የወያኔ አመራርም የመለስ ዜናዊ ሃሳብ በመደገፍ ፤አሰብ የኤርትራ ነው በለው ደገፉት ፤እነዚህም 1 ስዩም መስፍን 2 ብርሃነ ገብረክርስቶስ 3 አሰፋ ማሞ ናቸው ። በእነዚህ ተቃውሞ አሰብ ከኢትዮጵያ ተነስታ ወደ ኤርትራ ተጨመረች ።ይህ በዚሁ እንዳለ በትግራይ በረሃ የነበሩ ከፍተኛ አመራሮች ይህ የተከሰተው ነገር በሬድዮ መገናኛ ተላልፎ ሲነገሩ የእነ መለስ ዜናዊ ሃሳብ በመደገፍ አሰብ የኢትዮጵያ አይደለም፤ የኤርትራ ነው ፤የታገልንበትም ነው ፤የኤርትራ መሬት መነካት የለበትም በማለት ጠንካራ የድጋፍ መለክታቸው አስተላለፉ ።እንዚህም 1 ስብሃት ነጋ 2 ገብሩ  አስራት 3 ፃድቃን ገብረተንሳይ 4 አረጋሽ አዳነ 5 አዋዓሎም ወልዱ 6 አርከበ ዕቁባይ 7 ስየ አብርሃ ሲሆኑ በተጨማሪም ኤርትራ እንደተገነጠለች ከፍተኛ መተባበር ሲያደርጉ የነበሩ ናቸው ። ወያኔ አንድ የድንቁርና ባሪ የኧምሮ ስንኩልነት አለው ፤ለወደደው ስማይ ይሰቅለዋል ለጠላው ደግሞ መጥፎ ስም ሰጥቶ ሲያበሳብሰው ይታያል ፤ሻዕብያና ወያኔ ጠላት ናቸው ፤ወያኔ የኢትዮጵያ ህዝብ አደናግሮ ዋሽቶ አጭበርብሮ ፀረ ሻእብያን አሰልፈዋለሁ የሚል ቅዠት አድሮበታል ፤ለዚሁም ቱጃሩ ነጋዴው ፃድቃን ገብረተንሳይ ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ነው ፤አሰብ በጦርነት ወደ ኢትዮጵያ እናስመልሳት አለን እያለ ቱልቱላው ይነፋል ፤የዚሁ ዋና ምክንያት የወያኔ እድሜ ተመናምኖ ተዳክሞ ወደ መቃብሩ እያመራ በመሆኑ ፤ትንሽ የእድሜ ጥገና ከተገኘ

 

ተብሎ የታሰበ ነው ።ከሻዕብያ የተጠጋ በወያኔ የሚከሰሰው በሽብርተኛ ነው ፤የራስዋ ጉድ ያላየች የሌላው ታማስላለች የተባለው የወያኔው አይነቱ ነው ፤በሽብርተኝነት የተፈረጀው ህ.ወ.ሓ.ት. ነው ።ከወያኔ የተባረሩትም መሪዎችም የወያኔ አሳብ ደግፈው ክሻዕብያ የተጠጋ ሁሉ ሽብርተኛ ይሉታል ፤በተለይ በዚሁ ውገዛ ይተጠሙዱ ስየ አብርሃ አረጋዊ በርሄ ግደይ ዘራጽዮን በሰኔ 2017 በE.C.T. ETHIOPIAN TEGARU PALTALK በወያኔ በጀት የሚንቀሳቀስ አቤል በሚባል የወያኔ ካድሬ ጋባዥነት የተናገርው አርበኞች ግንቦት 7 እና ሌሎቹም በኤርትራ ያሉቱን ሁሉ አወገዛቸው ፤ድሮ ገና ትግሉ ከመጀመሩ በፊትና ትግሉ እንደተጀመረ እሱ ራሱ አረጋዊ በርሄ የሻዕብያ አፍቃሪ ታማኝ አሽከር ሆኖ የቆየ እስከ ተባረረ ዕለት ነበር ፤ ስለ ኤርትራ ነፃነትም የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት እያለም ከኤርትራውያን በላይ ጥብቅና ቆሞ ሲከራከር የተሟጋች ሰው ዛሬ ኢርትራ ውስጥ ከለላ ያገኙ ድርጅቶችን ማውገዝና መወረፍ ምን አመጣው ። አንድ ሓቅ ግን አለ የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች አረጋዊ በርሄ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ አባይ ፀሃየ ስዩም መስፍን ግደይ ዘራጽዮን ስየ አብርሃ ፃድቃን አውዓሎም ወዘ.ተ በህዝብ የፈፀሙት ወንጀልና ግፍ በሕግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑ ያውቃሉ ፤ከዚሁ በመነሳት የወያኔ ስርአት ለመጣል የሚንቀሳቀሱ ኋይሎች ከማውገዝ ትግሉን ለማደናቀፍ የማይቆፍሩት ጎድጓድ የለም ።                      ወያኔ ከወደቀ በሕግ ተይዤ ለፍርድ ከመቅረብ የወያኔ ዕድሜ ማራዘም የበለጠ ነው ፤ብለው ስለሚያምኑ ነው ፤ነገር ግን እነሱ ተናገሩ አልተናገሩት የሚያመጡ ለውጥ የለም በሰሩት በፈጸሙት አሰቃቂን ግፍ በተሞላበት ወንጀላቸው ተጠያቂ ናቸው ፤እንደ መለስ ዜናዊ ቢሞቱም ይጠየቃሉ ፤ዘር ያጠፋ፤ ህዝብ በአሰቃቂ ሁኔታ የፈጀ ሽብርተኛ ይኑር አይኑር በነጻ አያልፍም ። በታሪክ ማህደርም ለዝንተ ዓለሙ በጥቁር ምግባሩ እየተከሰሰ ይኖራል

። የኢትዮጵያ ህዝብም እነዚህ አረሜኔ ፋሽሽት ወያኔዎች ካለ ምንም ርህራሄ ተከታትሎ ለፍርድ ማቅረብ ግዴታው ነው ። ዛሬ የተነሳው ህዝባዊ ማእበል ፀረ ወያኔ በነዚህ ፋሽሽት ወንጀሎኞች አይቀለበስም ።

  1. ህ.ወ.ሓ.ት. እና ኢትዮጵያ

 

   ህ.ወ.ሓ.ት.እና የመስፋፋት ዓላማው

ወያኔ ህወሓት የኢትዮጵያን ሉአላዊነት፣ የሕዝftን አንድነት ፍቅርና ሰላም በማደፍረስ ህብረተሰftን አጋጭቶ ከፋፍሎ የመግዛት ዘዴውን ለማሳካት ያወጣው ፖሊሲ እጅግ አደገኛ ነው። ይህንን እኩይ ተግባሩንም በሥራ ላይ እያዋለው ይገኛል ። ወያኔ ህወሓት በፕሮግራሙ ቀርጾ በተግባር ያዋለውና በትገሉ ጊዜም በስፋት የተንቀሳቀሰበት ጉዳይ ነው። ይህ ድርጅት ኢትዮጵያ እገዛለሁ የሚል ህልም አልነበረውም ፤ፈፅሞ አይገምተውም ነበር ። የድርጅቱ ዋና አላማ ትግራይን አስገንጥሎ ፤ የትግራይ ሪፓብሊክ መንግስት መመስረት ሆኖ ፤እየታገለለት የመጣውም ለዚሁ ነው ። በጊዜውና በተፈጠረው አጋጣሚ ግን ለወያኔ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮለታል ፤ አሜሪካና እንግሊዝ የያዙት ፖሊሲ የደርግን ስርአት ማስወገድ ብለው የሚከተሉ የአቋም እርምጃ ተከትለው ፤ደርግን ስናስወግድ ኤርትራም ነፃነትዋ ስለምትቀዳጅ በኢትዮጵያ ደግሞ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ካስቀመጥነው ለአሜሪካ መንግሥት ጥቅም እጅጉ ጠቃሚ ነው ፤ የአፍሪካ ቀንድ በቀላሉ በአሜሪካ መንግሥት እጅ ቁጥጥር ይሆናል ፤ህ.ወ፣ሓ.ት. ብቻው ከገባ ህዝft ችግር ይፈጥርበታል ከኢትዮጵያ መሰል ድርጅት መተባበር ግን ጠቀሜታ አለው በህዝብ ተቃውሞ ቢፈጠርም ችግሩ ይቀንሰዋ በማለት የአሜሪካው የሲ.አይ.ኤ ( C.I.A..)ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከወያኔ መሪዎች መለስ ዜናዊ ፤ስብሃት ነጋ፤ ስየ አብርሃ ፤አባይ ጸሃየ ፤ገብሩ አስራት ፤ሥዩም መስፍን ፤ተወልደ ወልደማርያም ፤አውዓሎም ወልዱ ፤ ፃድቃን ገብረተንሳይ ፤ወ.ዘ.ተ. ተማክረው    ከኢ.ህ.ዴ.ን. ( የኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ) በወቅቱ በታምራት ላይኔ በረከት ስምዖን፤ህልዊ ዮሴፍ ፤ዮሴፍ ረታ ታደስ ካሳ ወ.ዘ.ተ. በትግሬዎችን በኤርትራውያን ሲመራ የነበረው ዛሬ በደመቀ መኮንን የሚመራ ፀረ አማራ ድርጅት ተላላኪ ftዱን ፤ ጊዜው ሓምሌ ወር 1981 ዓ.ም. ነበር ስሙን ለውጦ ብ.አ.ዴ.ን. ተባለም ይህ የተላላክ ድርጅት በወቅቱ የነበረው የሰዉ ብዛት ከ80 ሰው የማይበልጥ በጣም

 

ደካማ  ። በ1972 ዓ ም  በአምሳላቸው .ጠፍጥፈው የፈጠሩት ግኡዝ ftዱን  ለወያኔዎች ግን ለኋላ ኋላ እየጠቀማቸው የመጣ ብ.አ.ዴ.ን.፤  የትግራይ ግዛት ለማስፋፋት ፤ለሱዳን መንግሥት በ1975 ዓ.ም. ለጊዚያዊ ጥቅም ብለው የሸጡት    ለምና በጣም ሰፊ የኢትዮጵያ መሬትና ግዛት በወያኔ ተላልፎ የተሰጠው ለመስጠት ተባባሪም በመሆን ፤ፀረ ተውልዶ ላደገበት ግዛት ።ይህ ሆኖ ግንባር ፈጥረው ፤ አብረው ኢትዮጵያ ቢገft ይበልጣል ብለው ባወጡት እቅድ ፤ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ትም ይህች እጅ ነስቶ ተቀብሎ በፍጥነት ጊዜና ቀናት ሳይጨርስ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ( የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሳዊ ግንባር ) እኛ ለኢትዮጵያ ብለን የቆም ነን ብሎ በማጭበርበር በማታለል ህዝብ በማወናበድ ፤ለነ አሜሪካና እንግሊዝ በማሳወቅ ፤ደግፉን እርዱን የናንተው ፖሊሲ እናራምዳለን ኢትዮጵያም እንበታትናት አለን ብሎ ቃል የገባው ወያኔ ፤ዛሬ የትግራይ ግዛት በማስፋፋት

፤ሲዳሞ ጫፍ ደረሰ ።በአሚሪካ በእንግሊዝ ፤ ድጋፍ በለሱን ቀንቶት ካለምንም ችግርና ጦርነት ፤ ወያኔ ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ስርዓቱ ተቆጣጠራት ፤ ኤርትራን አስገንጥሎ ኢትዮጵያ ታሪካዊ ግዛቷ በህረነጋሽን በማሳጣት የቀይ ባህር እመቤት እየተባለች እንዳልተጠረች ሙሉ በሙሉ የባህር በሯን በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም.አጣች ፤ ይህም የሆነው ካለ ምክንያት በድንገት የተፈጠረ ሳይሆን ወያኔ ገና በረሃ ወጥቶ ትግል ከመጀመሩ በፊት ማ.ገ.ብ.ት እየተባለ በሚጠራበት ወቅት ለኤርትራ ነፃነት በሞቆም ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት በአማራው መንግሥት የተወረረች ናት እያሉ የቆሙበት ጊዜ ፤ቀጥሎም ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. እንደተመሰረተም የትጥቅ ትግሉ እንደተጀመረም በዚሁ በመቀጠል ለብዙ አመተት የቆሙለት አላማቸው ነው ። የትግራይ ማስገንጠል እንደተጠበቀው ሆኖ ለጊዜው በአዳሪ አስቀመጠው ፤ መጀመሪያ ኢትዮጵያ ሃብትዋና ንብረትዋን እንዝረፍ ፤ህዝብዋም እርስ በራሱ እናጋጨው፤ አማራውም ተመናምኖ ይወድቃል ፤                                                                                      ቀጥሎም በጣም ሰፊና ለም መሬቷ ለሱዳን መንግሥት ከተሰጠ ሱዳን ያገኘው መሬት ለመከላከል ብሎ የአማራው መንቀሳቀስ ያዳክማል አማራ ተዳክሞ ይወድቃል በዚሁ ህልውናው ያበቃል ። ሕዝftን በዘርና በቋንቋ ክልል

ከተበታተነ አማራውም ካዳከምነው ፤ሃገር የለም ህዝብ የለም ኢትዮጵያዊነት አብሮ ይጠፋል ፤                    ኢትይጵያም ተሸንሸና ትጠፋለች ።የትግራይ የቆዳ ስፋት፤ ላይ አርማጮህ ታች አርማጮህ ሌላ ቦታም ተጨምረው በእጅጉ ይሰፋል ፤እነዚህ ቦታዎች ለም ድንግል መሬት ናቸው ፤ ከዚህ ባልትለየ፣ ጠባft፣ ጎጠኛው ወራሪ የፋሽስት ስርአት ከ1983 ጀምሮ በፕሮግራሙ መሰረት የሰሜን ጎንደርን፣ ወልቃይትን፣ ጠገዴን፣ ጠለምትን፣ ቃፍታ ሁመራንም እና የሰሜን ወሎ ለምና ሃብታም መሬት ከአለ ውሃ ምላሽ አንስቶ በዙ ሰፊ ለም መሬት ወደ ትግራይ ጠቀለለ ከአፋር መሬትም በመአድን ይዞታቸው የሚታወቁ ወደ ትግራይ አካለለ ነጠቀ፤                                           በትግራይ ካርታም አካተተ። ወያኔ መስፋፋቱን ቀጠለ ፤ከዚህም አልፎ ወያኔ እስከታች በመስፋፋት ቤኒሻንጉል ድረስ፣ አልፎም አዋሳ ድረስ ፤ ግፈኛው ወያኔው የትግራይ ግዛት በማለት ተስፋፊነቱን እየቀጠለ ይገኛል ። የወሉ ህዝብ       ለዘመናት በእጁ የነበሩት ለም መሬቶችም ራያን አዘቦ ቆቦ፣ አፍላ ደራ. ወልዲያ፣ ሰቆጣ ወዘተ ሲሆኑ እነዚህም ለወሎ ህዝብ የማንነቱ መግለጫዎች ናቸው ፤ዛሬ በህ.ወ.ሓ.ቱ ፋሽሽት ስርአት ተነጥቆ                                 የወሎ ህዝብ ለድህነትና ለችግር ዳርጎታል ፤ህዝft ሃብቱ ልማቱ እነዚህ ነበሩ ።፣ ተስፋፊው ፋሽስት ህወሓት ኗሪዎችን በማፈናቀል የመሬት ወረራ ሲፈጽም ነዋሪ ህዝftም ለስደትና ለችግር ተዳርጎ መሬት አልባ ማንነቱ የተገፈፈ ህዝብ ሆኖ ቀረ    ፤ማንነት የሌለው ህዝብ ደግሞ ዜጋ ሳይሆን መጤ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ነው የሚሆነው ፤እነዚህ ግን ኩሩ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ ሃገራቸው ናት ፤ ህ.ወ.ሓ.ት ግን ኢትዮጵያውያዊ ሳይሆን ወራሪ ፀረ ኢትዮጵያ ቅኝ ገዢም ነው ። በኢትዮጵያዊ ሁሉ                                    እየፈጽመ ያለው ግፍ በደል በኋላ በራሱ ላይ ይወድቃል ። ድርጊቱም የወያኔ ማንነት እያጋለጠ ነው ፡ ውድቀታቸውም እያፋጠነው ይገኛል ። በኢትዮጵያ ሃያል ህዝብ እጅ ስለሚወድቁ የሚያድናቸውም የለም ። ለሁሉም ጊዜ አለውን ፤ሩቅ ሳንሄድ ባጭር ጊዜ የወያኔ ውድቀትና በኢትዮጵያ ህዝብ እጅ እንደሚወድቅ ፍርዱም ከህዝብ የሚሰጠው እናያለን ።

 

 

በዚሁ የመሬት ወረራ ህወሓት የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመ ድርጅት ነው ። በአጠቃላይ በፕሮግራሙና በተለያዩ መጽሔቶቹ፣ በተለይም ወይን በሚባለው መጽሔቱ ጠቅላላው አማራ ደመኛ ጠላት ብሎ በመፈረጅ መጥፋት እንዳለበት አስረግጦ የተናገረበት ገና ትግሉ ሳይጀመር ነው። ትገሉ እንደተጀመረም ያንኑ አቋሙን ከ1969 ጀምሮ በተግባር ላይ አዋለ። በታህሳስ 1972 በእነ አረጋዊ በርሄ የሚመራው ድርጅት ህወሓት በሰሜን

 

ጎንደርና በሌሎች የጎንደር አካባቢ የአማራን ዘር በማጥፋት ከሚሊዮን በላይ ሰዎች በመግደል ዘራቸውን ለማጥፋት በስፋት ዘመተበት ፤ይህ የዘር ማጥፋት የወንጀል ድርጊቱ ቀጠለበት ፤ስልጣን እንደያዘም በከፋ መልኩ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖረ ኢትዮጵያ አማራ በመለስ ዜናዊ እየተመራ በብ.አ.ዴ.ን. ሥራ ፈጻሚነት ተግባራዊ የግድያ ስሚሪት አማራው በተለያዩ በገዛ ሃገሩ የሚኖረው ተገደለ ጠፋ ። በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የጠፋውና የተገደለው አማራ ከ5 እስከ 7 ሚልዮን መድረሱን የተለያዩ መረጃዎች በግልፅ ያመለክታሉ በሌላ እስታክቲስ የተገኘ መረጃ እንደገለጸው  ደግሞ የሚያሳየው ህ.ወ.ሓ.ት ትግሉን ከጀመረበት ከ1969 ዓ.ም አንስቶ ወያኔ ሃገር ወሮ በቅኝ አገዛዝ ስርአቱ ኢትዮጵያ ከገባች እስከ 1985 ዓ ም በተካሄደው ህዝብ ቆጠራ 3 ሚልዮን ( ሶወስት ሚልዮን ) አማራ መጥፋቱ ።

በ1998 ዓ.ም .በተደረገው ህዝብ ቆጠራ 6 ሚልዮን አማራ መጥፋቱ ያመልክታ ይህ ሁሉ አማራ በህ.ወ.ሓ.ት እጅ የተገደለ መሆኑ ለማረጋገጥ በቂ አሳማኝ ማረጃዎች ይገኛሉ ። በቂ አስተማማኝ ማስረጃዎች አለ ።ጊዚው ይመጣል ሩቅ አይደለም ፤የመሬት የጅምላ መቃብር ፤የሰው ማስረጃ ወ.ዘ.ተ. ሁሉ ይቀርባሉ ።

ወያኔ ህወሓት በለስ ቀንቶት ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ሲቆጣጠር ኢትዮጵያን ከመፈራረስ አደጋ አዳንኩ የሚለው የማጭበርበሪያ ውሸት ፤ ኢትዮጵያ በደርግ ጊዜ ሉአላዊነቷን እና አንድነቷን ጠብቃ ነው የቆየችው። ኢትዮጵያን ያፈረሰና ያጠፋው ህወሓት ወያኔ ስልጣኑ ከጨበጠ ነው። ለዚህም ያበቁት የውጭ ሃገር ባእዳን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶቿ ናቸው። በሱዳን፣ በግብጽ፣ በሊቢያ፣ በኢራቅ፣ በሶሪያ፣ በፍልስጤ፤ ኢራን፤ ወዘተ ተፈጥሮና ተደራጅቶ የመጣ ድርጅት ነው። ሀወሓት ገና ወደ ትገል በረሃ ሳይወጣ በሱዳን፣ በሊቢያና በግብጽ መንግሥታት ምስጢራዊ እርዳታ ይደረግለት ነበር። የድርጅቱ መስራችና መሪ አረጋዊ በርሄ በእነዚህ በተጠቀሱት መንግሥታት አዲስ አበባ የሚገኙ ኤምባሲዎቻቸው፤ ቆንስላዎች ፤ እየሄደ ገንዘብ ሲቀበል መኖሩን                                                                                                                   አነስተኛ እርዳታ ሲያደርጉለት፤ በወቅቱ የታየ፤ የሚታወቅ ሃቅ ነው ፤ይህ ፀረ-ኢትዮጵያ ድርጊታቸውን በርካታ ሰዎች ያውቁታል፡ የወያኔ መሪዎች ይህን ዛሬ ቢክዱ ፤ሃቁም ነገ ይወጣል ፤ ይህ ሁሉ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ለማፍረስ ሲሆን፣ በተለይ ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤት እንደመሆኗ ከዚህ ተወግዳ ካለባህር በር እንድትቀርና እንድትዳከም ለማድረግ ነው፤ከዚህም ዋና ምክንያት ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝ ባለቤት ከመሆንዋ የተነሳ ግብፅና ሱዳን አባይን በበላይነት ለመያዝ ኢትዮጵያን ካዳከምናት ከወደቀች የሚያግደን የሚቆጣጠረን የለም ፤ ኢትዮጵያ ከአባይ ባለቤትነት ማስወጣትም ህ.ወ.ሓ.ት. ትልቅ ሚና አለው ቀዳሚ ሥራው ይህ እንዲሆን ማድረግ እንችላለን ብለው የተነሱ ግብፅንና ሱዳን ዛሬ በግልፅ የምናየው ሃቅ ሆኖዋል። እቅድ አፈጻጸም ለህወሓት አመራር የተሰጠ ነው ። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥም እንደ ህወሓት ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ያጠቃ  የካደ ድርጅት የለም ፤  ለክፉ ጥቃት ዳረጋት ። የህወሓት አመራር ገና ከ1967 ጀምሮ እሰክ አሁን ያሉት አመራሮች ኢትዮጵያን አፍርሰዋል፣ ለም ታሪካዊ መሬትዋ ወንዝዋ የቀይ ባህር ባለቤትነትዋ አሳጥተዋታል ለግልፅ ለሱዳን መንግሥት ሽጠዋል ፤ በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ ከባድ ግፍና መከራ ፈጽመዋል። የኢትዮጵያ አንድነትና ሏላዊነትዋ በመፃረር ሃገር ፈርሳለች ።ተጠያቂ ወያኔ ህ.ወሓ.ት ነው።

 

ከላይ በስም የተጠቀሱትና በሥልጣን ሽኩቻ የተባረሩትም ሆነ አሁን በስልጣን ያሉት ወያኔዎች በኢትዮጵያ ላይ ያለቸው ጥላቻ ሕዝቧን የመበታተን ኢትዮጵያን ተዳክማ ወድቃ ለማየት የሚጓጉ በአንጻሩ ደግም ታላቅዋን ትግራይ፤ ሰፍታ ፤እደጊ ተመንደጊ የቅዠት ህልማቸውና ፍላጎታቸው በምኞት የተንጠለጠለ ዥዋዥዌ ቁጢጥ በለው ልሃጫቸው ሲንጠባጠብ ይታያሉ ፤የጊዜው ባለስልጣናት ፤ ኢትዮጵያ ሃብታም ለም ሃገር ናት ገና እንቦሮብራት አለን ብለው በሚከተሉት ፖሊሲያቸው የሃገር እና የህዝብ         ሃብት በማጋዝ ተሰማርተዋል ። ህ.ወ.ሓ.ት. ኢትዮጵያን ባለው ሁሉ አቅሙ እያዳከማት እያጠቃትም ነው፤ ህዝብዋ ተጎሳቋለ ፤በግድያ፤መኖሪያ ቤቱ እየተቀማ በራንዳ አዳሪ ሆነ ፤ለለማኝነት ተዳረገ ፤ በእስር፤በርሃብ፤በበሽታ፤ በስደት፤ ኢትዮጵያዊ ለህ.ወ.ሓ.ት. ሲኦል ተዳረገ ። ዛሬ ኢትዮጵያና ህዝብዋ በህ.ወ.ሓ.ት. እጅ ቢወድቁም ፤ነገ እንደዚሁ አይቀጥልም ከወደቀችበት ትንሳለች ታሪክዋም በልጆችዋ መስዋእትነት ይመለሳል ። ወያኔን እዚህ ያደረሱት ባለሥልጣናት ነበር አሁን ያሉትም የወያኔ ባለሥልጣናት መሪዎች አቋማቸው አሁንም ኢትዮጵያ ገና አልፈረሰችም፣ ሕዝቧም አልተበታተነም፣ ብዙ ውስጣዊ ስራ ቀርቶናል ብለው የሚያምኑ ናቸው። ሕዝብን ለማጭበርበርና በግንባር ቀደምትነት የሚያነሱት ግን ኢትዮጵያ የባህር በሯን አጣች እያሉ የተቆጩ

 

በማስመያወራሉ። ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል አይደለችም ፤ ኤርትራና ኢትዮጵያ የተለያዩ ሃገራት ናቸው ቀይ ባህርም ሆነ አሰብ ወደብ ኢትዮጵያን አይደለም ፤ ፤አሰብ የኤርትራ ነው ፤ ብሎ በየውጭ ሃገራት ባለሥልጣናት በር ላይ በመቆም ሲማጎትና አቤት ሲሉ የነበሩት የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች አልነበሩም ? አሁን ወይኔና የሻዕብያ መንግሥት ስለተጣሉ፤የለመዱት ጉርሻ ስላጡ አፍቃሬ ኢትዮጵያ መስለው አሰብ የኢትዮጵያ ነው ቀይ ባህርም የኢትዮጵያ ነው የሚሉት የሚዘላብዱት ወያኔዎች እድሜያቸው ለማራዘም አሁን የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ፀረ ወያኔ ሆኖ በመነሳቱ በዚህ አጭበርባሪ ባህሪያቸው ህዝftን ሃሳftን ለማስቀየር ለማለዘብ በነሱ የተነሳው ተቃውሞ ለማብረድ ያለመ የማወናበጃ ተግባራቸው ነው ። በ1983 ዓ.ም በለንደኑ ስብሰባ ሄርማን ኮሆን ሌሎቹም አደራዳሪዎች አሰብ የኢትዮጵያ ነው፤ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ሆኖ የመጣ በዙ ዘመናት ያስቆጠረ ነው ስለሆነም የኢትዮጵያ ግዛት ፤በዚሁ ይካለላል ፤ ትልቅ ሃገር ብዙ ሚልዮን ህዝብ የሚገኝባት ዝግ ሃገር መሆን የለባትም ብለው ሲወስኑ፤ የወያኔው መሪ መለስ ዜናዊ ይህን በመቃወም ፤አሰብ የኢትዮጵያ አይደለም አሰብ የኤርትራ ነው ፤ በምሬት የተቃወመ የእናንተውው መሪ መለስ ዜናዊ አይደለም ? ባነሳችሁት ተቃውሞም ኢትዮጵያ ከግዛትዋ ከባህር በርዋ እንድትባረር አደረጋቹህዋት ሃገርና ህዝብም ለመጥፎ ችግር ጣላችሁት ፤ ይህ በቻ አይደለም ገና ህ.ወ.ሓ.ት ወደ ደደቢት በረሃ ከመውረዱ በፊት በኋላም ደደቢት በረሃ እንደወረደ በፕሮግራሙ ውስጥ ያሰፈረው ኢርትራ ነፃ ሃገር እንደሆነች በአማራው መንግሥት ተወራ በአማራው ቅኝ አገዛዝ ስርአት የወደቀች ሃገር ናት በትግላችን ነፃነትዋ ትቀዳጃለች አያላችሁ የየቀኑ መፈክራችሁ ይህ አልነበረም ወይ ? ለምን በትግል በነበራችሁበት በአመራርም ወንበር ቁጭ ባላቹህ በነበረው ወቅት አሰብ የኢትዮጵያ መሆኑን ኢትዮጵያም የቀይ ባህር እመቤት መሆንዋን አንስታችሁ ስትከራከሩ ተሰምቶም ታልሞሞ በፍፁም አይታወቅም በጠላትነት ከመፈርጅ በስተቀር በጠላትነት መፈረጅ ብቻ አይደለም የኢትዮጵያ ሏላዊነት በመፃረር ግዛትዋ ለባእዳን በመሸጥ ሱዳን በህ.ወ.ሓ.ት. ድጋፍና ትብብር የኢትዮጵያ መሬት ወረዋል ፤ ተጠያቂም ናቹህ ዛሬ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ የሆናችሁት ? ከኢትዮጵያ ህዝብ በጠራራ ጸሃይ የዘረፋችሁት ሃብት ንብረት ባንኮች የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከህዝባዊ ተቋማት የዘረፋችሁት ወርቅ ገንዘብ ኢ.ፈ.ር.ት. (ትካል እግሪ ምትካል ትግራይ ) የኢትዮጵያ ህዝብና የሃገር ሃብት ሙልጭ አርጋችሁ ዘርፋችሁ ያቋቋማችሁት ት.እ.ም.ት. ወይም እ.ፈ.ር.ት የሃገርና የህዝብ ሃብት ንብረት ነው ። በዓለም ውስጥ እንደ ህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ወንጀለኛ ዘራፊም የለም ፤ማንነታችሁም በተግባራችህ አስመስክራችኋል ።. የኢትዮጵያ ህዝብ በፀረ ወያኔ ተነስቶ ህዝባዊ ማእበሉ አቀጣጥሎታል                                       እኛም ሃብታችን እ.ፍ.ር.ትም. ለከፉ አደጋ ወድቀናል ፤ ከእንግዲህ ህዝft አይመለስም በስጋትና ድንጋጤ ወደቃቹህ      ፤ ለማጭበርበርና የህዝftን ስሜት ማስቀየሻ ብላቹህ ኢትዮጵያ

 

የባር በርዋ እናስመልሳለን ካልን የህዝft ድጋፍ እናገኛለን ብላችሁ ማሰባችሁም ምን አይነት ደረቅ ዓይን አውጣ አጭበርባሪ መሆናቹህ ራሳቹህ ተመልሳቹህ አረጋገጣችሁት ፤ ይህ ሁሉ የምትቀባዥሩት የዘረፋችሁት ሃብት እስክ ታሸሹ ፤ዓላማው ይህ ነው ።የኢትዮጵያ ህዝብ አያደርገውም እናንተ ወያኔ በኢትዮጳያ ህዝብ ሙሉ በሙሉ ስለ ተተፋቹህ ጦርነት ከሻዕብያ ብታነሱም የኢትዮጵያ ህዝብም እንኳንስ ደጋፍ ሊሰጠው ቀርቶ ዘወር ብሎ የሚያያቹም አንድም ኢትዮጵያዊ ዜጋ አታገኙም ።ከፉ ጠላት ለኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ነው ፤ ከሃዲ ባንዳ ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ህዝብ ወያኔ ሃገር የሸጠ ከሃዲ ወንጀለኛ ባንዳ የስንት ሚልዮን ህዝብ ሂወት ያጠፋ ጠባብ ዘረኛ ሽብርተኛ የኢትዮጵያ ህልዉና ያጨለመ እንደ ወያኔ ማን አለ ። ፤የሃገር ታሪካዊ እና ለም መሬት ለሱዳን የሸጠ ማነው? ከጎንደርና ከወሎ መሬት ወደ ትግራይ በጉልበት ነጥቆ ያካለለው ማን ነው? የአማርውን ዘር ያጠፋ በተልያዩ ዘዴዎች እየገደለ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመና እያስፈጸመ ያለው ማነው? የሕዝብ ንብረት ያወደመና የዘረፈ ማን ነው? የህወሓት መሪዎችና አጋሮቹ አይደሉምንመውረርና መስፋፋት፡ የአንድ የፋሽስት ስርአት ቀዳሚ ተግባሩ ነው ። የሚከተለውን ካርታ እንመልከት ፤ትግራይ ብትግራይነትዋ የምትታወቀው ሁሉ ኢትዮጵያዊ አስተካክሎ ያውቀዋል ፤ዛሬ በወያኔ ስርአት ደግሞ በጣም ሰፊ ለም መሬትና ጫካዎች ወንዞች ተራሮች ያቀፈች ከሰሜን አስከ ደftብ በሱዳን የተካለለች ትግራይ ሆና ትገኛለች ፤ ይህን ሁሉ ግዙፍ የቆዳ ስፋት ከየት መጣ ? በሌላም በኩል ከአፋር ተነጥቆ ወደ ትግራይ የትግራይ ግዛት ነው ተብሎ የገባ ሰፊ መሬት አለ ፤ ያ ሰፊ ለም መሬት ጫካው ተራራው ወንዞቹ ከአማራው ህዝብ የተነጠቀ ነው ።በጉልበትህ ተማምነህ የአማራው ህዝብ ተወልዶ ያደገበት ስንት ዘመናት በነዋሪነቱ ያስቆጠረው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ተባሮ ለስደትና መከራ ተዳርጎ ፤ማንነቱ ተነጥቆ በስቃይና በእንግልት ውስጥ ይገኛል ፤ በደftብ ወሎም ይህ ነው የደረሰው ፤የወሎ ህዝብም በስቃይና ችግር ይገኛል፤ጎጃምም በጣም ሰፊ መሬትዋ ተነጥቃ የትግራይ ግዛት ቤንሻንጉል ጉመዝ ደርሰዋል ፤ ታላቅዋ ትግራይ ከታች ያለውን ካርታዋን ተመልክተን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ውሳኔው ያሳርፍበት። ወያኔ የሕዝብ አንድነትን እየበተነ ሃገርን በማፍርረስ የራሱ የትግራይ ግዛት ለማጠናከር ብሎም የሃገርን አንድነት በማፍረስ ሕዝብን እርስ በርሱ እልቂት እንዲፈጥር ማድረግ ዋናው ስትራቴጂውና እቅዱ ነው። ቅኝ                                                                                                                      ገዢው

ተጨማሪ ያንብቡ:  ትዝብት ቁ.23- ልማት ሲሉ፣ ልማት ስንል (አገሬ አዲስ)

ህወሓት

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

አጋጣሚውን በመ ጠቀም የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በቋንቋ ወዘተ እየከፋፈለ እቅዱን በተግባር ላይ እፈፅመዋለሁ ጉልበት አለኝ ለሚለው ስንኩል አስተሳሰft፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ብርታትና ጥንካሬም ዛሬ እያየው ነው  ። ህወሓት መውረርና መስፋፋት የጀመረው ከ1967 ጀምሮ ነው። በ1968 የበተኑት ፕሮግራማቸው የትግራይ መንግስት የማቋቋም ፍላጎታቸው የሚያረጋግጥ ነው።ጊዜው እየጠበቁ ናቸው ።

 

ወያኔዎች ሳይቀድሙን እንቅደማቸው የማስፋፋቱን ሂደትም በፍጥነት ማካሄድ አለብን ፤የሚል ፍልስፍናቸው ከትግሉ ጊዜ ይዘዉት የመጡ ነው ፤ ። ለዚህ ዓላም እውን መሆን ሕዝftን የመበታተን እቅድ በግልጽ ያረጋገጠ ሰነድ ነው።ወረራ ሲፈፅሙም ኗሪውን ሕዝብ ማጥፋት አለብህ። ለመስፋፋቱ አመቺ ሁኔታ ለመፍጠር ኗሪውን ማፈናቀል፣ መግደልና ማጥፋት ትፈጽማለህ። በሰሜን ጎንደር የሆነውም ይኸው ነበር። ገና ከ1969 ጀምሮ፤ ጠንከር ባለ መልኩ ደግሞ ከታህሳሥ 1972 ጀምሮ የህወሓት መሪዎች ወልቃይትን በሙሉ በአረጋዊ በርሄና ስብሃት ነጋ የሚመራ፣ ጠገዴን በሙሉ ደግሞ በግደይ ዘርአጽዮን እና አባይ ፀሃዬ የሚመራ፣ ጠለምትን በሙሉ ተባባሪነት ሰራዊታቸውን አስከትለውና በስየ አብርሃ፣ ሀየሎም አርአያ፣ ታደሰ ወረደ ወዘተ ተጠናክረው የሰሜን ጎንደርን ሕዝብ ፈጁት። የዚህ ወረራ አላማ መስፋፋትና የአማራውን ሕዝብ ዘር ማጥፋት ነበር። የሰሜኑን ወረራ ተከትሎ ትግራይ ተስፋለች። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ቃፍታና የሁመራ ባለቤት ሆነች። የህወሓት መሪዎች በሕዝft ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ የሰሜን ጎንደር ህዝብ ሃይሉን በማስተባበር እስከመጨረሻው ድረስ ወያኔን በመዋጋት ጀግንነቱን በሚያኮራ ሁኔታ በማሳየት ወያኔ ላይ ትልቅ ኪሳራ አድርሶበታል። ለጊዜው የመስፋፋት እቅዳቸው እንዳሰftት ሙሉ በሙሉ ሳይሳካ ቢቀረም፣ ወያኔ በለስ ቀንቶት  በግንቦት ወር 1983 ካለምንም ችግር ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛቱ ስር አደረገ። በትረ ስልጣኑን እንደያዙም አላማችወን ከግብ ለማድረስ በመላው ኢትዮጵያ የጥፋት ዘመቻቸውን አጧጧፉት። አማራውን ከየሚገኝበት ክፍለ ሃገር ማሳደድ፣ መግደልና ማፈናቀል ቀጠሉ።ህወሓትም መስፋፋቱን ለመቀጠል፣ የአማራ ህዝብ አዳከሙት ፤ወያኔ ስልጣኑ በማደላደል ቀደም ሲል ሰሜን ጎንደር በመቀጠልም ፣ ላይ አርማጮሆ፣ ታች አርማጮሆ፣ ቤኒሻንጉል ጕሙዝን በሙሉ፣ እስከ አሶሳ ታንጎ መጨረሻ ዳርቻ ምእራብ ወለጋን ጨምሮ አዋሰኑ (ካርታውን ይመልከቱ)። የትግራይ መሬት ነው ብሎ ወደ ትግራይ እያካለው ይገኛል ።ጥንታዊው የቦታዎቹ ስም በመለወጥ የትግርኛ ስምም በመስጠ ት ወረራውና መስፋፋቱ እያፋጠነው ይገኛል ።

ተስፋፊው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ወይም የትግራይ ነጻነት አውጪ ድርጅት የትግራይን መንግስት እመሰርታለሁ ብሎ በወጣበት ጊዜ የሰሜን ጎንደር፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ፣ ከሰሜን ወሎ ደግሞ ራያን ቆቦ፣ ወልዲያ፣ አፍላ ደራ፣ እስከ አለውሃ ምላሽ በፕሮግራሙ አካትቶ በረሃ የወጣው ወያኔ ዛሬ በይበልጥ ተስፋፍቶ ወደታች ወረደውን ወረራ በማስፋት ፤ ባለቤት የሆነው ህዝብን በማፈናቀል በመግደል በማሰር ሰቆቃ ግፍ እየፈጸመ ያለው ህ.ወ.ሓ.ት. ፤ ኢትዮጵያን አዳክሞ ፤የህዝftን አንድነት ኢትዮጵያዊነት ፤የአንድነት ታሪኩን አዳክሞ ፤ለጥንታዊ ባእዳን ጠላቶችዋን፤ የሰጣችሁን አደራ እየፈጸም ነን ደስ ይበላቹህ እያለ ነው ። ሱዳንም የምትመኘው የኢትዮጵያ መሬት በህ.ወ.ሓ.ት. ገጸ በረከትነት አገኘች ፤ይዛለች። ግብፅም የአባይ ወንዝ ባለቤትነቱ ፈላጭ ቆራጭ ለመሆን እየተቃረበኩ ነኝ ትላለች ፤ የኢትዮጵያ መዳረሻ የት ይሆን? የሚታዩ በመሬት ያሉ ግልፅ አሳማኝ ተስፋዎች ግን ይታያሉ ፤ኢትዮጵያ እድሜ ለልጆችዋ አትወድቅም አትበታተንም ፤በልጆችዋ ጥንካሬና መስዋእትነት ትነሳለች ፤ጠላቶችዋን ሁሉም ታንበረክካቸው አለች ፤ በቁጥጥርዋ ሥር ይወድቃሉ ።ኢትዮጵያ ጠንክራ ጎልብታ ከወደቀችበት ትነስታ ፤ልጆችዋም የኢትዮጵያዊነታቸው መንፈስ ይጎናጸፋሉ ፤ይህ ሁሉ የኛም ብርታት ይጠይቃል ።

የካርታው ቅርጽና አቀማመጥ ክftር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ፣ የወያኔ አገዛዝና የኢትዮጵያ ወደፊት እጣ ብለው ከጻፉት ፅሁፍ የተገኘ ነው። እዚህ ጽሁፋቸው ውስጥ ካርታው የትግራይ ግዛት መስፋፋት የሚገልጽ ሆኖ ፣ ከአፋር እና ከኤርትራም አሰብን ያጠቃልላል። ካርታው በህወሓት የተዘጋጀ ነው። ይህን ያዘጋጁት የመስፋፋትና የመሬት ወረራ ተግባራቸውን ከመጀመራቸው በፊት ነው። ሕዝftን በጎሳ ከፋፍሎ እርስ በርሱ ማጋጨትና በመካከላችው ቅራኔ መፍጠር ቀዳሚ አጀንዳቸው ሆኖ ። ለዚህም አላማቸው፣ ቅማንትና አማራን ማጋጨት፣ የቅማንት ህብረተሰብ አማራ አይደለንም ብሎ ከጎንደር ጠቅላይ ግዛት ተገንጥሎ የራሱን ግዛት እንዲያቋቁም የመገፋፋት ተንኮል ላይ ተጠምደዋል። ይህ ህወሓት ምን ያህል ጸረ-ኢትዮጵያ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ህወሃት ይህንን ጸረ-ኢትዮጵያ የሆነ ዘመቻ ቢያራምድም፣ የቅማንት ህብረተሰብ ግን በጎንደሬነቱ የሚተማመን ሕዝብ ነው። ጎንደር የቅማንት ቅማንትም የጎንደር መሆኑን ያምኑበታል። ሕዝft በጋብቻ፣ በመዋለድና አብሮ ለብዙ ሺህ አመታት የኖረ የአማራ ሕዝብ ነው። የህወሓት ሕዝብን ከሕዝብ የመከፋፈሉ ተግባር በቅማንት ሕዝብ ላይ ብቻ የተፈጸመ ድርጊት አይደለም። በአፋር፣ በጋምቤላ ወዘተ ሕዝብ

 

ላይም የተፈጸመና በመፋጸም ላይ ያለ ድርጊት ነው።፤የዚህ ጎጠኛና ፋሽሽት ሽብርተኛ ወያኔ የመሬት መስፋፋት ብቻ ያተኮረ ሳይሆን ወያኔ በሚያዘጋጀው የተንኮል ዘዴ ህዝብን እርስ በራሱ ደም እንዲቃባ በጠላትነት በመጠራጠር እንዲኖር ፤የህንንም በማድረገ የህ.ወ.ሓ.ት. የሥልጣን ማራዘም ዕድሜ ለማግኘት ነው ።በካርታው ውስጥ የተካተቱ ወደ ትግራይ የሚጠቀለሉ ደባርቅ ፤አዲ አርቃይ ፤በየዳ ፤ጃናሞራ ፤ ላይ አርማጮህ ፤ በስተ ምእራftም መተማ ፤ቋራ ፤ታች አርማጮህ ።

በሃገሪቱ ወስጥ ህ.ወ.ሓ.ት. በየቦታው የሚያካሂደው ያለ መስፋፋት ለም መሬቶችን፣ የማእድን ስፍራዎችን፣ የሃገር ኢኮኖሚ ተቆጣጥሮ ወዘተ ወደ ትግራይ ማካለል የሚያካሂደው ያለ ፤ በመጨረሻ ውድቀቱ ሲደርስ ታላቂቷን የትግራይን መንግሥት     ለመመስረት የቅድመ ዝግጅት ሥራው መሆኑ  አመላካች ነው።የወያኔ መሪዎቹ ቢያቅዱም ተግባራዊነቱ ግን ተፈጻሚነት የለዉም ፤ዘራፊ ተስፋፊ መሬት ነጣቂ በሰፊው ህዝብ ክንድ ይደመሰሳል ፤በዚህ ዓለም ከባድ ሃይልና ጉልበት ያለው ህዝብ ብቻ ነው ።ተወልዶ ያደገበት መሬት ተነጥቆ የሚተኛ አማራ ፤አኦሮሞ፤ወላታ ፤አፋር፤ ከምባታ ወ.ዘ.ተ.የለም ። ወያኔ ያቀደው ዕቅድ ይሳካል ብሎ የሚያምን ካለ ስህተት ነው ፤ወያኔ ከማን በልጦ ጎልብቶ ነውና ፤ ፋሽሽቱ ፤ሽብርተኛው ወያኔ በትእቢት የሰከር በያዘው መሳሪ የሚደነፋ አጉል ሽብርተኛ ነው ፤ ከኢትዮጵያ ህዝብ የአፀፋው ምላሽ ያገኛል ።ይህ ደግሞ የሁሉ ኢትዮጵያዊ እምነትና ህዝባዊ የስትራተጂ የሃላፊነት ግዴታ ነው ። አእምሮ ሰንካላው ወያኔ ግን ለጊዜው እንደኔ ማን ቢሊም ይህ የፋሽሽቶች ባህሪን መገለጫ ። አወዳደቁ ግን ተሰባብሮ የማይነሳ በአስቃቂና ክፉ ውድቀት ይወድቃል ።

ህወሓት ገና ኢትዮጵያን ክግንቦት ወር 1983 ዓ.ም ጀምሮ መግዛት ከመጀመሩ በፊት በአሜሪካ መሪነት በለንደን የደርግ መንግሥትን ለማግለል የተደረገው የሰላም ድርድር ህወሓትን ወደ ሥልጣን ለማምጣት የተሠራ ዘዴ ነው። ኤርትራ እንድትገነጠል፣ ተገንጥላም በኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራ መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ደግሞ በመለስ ዜናዊ የሚመራ መንግሥት እንዲመሰረት ፈቅደው ያደረጉት ጉዳይ ነው። አስቀድሞ ግን ኢትዮጵያ ሰፊ አገር ስለሆነች የባሕር በር ያስፈልጋታል፣ ስለዚህ አሰብ ወደ ኢትዮጵያ ተካቷል የሚለ ውሳኔ ተሰጥቶ ነበር። ይህንን ሃሳብ አቶ ኢሳያስ አፈወርቂም የተስማማበት ጉዳይ ነበር። መለስ ዜናዊ ግን ጠንከር አድርጎ በሄርማን ኮኸን የቀረበውን የአሰብ ወደ ኢትዮጵያ መካለል ትክክል አይደለም በማለት አጥብቆ ተቃወመው ። እንዲያውም ስብሰባውን ረግጦ ሲወጣ አብርውት የነበሩት የህወሓት አመራርና አባላት፣ ሥዩም

መስፍን እና ብርሃነ ገብረክርስቶስ፤ አሰፋ ማሞ ሃሳftን በማውገዝ ተከትለውት ወጡ። አሜሪካዊው የስብሰባው መሪም በድርጊቱ ግራ ተጋft። መለስ ዜናዊ እና አባሎቹ ፤ ኢትዮጵያ የባህር በር አያስፈልጋትም ከፈለግን ከሌሎች ሃገራት የባህር ወደብ ተከራይተን ለመጠቀም እንችላለን ሞምባሳም አለን ሲል ፤ አደራዳሪው ከሌሎች አባሎቻቸው ጋር በመነጋገር አሰብን ወደ ኤርትር ውስጥ እንድትካለል አደረጉ። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በዚሁ ተወሰነ ።ኢትዮጵያም የባህር በር የሌላት ሃገር ዝግ ሃገርም ሆነች ፤በህ.ወ.ሓ.ት. ፍርድ ። ፀረ-ኢትዮጵያው መለስ ዜናዊም የተፈጠረውን ሁኔታ ትግራይ ለነበሩት አመራር አባላት አስተላለፈ። በጊዜው ትግራይ የነበሩት የፖሊት ቢሮ አባላት፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስየ አብርሃ፣ ገብሩ አስራት፣ ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ አረጋሽ አዳነ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ተወልደ ወልደማርያምና አርከበ እቁባይ ነበሩ። እንሱም፣ በስብሃት ነጋና በአባይ ፀሃየ እየተመሩ ከፍተኛ ተቃውሟቸውን ለሄርማን ኮኸን በሬዲዮ መገናኛ አሰሙ። ሰብሰባው ቀጥሎ፣ አሰብን በተመለከተ ወደ ኤርትራ ተካቷልና ሀሳባችሁን ንገሩን ሲሉ ሰብሳቢው ጠየቁ። መለስ ዜናዊ ተነስቶ፣ ኢትዮጵያ የምትባል አገር የተፈጠረችው ክ100 ዓመት በፊት በአፄ ምኒሊክ ነው፤ ኤርትራ የተፈጠረችው ግን ከኢትዮጵያ በጣም ቀደም ብሎ ሲሆን ሰፊ ባለታሪክ አገር ነበረች፣ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የምትነጻጸር ሃገር አይደለችም ሲል ምስክርነቱን ሰጠ። በመቀጠለም፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ያልነበራት አገር ነበረች። ስለሆነም የአሰብ ጉዳይ ኢትዮጵያን አይመለከትም፤ አሰብ የኤርትራ ብቻ ነው ብሎ በተደጋጋሚ በመናገር ውሳኔው እንዲጸና አደረገ ።

ህወሓት ወያኔዎች ሲናገሩ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር አያስፈልጋትም። ካስፈለገነም የጅftቲን፣ የኬኒያን እና የሶማሌን ወደቦች እንጠቀማለን ሲሉ የነበሩ፣ ዛሬ ደግሞ ኤርትራን ወረው አሰብን ለማስመለስና በካርታቸው ላይ

 

ከትግራይ ጋር አካለውታል። ኤርትራ ነፃ ሀገር ሁና የተባበሩ መንግሥታት ፤የአፍሪከ አንድነት ሙሉ አባል ናት በምን ሃይሉ ነፃ ሃገር ሊወር ወሮም አሰብን ወደ ትግራይ ሊያካልል ይችላል መብቱስ ማን ሰጠው ፤አይችሉም ። እንደ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት የመሰለ የኢትዮጵያ ደመኛ ጠላት ፤የትም አይደርስም ብለህ በንቀት ልታልፈው አይገባም ይህ ድርጊታቸው የህወሓት አመራር ኢትዮጵያን በታትነው የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ሪፓብሊክን ለመመስረት የታለመ እቅዳቸው ነው። ይህስ ማድረግ ይቻላል ወይ ? ነው ጥያቄው? መልሱ የሚቻል አይደለም ነው። አሁን ያወጡት ካርታ ከጎንደር እስከ አሶሳ የወረሩት መሬት በተግባር ሊወል አይችልም። ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ ወደቀድሞ ግዛታቸው ወደ ጎንደር ይመለሳሉ። የወሎም እንደዚሁ። በኤርትራ ውስጥ የሚገኘው       አስብን ወደ ትግራይ ለማጠቃለልም ወያኔ ፈጽሞ አይችልም ። ይህ የወደ ፊት ትልቅ ሥራ የኢትዮጵያ ህዝብ ሥራ ስለሆነ ፤ሽብርተኛው ፋሽሽት ወያኔ አይመለከተውም ፤ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታም የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ነበርና አሁንም በስልጣን ያሉ የመናገር መብት የላቸውም ;። ይህ የኢትዮጵያውያን ጉዳይ ብቻ ነው ። ያሉት የሚያሳየውም የወያኔ ህወሓት ውድቀት መቃረftን ብቻ ነው። ።ይህን ሁሉ ችግር የፈጠሩት ራሳቸው የወያኔው መሪዎች እንጂ ሌላ ሰው የፈጠረው አይደልም ፤ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ለማጥቃትና ለመጉዳት ።በተግባርም ስለስሩት ወያኔዎች ኢትዮጵያ ለማጥቃት ደደቢት እንደወረዱ ኢትዮጵያ አዳክመ እንበታትናት ያሉቱም በፕሮግራማቸው ያሰፈሩት ሁሉ ፈፅመዋል ፤እየፈፀሙም ናቸው ፤።ኤርትራ ነፃ ሃገር በአማራው የቅኝ አገዛዝ ቀንበር የወደቀች ሃገር እኛ የተ.ሓ.ህ.ት ህ.ወ.ሓ.ት. ቅድምያ ትኩረት የምንሰጠው ከትግራይ ነፃ ማውጣት እኩል መሆኑን ተገንዝበን ለኤርትራም የምንከፍለው መስዋእትነት ግዳጅ አለን ።ብለው ስላመኑበት ከ1969 ዓ.ም ጀምሮ የትግራይ ወጣት ሴት ወንድ በኤርትራ  ከሻዕብያ ሳሕል በረሃ አሰልፈውታል በዙም የትግራይ ወጣቶች ሞተዋል ፤የ1974ዓ.ም የቀይ ኮከብ ዘመቻ የተለየና ከባድ ዘመቻ ከመሆኑም የተነሳ ከ120000 ( ከአንድ መቶ ሃያ ሺህ ) አስከ 160000 ሺህ ወጣት የትግራይ ገበሬዎች  በዚሁ ጦርነት ተማግደው ያለቁበት ወቅት ነው ፤ይህ ድርጊትም የትግራ ህዝብ በሚገባ የሚያውቀው ሃቅ ነው ፤ በትግራህዝብ ሁሉ ተቃውሞ የተነሳበት ነው ፤ይህን ነገ ወያኔ ከመንበረ ሥልጣኑ ሲወገድ የትግራይ ህዝብ አቤቱታም የሚቀርብበት ነው ። ይህን ሁሉ ሰው ኤርትራ ሂደው ከሻዕብያ ምሽግ ውስጥ ገብተው የሻዕብያ ሓራ ( ነፃ ) እንዲከላከሉና ፤ ደርግን እንዲደመስሡ ግዳጅ ተሰጥዋቸው ፤በየምሽጉ ወድቀው ቀርተዋል ።ከዚሁ ሁሉ አካለ ጎደሎ ሁነው የተመለሱ 1347 ታጋዮች በቻ ነበሩ ።እነዚሁም ሲመለሱ አቀባበል ያደረግንላቸው ሙሉጌታ አልምሰገድና እኔ የዚሁ ፅሁፍ አቅራቢ ገብረመድህን አርአያ ነን ቦታው ተከዜ ወንዝ ዳርቻ ።ጥር ወር 1975 ። የዚሁ ሁሉም ተጠያቂዎችም ግንባር ቀደም አረጋዊ በርሄ ሲሆን ግደይ ዘራፅዮን ስብሃት ነጋ አባይ ጸሃየ ሥዩም መስፍን መለስ ዜናዊ ።እነዚህ አመራሮች በዓመት ውስጥ ከስድስት ጊዜ በላይ ኤርትራ እየሄዱ ደጅ የሚጠኑበት ጊዜ ነው የነበረው ።በተለይ ደግሞ አረጋዊ በርሄ ስብሃት ነጋ ግደይ ዘራጽዮን እነዚህ ተያይዘው ሳሕል በመጓዝ ከአቶ ኢሳያስ አፈወርቅ ደጃፍ የማይለዩ ደጅ ጠኒ የነበሩ ናቸው ።ስለኤርትራ ሲዋጉና ሲጨነቁ የነበሩት እነዚ የወያኔ አመራር ናቸው ፤አሁን ከኢሳያስ አፈወርቅ ስለተጣሉ ፤የለመዱት ጉርሻ ስላጡ ፤አሰብ የኤርትራ እንጂ የኢትዮጵያ አይደለም ኢትዮጵያ የባህር በር የላትም ያሉት እነሱ እንጂ ኢሳያስ አፈወርቅ አይደለም ።ጠበቃ ሁነው የሚከራከሩ የወያኔ መሪዎች ናቸው ፤ ፤ከዚሁም ተነስተው ኢትዮጵያን በሚያሳዝን ደረጃ አጠቁዋት ፤ ተጠቃችም ።የኢትዮጵያ ህዝብም ይፋረዳቸዋል ፤ገና ከኢትዮጵያ ህዝብ የሚወርድባቹ የሲኦል ነበልባል ትቀምሱት አላቹህ ። ለፍርድም ትቀርባላቹህ ። በየአደባባዩ በገመድ ትሰቀላላቹህ ።ባልር ጥቁር ታሪክ ናቹህ ።

እነዚህ እርማቸው የበሉ ከሃዲ አረሜኔ ጠላቶች ወራሪ ፋሽሽቶች ቅኝ ገዢዎች ኢትዮጵያን አፍርሰው የአንዲት ሏላዊት ሃገር ሏላዊነትዋን አሳልፈው የሸጡ ለሱዳን የኢትዮጵያ በታሪካቸው የሚታወቁ ለምና ሰፊ መሬት ለጥቅማቸው የሸጡ ከሃዲ ባንዳ ወራሪዎች አሁን ተመልሰው የሚናገሩት የጤንነት ሳይሆን የእብደት ንግራቸው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር በርዋ ማስመለስ አለባት የኢሳያስ አፈወርቅ መንግሥት መጣል አለበት እያሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ቅስቀሳቸው ጀምረዋል ፤ኤርትራ ከኢትዮጵያ ተገንጥላ ነፃ የሆነችው  ከግንቦት ወር 1983 ዓ.ም . በተባበሩ መንግሥታት እውቅና ያገኘት ሃገር ፤የኢትዮጵያ ህዝብ የናንተ የእብዶች ሃሳብ ሰምቶ ወደ አልሆነ ጦርነት አይገባም ፤ እናንተ ራሳችሁ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላትና ሽብርተኛ ፋሽሽት ቅኝ ገዢዎች ናቹህ ፤ስለ ኢትዮጵያ ልታስftና ልትቆሮቆሩ በህዝብ የተሰጣቹ መብትና ግዴታ የለም ። በህዝብ ያልተመረጠ ቅኝ ገዢ

 

ህ.ወ.ሓ.ት. ይህን ሁሉ አንደ ዕብድ ውሻ የምትፈራጩት የምትቅበዘበዙት ያላችሁ ዕድሜያችሁ እያበቃ መሆኑ ተንሽ የዕድሜ ማራዘሚያ ቀን ለማግኘት ብላቹህ ህዝብን ለማወናበድ ያሰባችሁ የሌባ ማተላይ ነው ፤የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ከህፃን አስከ ሽማግሌ ፀረ ህ.ወ.ሓ.ት. እና አበሮቹ ሁላቹህ ዳግም እንዳትነሱ ግባተ መሬት ሊከታቹ ተነስተዋ ፤የወያኔ ዕድሜ እያበቃለት መሆኑ ወያኔዎች ተገንዘftት ።እናንተ ግባተ መሬት ከገባቹ ፤የኢትዮጵያ ህዝብ ይበጀኛል ይጠቅመኛል ብሎ በሚያቋቁመው መንግሥት ሁሉ የኢትዮጵያ ችግሮች ይፈታሉ ። ቅድሚያ የኢትዮጵያ ህዝብ ሥራና ተግባር ግን የወያኔ(የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ) ሥርአት እና አሰስ ገሰሱ ለማስወገድ ትግሉን እያፋጠነ ነው የሚገኘው።”ዋዋዋ “ እያለ ያንዣብባል ጥቁር አሞራው፤ በራሳቹህ ላይ ፤። በስንት ሚልዮን የሚቆጠር ህዝብ ያፈሰሳችሁት ንጹህ ደም እግዚአቢሄር ፊት ቁሞ አብየት እያለ ነው ።

ህወሓት ገና ሲፈጠርና ወደ ትግሉ በረሃ ሳይወጣ አብሮት የተፈጠረ ባህሪያት አሉት። ትምክህት፣ ዘረኝነት፣ ጠባብነት፣ ውሸት፣ ሌብነት አስመሳይነት አጭበርባሪነት አደናጋሪነት ወዘተ የመሳሰሉ ቫይረስ የተሸከመ ድርጅት ነው። ከነዚህ በሽታዎች የባሰ ደግሞ ፀረ-ኢትዮጵያ፣ ፀረ-ሕዝብ አንድነት፣ ወራሪና ተስፋፊ ሆኖ የተፈጠረ ድርጅት ነው። ኢትዮጵያዊነትን የተላበሰ አንድ የህወሓት አመራር ፈልጎ ማግኘት አይቻልም። ከመጀመሪያ ትግሉን የመሰረቱ እስክ አሁን ያሉ መሪዎች ፀረ ኢትዮጵያ ፀረ ህዝብ ባንዳዎች ናቸው ፤በተደጋጋሚ የተጠቀሱ አመራሮች ብናይ፣ ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይጠላሉ። ሕዝftን እና አንድነቱን አንድላይ ያወግዛሉ። ስለዚህ፣ ህወሓት ማለት ፀረ-አገርና ፀረ-ሕዝብ የሆነ ሽብርተኛና ፋሽሽት ድረጅት ነው።የዚሁ ድርጀት ዋናው መሳሪያው ደግሞ ግድያ ነው ፤ግድያው ማስፈፀሚያ ድግሞ የተለያዩ ዘዴዎች አሉት ።

በዚች ዓለም ውስጥ እንደ ህወሓት አመራር ኢትዮጵያን የሚጠላና ታሪኳን የካደ የለም። ጣልያን እንኳን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜያቶች የኢትዮጵያን አስደናቂ ታሪክና ያለፉትን ገናና መሪዎቿን ጨምሮ አልካደችም። የህወሓት አመራር ግን ገና ትግሉን ሳይጀምሩ ኢትዮጵያ በምኒሊክ ዘመነ መንግሥት የተፈጠረች አገርና ከ100 ዓመት እድሜ ያልበለጠ አገር ናት ይላሉ። የኢትዮጵያ አንድነትና ታሪክ በብዙዎች አጥንትና ደም የተገነባ የብዙ ሺህ ዓመት ባለታሪክ ነው። ወያኔ ሀወሕት ይኽንን ታሪክ መካድና የማጥላላት ሥራውን የጀመረው  ክ1964 ዓ.ም ጀምሮ ነው። ይህንን አስቀያሚ ክህደት የሚያራምዱት ለበርካታ ጊዜ ካላይ የተጠቀሱት የፖሊት ቢሮ አመራሮች ናቸው። በወቅቱ ያዘጋጁእት በራሪ ወረቀት ‘ድምፃ ብሄር ትግርይ’ (ቮይስ ኦፍ ትግራይ ኔሽን) በለው በጠሩት መጽሄታቸው ውስጥ ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ወንጅለዋል። አሁንም በዚሁ እምነታቸው ቀጥለውበታል። የዚሁ ዋና አዘጋጆች የነብሩ አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘራፅዮን ናቸው ; በወቅቱም በህዝft ውግዘት ደርሶባቸዋል ፤እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያን ሲተነትንዋት እንደ ሃገር ሳይሆን እንደውዳቂ ftቱቶ ረጋግጠው ሲያጨማልቅዋት ሲታዩ በህዝብ ተረግመዋል ። ዛሬ ደግሞ ስው ማሳይ በሸንጎ ሆነው ስለኢትዮጵጵያ ተቆርቋሪ መስለው ፊታቸው ሸፍነው ከኢትዮጵያውያን ጎን ተቀምጠው ስለ ሃገር ይናገራሉ ፤በደም የሚጠየቁ ።ሃገር ያፈረሱ ፤ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸሙ ፤ሃገር የሸጡ ፤ኢትዮጵያን በዘር ብቋንቋ ከፋፍለው አሁን የደረሰችበት አስከፊ ደረጃ ያደረስዋት ናቸው ።

የህወሓት መሰረታዊ አቋሙ ኢትዮጵያን ለመበታተን ነው።ህዝብን ከፋፍለው ማቆምያ በሌለው የእርስ በርስ ግጭት ፈጥረው ራስ በራሱ እንዲተላለቅና ህዝብ እንዲጠፋ ይህ ከሆነ ፤ ኢትዮጵያ ተዳክማ እንድትበታተን ነው ። ህ.ወ.ሓ.ት. ሲፈጠር ጀምሮ በተለያዩ ዘዴዎች ይህን እያራምዱ የመጣ የመስፋፋት ዓላማው አሁንም በስፋት መስፋፋቱን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን፣ በወያኔ ህወሓት ሴራ ሳይፈታ፣ አንድነቱን፣ ፍቅሩን እና ኢትዮጵያዊነቱን እያጠናከረና እያዳበረ ይገኛል።

አርእስትዋን ለማጠቃለል ፤ ይህን ያህል የህ.ወ.ሓ.ት. የመስፋፋት ዓላማ ፤ሕገ ወጥ ወረራ ነው ፤ የወያኔ የመስፋፋት ዘመቻ ፤በስፋት የሚያካሂደው ያለ በአማራው መሬትና በአማራው ህዝብ ላይ ዘሩን እያጠፋ የሚደረግ ሲሆን የሚወረረው አማራ ብቻ ሳይሆን ተወራሪው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው ።ግዛቱ የኢትዮጵያ በመሆኑ ።ስለዚህ በሙሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ተባብሮ በወራሪው ህ.ወ.ሓ.ት ሰፊ ሃገራዊ ጥቃት ከፍቶ ወያኔን ላንዴና ለመጨረሻ ግብአተ መቃብሩ መክተት ግዴታው ነው ። ይህ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ፤መስፋፋትም ዓላማ ያለው ነው መደመር መቀስ አያስፈልገውም ፤ይህም ትግራይን ገንጥሎ ሰፊ

 

የትግራይ መንግሥት ለማቋቋም የመጨረሻው  ግft ይህ ነው ። መለስ ዜናዊ በ1984ዓ . ም. በየካቲት ወር ድርጅቱ የተመሰረተበት በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ወደ ትግራይ ሂዶ በበዓሉ የተናገረው ፤እኛ የህ.ወ.ሓ.ት. ታጋዮች የሞትንለት ዓላማ ደማችን ፈሶ አጥንታችን የከሰከስነው ትግራይን ለማልማትና ለማሳደግ ዘመናዊት ትግራይ ለመፍጠር እንጂ ለማንም ብለን አይደለም ብሎ እቅጩን የተናገረበት ጊዜ ነው ።ይህ የመለስ ዜናዊ አነጋገር ቀስቱን ያነጣጠረው ፤አንድ ቀን ትግራይ ከኢትዮጵያ ተገንጥላ የራስዋ መንግሥት ትመሰርታለች ነው ። ይህ የትግራይ መገንጠል በፕሮግራማቸው አስቀምጠው ትግሉን እየመሩ የመጡት እነ አረጋዊ በርሄ፤ ግደይ ዘራጽዮን ፤ ስብሃት ነጋ፤ ፤ አባይ ጸሃየ፤ ሥዩም መስፍን፤ መለስ ዜናዊ፤ ቀጥሎም ገብሩ አስራት፤ ስየ አብርሃ፤ አውአሎም ወልዱ፤ አረጋሽ አዳነ ፤ አርከበ ዕቁባይ፤ቀጥሎም ሃለቃ ፀጋይ በርሄ፤ አባዲ ዘሞ ፤ቴድሮስ ሓጎስ ፤ አሁንም የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች 1 አባይ ወልዱ 2 ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል 3 አዲስ ዓለም ባሌማ 4 ጌታቸው አሰፋ 5 ቴድሮስ አድሃኖም 6 አዜብ መስፍን 7 በየነ ምክሩ 8 ፈትለወርቅ ገ/እግዚሄር 9 ዓለም ገ/ዋህድ ሌሎቹም ከአንድ መሪ ወደ ተከታዩ መሪ እየተላለፈ የመጣ የዓላማቸው መርሃ ግብር ነው ።ስለዚህ ከዚሁ የአቋም ፖሊሲ ተነስተው ኢትዮጵያን በታትነው ፤በተስፋፊነት በወረራ የያዙት ሰፊና ለም መሬት ይዘው ትግራይ ገንጥለው ፤ <« የትግራይ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ መንግሥት >›ለማቋቋም በጥድፍያና በመረባረብ የሚገኙት ።ይህ ነው የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች የፖሊሲ እና የአቋም የመጨረሻ ግባቸው ።

  የህወሓት አመራር በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የፈጸመው ወንጀል    

በመጀሪያው ገጽ እንዳስቀመጥኩት፣ ‘በዝሆን ላይ የሚጮህ እብድ ውሻ ነው’ ያልኩት ያለምክንያት አይደለም”። ዛሬ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ህወሓት ማን እንደሆነ፣ የተፈጠረበትን ምክንያት፣ የወደፊት እቅዱን፣ የፈጸማቸውን አስከፊ የወንጀል ድርጊቶች፣ ኢትዮጵያን የማዳከም ጥረት፣ ሃገር ለመበተን ያልውን እቅድ ወዘተ በዝርዝር የሚያውቀውና የሚተነትን ኢትዮጵያዊ ህዝብ ነው። የወያኔ አመራር ዘረኛ ስርዓቱን በፍለገው መንገድ ሊያስኬደው አይችልም ሕዝብንም ከእንግዲህ ልያታልል አይችለም የሆነ ይሁን የህ.ወ.ሓ.ት ገዢ አፓርታይድ ስርአት የሚናገረው የሚሰራው በኢትዮጵያ ህዝብ ተቀባይነት የለውም .። እየዋሸን የስልጣን እድሜአችንን እናራዝማለን ማለቱ ከቀቢጸ ተስፋ የመነጨ ነው። እምቢ ለወያኔ ህወሓት ብሎ ያመጸው ሕዝብና የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ትግል ሊያቆመው ፈፅሞ አይችልም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ሁለገብ ትግል ነው። በኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ፤የነፃነት ትግል ነው። በትጥቅ ትግሉ ላይ የተሰማሩ የነፃነት አርበኞችም የህዝft አካል ናቸው ሃይልና ብርታቱም የነሱ ነው ፤በመሆኑም ወያኔ ህወሓትን ተሸንፎ መቃብሩ ውስጥ መግባቱ የማይቀርለት ነው ። ገበሬውና ይከተማው ሕዝብም እምቢ ለወያኔ ዘረኛና ከፋፋይ ፋሽስት አንገዛም በማለት ውጤታማ ሰላማዊ ትግል ተሰማርቶ የወያኔን ኢኮኖሚ እያሽመደመደው ይገኛል። እነዚህ ጣምራ ትግሎች ወያኔን አዳክመውታል፣ ግብአተ መሬቱን አቃርበውታል።

የህወሓት ባህሪያት ቀደም ብለው ተጠቅሰዋል። የህወሓት ፀረ-ዲሞክራሲ ባህሪው ወደ እብድ ውሻነት ለውጦታል። ከዚህ እብድ ውሻ ጋር በውይይት መድረክ ተቀምጦ በመወያያት ማንነቱን ማስለወጥና ሥልጣኑን ለሕዝብ ያስረክባል የሚሉ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች ካሉ እጅጉን ተሳስተዋል። ወያኔ የማይለወጥና የማይሻሻል አእምሮ ስንኩል ነው። ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ለማዳን የተጀመረውን ትግል አጠናክሮ በአንድነት ህዋሓትን ወደማይቀረው ግብአት መሬቱ ማስገባቱ አማራጭ የሌለው ግዴታ መሆን አለበት። የህ.ወ.ሓ.ት. የቀድሞዎቹና የዛሬው ያሉትን አመራሮች ባላቸው የታጠቁት መሳሪያ የሚተማመኑ ፤ሌላ መተማመኛ ካርዳቸው እንግሊዝና አሜሪካ ናቸው ፤ይህን ሁሉ ዋጋ የለውም ፤የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ደግሞ ፤ህዝባዊ ትግል ነው ፤የመሳሪያ ብዛት የመሳሪያ ጋጋታ ፤ለህዝብ ሃይል ሊገድበው አይችልም ። የጠላት ሃገራት ከወያኔው ጎን መቆም ፤ትግሉ መራራና መስዋእትነትን የሚጠይቅ ያደርገዋል እንጂ ፤ተሸናፊው ተማራኪው ወዳቂው ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት ነው ። የኢትዮጵያ ህዝብ የጀመረው ህዝባዊ ትግል ሊሰብረው ሊያሸንፈው ፍጹም አይችልም ፤አሸናፊው ፤ድሉን የሚቀዳጀው የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ብቻ ነው ።

   የህ...መስራቶች ዋናዎች ከየት መጡ ፤እንዴትስ ተሰባሰft፤

 

የህ.ወ.ሓ.ት. አመጣጥ ቀደም በማለት ሰባቱ መስራቶቹ ከላይ የተገለጹ ናቸው ።ከነዚህም ውስጥ አጋአዚ ገሰስ ራሳቸው መሪዎቹ የገደሉት ነው ፤ሌላው ሃይሉ መንደሻ በ1968 ዓ.ም መጨረሻ ከነሱ ከድቶ እጁን ለጀብሃ ( ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ ) በመስጠት ከትግሉ ሜዳ ወጣ ፤ጠፍቶም በሱዳን አድርጎ አሜሪካ ገባ ።አሁን የቀሩት አምስት አመራር ሲሆኑ ፤ እነሱም 1 አረጋዊ በርሄ 2 ስብሃት ነጋ 3 አባይ ጸሃየ  4 ግደይ ዘራፅዮን 5 ሥዩም መስፍን ናቸው ። ድርጅቱም በዋናነት የሚመራው        በአረጋዊ በርሄ ነው። መለስ ዜናዊ እና ስብሃት ነጋን አረጋዊ በርሄ የነብስ አባታቸው ነው ። በወቅቱ የነበረው ታጋይ መለስና ስብሃይን አያምናቸውም ይጠላቸዋል ፤እነሱም ከባድ ስጋት ያሳደሩበት ወቅት ነው ።ለማኝናውም ማንነታቸውን ባጭሩ ላቅርበው ።

 መለስ ዜናዊ ማን ነው ፤   

 

ህ.ወ.ሓ.ት.በግንቦት 20/1983 ዓ.ም ኢትዮጵያን ወሮ በቅኝ ግዛት መዳፍ እጁን ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በየ ቦታው በሄድክበት ስለ መለስ ጀግንነት የጦርነት አመራር ችሎታው የጦርነት እስትራቴጂ ሊቅ፤ በታንክ እየተዋጋ በአንድ እጁ ሲዋጋ በአንድ እጁ መፃህፍት እያገላበጠ ጦርነቱን ለድል የሚያበቃ ፤በዚች ዓለም ያልተፈጠረ ያልታየ ጀግና ከትግራይ ተፈጠረ እየተባለ ከንቱ ውዳሴ ሲወደስለት ከበሮ ሲደለቅለት አይተናል ። የሚያሳዝኑ ይህን በባዶ ሃዋሁው የሚለፍፉ ሰዎች ፤እነዚህ አድማቂዎች የራሳቸው ጤንነትም አጠያያቂ ነው ፤ ምክንያቱም መለስ ዜናዊ ማን ነው? የሚለውን ጥያቄ ሊመልሱም አይችሉም።

መለስ ዜናዊ የመናገር ችሎታ አለው ፤ወላጅ አባቱ ዜናዊ አስረስም ሙልጭ ያለ ተናጋሪ ወስላት ነው ፤ያላየው ያልሰማው ፤እንዳየ እንደሰማ አስመስሎ የሚናገር ውሸታም መሆኑ ህዝብ የመሰከረለት አስመሳይ ውሸታም የሚወዳደረው የለም ።

መለስ ዜናዊም የወላጅ አባቱ ባህሪያት የወረሰ የዜናዊ አስረስ ልጅ በው ።ከመለስ ዜናዊ አብረን ለብዙ ዓመታት በረሃ ገብተን ታግለናል መጻህፍትም ያገላብጣል ነገር ግን ለእለቱ የሚጠቅሙት ካልሆነ በስተቀር ርቆ አይሄድም ፤ይጽፋልም አሁኑም ለጊዜ የሚጠቅሙት ብቻ ይመርጣል ፤የሚመርጣቸውም ለማደናገር በቂ ናቸው ብሎ ካመነባቸው ይጠቀምባቸዋል ለሁሉም ይደርሳል ።

መለስ ዜናዊ በሚያደርጋቸው ንግግሮች ሁሉ አስቀድሞ ውሸትና ማስመሰል በማርና ቅቤ ተለውሰው ለሰሚውም እውነት ወደ ተግባር የሚለወጡ በማስመሰል ፤ውስጡ ግን ባዶ ጠብ የምትል እውነታ የሌለበት የውሸት ዲስኩሩ በሚድያም ሆነ በፅሁፍ ያሰረጫል ግን ሃቅነት የሌለው የውሸት ተስፋ ማደናገሪያ ነው ።

መለስ ዜናዊ ትልቁ ችሎታው በውሸት እና በማስመሰል የፈጠራ ችሎታው የሚወዳደረው የለም ይችልበታ ዘዴው ብልሃቱ አቀነባበሩ ያውቅበታል በዚሁ ብቃቱም ሰው አሳምኖ ሙርከኛ ያደርገዋል ።ይህ ለጊዜው ያገኘው ድል ፤ጊዜና ወቅት ቢወስድም የተናገረው የሰጠው ተስፋ ሁሉ በሙሉ ውጤት አልባ ባዶ ናቸው ፤ ምክንያቱም በውሸትና በማስመሰል የምትናገረው የምትንቀሳቀሰው በአሸዋ ላይ የተገነባ በተጨባጭ ፍሬ የሌለው በናኝ የውሸት ነው ።

የመለስ ዜናዊ ትውልድ እና እድገት _፟መለስ ዜናዊ ትውልዱ ኤርትራዊ ነው ፤1/4 አንድ /አራተኛ አድዋ በሴት አያቱ ትውልድ አለው ። ወልጅ አባቱ ዜናዊ አስረስ ይባላል የሹምባሽ አስረስ ተሰማ የጣልያኑ ባንዳ ልጅ ፤ ራሱም ባንዳ የጣልያን አሽከር ።የመለስ ዜናዊ ወላጅ እናት ው/ሮ አለማሽ ወልደሉዑል ይባላሉ እንደባላቸው ሙሉ ቤተ ስቦቻቸው የጣልያን ባንዳዎች ናቸው ። ስለዚህ መለስ ዜናዊ ከዚህ ቤተ ሰብ የተወለድ ተወልዶም የመጣ ነው ።ከዚሁ ዓይነት ቤተሰብ የመጣም ፀረ ኢትዮጵያ መሆን ደሙ ያስገድደዋል ። እኔ የዚሁ ፅሁፍ አቅራቢ ፤ከመለስ ዜናዊ በጣም የምንቀራረብ ፤ጥሩ ጓደኝነት በትግሉ ወቅት ነበረን ፡ከዚሁ በመነሳት የነበረው ተፈጥራዊ ባህሪ ፤በተገቢው አውቀዋለሁ ።

ልጅ የአባቱን ባሪይ ይወርሳል፤ የሚል የአባቶቻችን አነጋገር ትክክል ነው ፤ አንድ ኡነተኛ ታሪክ ላቅርብ ። በ1952ዓ.ም. ዓድዋ አውራጃ ፍ/ቤት ዜናዊ አስረስ ለምስክርነት ተጠርቶ ፤የውሸት ምስክርነት በመመስከሩ

 

ፍ/ቤቱ የ3 (ሶስት )ወር እስራት ፈርዶበት በማንኛው የመንግሥት መ/ቤት ለምስክርነት እድሜ ልኩ እንዳይፈለግ የሰጠው ብይን በዓድዋ አውራጃ ፍ/ቤት [በዓድዋ አውራጃ ፖሊስ ጽ/ቤት የሚገኝ ማስረጃ ነው ።

ወያኔዎች አውጥተው ካላጠፉት ። መለስ ዜናዊም ከወላጅ አባቱ የውረሰው ብዙ ነው ።

የመለስ ዜናዊ ባህሪያት>>ውሸታም ፤ ፈሪ ፤ አስመሳይ ፤ አጭበርባሪ ፤በጣም ተንኮለኛ መሰሪ ፤ቂመኛ ፤ ገዳይ ፤ ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት፤ ፀረ ህዝብ ፤ከፉ ዘረኛ ፤ ሌባ ፤ ሽብርተኛ ፤ ዘራፊ ቀማኛ ፤ እልም ያለ ፀረ አማራ  100%ከዚሁም ይበልጣል፤ ወ.ዘ.ተ.።

የመለስ ዜናዊ እውቀትም ችሎታም በተመለከተ ፤መለስ ዜናዊ ጥልቅ እውቀት ችሎታም የለውም እውቀትና ችሎታ ለማግኘት መማር የግድ ይላል ፤መለስ ዜናዊ በእርግጥ በቀ.ኃ.ሥ.ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዓመት ተምሮ በ1967 ዓ.ም በረሃ ወጣ ፤ይህም የተማረ ነው አትለዉም ፤ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቁ ብቻ ያረጋግጣል ፤ስለሆነም መለስ ዜናዊ ፤የትምህርት ደረጃው አነስተኛ ነው እውቀትም ብቃትም ትምህርትም የለውም ።አዶልፍ ሂትለርም እንድዚሁ ነበር ።

መለስ ዜናዊ ትልቁ ችሎታው ፤« ውሸት+ማስመሰል+ ማጭበርበር » እነዚህን በአንድ ላይ አደባልቆ ደመሮ

+ቤት ካለምሶሶ ያቆማል ፤ምንም ያልተገነባ ቤት በባዶ ሜዳ እልም ያለ ያጌጠ ያሸበረቀ አዳራሽ እንደገነባ አድርጎ ያሳያሃል ፤ይህም ትልቅ የማጭበርበር ስጦታ ነው ፤ብንለውም የኋላ ኋላ ግን የሚያስከትለው ተሰባብሮ ውድቀት ነው ። በውሸት በማጭበርበር በማስመሰል የምትጓዘው የውሸት የአሸዋ አስፋልት ክምር ተንዶ እዛው አንተና ተከታዮችህ ደምሮ ተቀብረህ ትጠፋልህ ። መለስ ዜናዊም በዚሁ የባዶ አሸዋ ክምር ሲዋልል የኖረ ሬሣ ነበረ ።ጣልያኖች ይዋሻሉ ይባላል ፤የመለስ ቤተሰብም ይህን መውረሳቸው እይቀርም በምን ብንልም ዘር መንዘሩ ሁሉ በአባቱ በእናቱ የጣልያን አሽከሮችና ባንዳዎች በመሆናቸው የፋሽሽት ጣልያን ባህሪ ይወርሳሉ ፤መለስ ዚናዊም ይህን ወረሰ ። ውሸታም ፀረ እትዮጵያ መቀኛ ፤ደመኛ ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ሆኖ የመጣው ።

መለስ ዜናዊ ==የህ.ወ.ሓ.ት ነባር ታጋይ ነው። ፤መስራች ግን አልነበረም። ህ.ወ.ሓ.ት የመሰረተው አረጋዊ በርሄ ነው ።መለስም ደደቢት ውስጥ ተቀላቀለ ፤የካቲት ወር 11 ቀን 1967 ዓ.ም ተ.ሓ.ህ.ት. (ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ) ተብሎ ሲመሰረት ግን እዛው ነበረ ፤ጠቅላላ የነበሩም 32 ታጋዮች ተሰባሰበው የነበሩበት ጊዜ ነው ።በወቅቱም ያጊዜ ለመለስ ዜናዊ አልተመቸውም ነበር፤ርሃft ብርዱ የወባ በሽታው ተደራርበው የስነ ኧእምሮ ጭንቀት በስፋት ይታይበት ስለነበር ፤ወደ ቤቱም እንዲመለስ የጠየቀበት ወቅት ነበር የሚሉም አመራር ታጋዮች ነበሩ፤ ይህም እውነት ነው ፤ አረጋዊ በርሄ አግባብቶ ሃሳftን እንዲለውጥ አደረገው ።ይህ ሃቅም ራሱ መለስ ለኔ ነግሮኛል ፤በበለጠም ተክሉ ሃዋዝ የድርጅቱ የደህንነት ሃላፊ ይህን ነገር ስለዊያውቅ አጫውቶኛል ።

መለስ ዜናዊ ጦርነት አይወድም በእጅጉ በጣም ፈሪ ነው ። ለመጀመሪያ ጊዜ በጦርነት የተሳተፈው ዓድዋ ውስጥ የሚገኘው ንግድ ባንክ ለመዝረፍ የብዙ ቀናት ጥናት ተካሂዶበት ፤ጥናቱ እንድተጠናቀቀ በአረጋዊ በርሄ የሚመራ ኦፐረሽን፤ መለስ ዜናዊም እንደ ማእከላይ ኮሚቴ አባልነቱ፤ ባንኩ አጠገብ ሆኖ ታጋዮችን እንዲያስተባብር ተመድቦ ፤ ኦፐረሽኑ ይሳካል በለው ያቀዱት ፤፤የሚጀመረውም ከለሊቱ በ10 ሳአት ንጋቱ አካባቢ ተብሎ ፤ልክ ኦፐረሽኑ ሲጀመር ቶክሱም ሲከፈት መለስ ዜናዊ በተፈጠረበት ፍርሃትና ድንጋጤ የተሰጠው ሃላፊነት ትቶ በመሸሽ  በታጋዩ ላይ ከባድ ኪሳራ ወደቀ ፤ ታጋዮቹ በየቦታው ወደቁ በአብዛኛው ታጋዩ ሙቶ ( ተገድሎ ) ፤ ክፉኛ ቆስሎም በየጥጉ ወደቆ ፤መለስ ዜናዊ ግን ፤ከዓድዋ ከተማ የጀመረው ሽሽቱ በእጁ ይዞት የነበረው ሬድዮ መገናኛ ዎኪ ቶኪ ጥሎ ፤በመሸሽ በእንዳማሪያም ሸዊቶ አድርጎ እገላ ( ገርሁስርናይ )ተገኘ ። በዚሁ አኦፐረሽን የተመድft ሃይሎች አራት ነበሩ ከእነዚህ በሂወት የተመለሱት ጥቂት ናቸው ፤የዓድዋ ነዋሪ ህዝብ በአይኑ ስለተመለከተው በታጋዩ ለደረሰው እልቂት በጣም አሳዝኖት ነበር ፤ ጊዜው ግንቦት መጀመሪያ 1969 ዓ.ም .ነበር ።በዚሁ ወቅት ይህን ሁሉ ታጋይ ሙትና ቁስለኛ ሆኖ ሳይመለስ የቀረው ፤በድርጅቱም የደረሰው ከባድ ኪሣራ በመለስ ዜናዊ ምክንያት እንደሆ የድርጅቱ ታጋይ ሁሉ ከባድ ተቃውሞ ቢያስነሳም ፤እድሜ ለነብስ አባቱ አረጋዊ በርሄ የተጠየቀበት አንዳችም ነገር የለም ። በድርጅቱ ሕግ መሰረት ከጦርነት ፈርቶ የሸሸ ፤ከጦርነት ያፈገፈገ የሚሰጠው ፍርድ ሞት ተብሎ ተደንግጎ ፤በሕግ የሰፈረው በሌሎች ታጋዮች በተግባር እየተፈፀመ ፤በስንት መቶዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች ፤ከጦርነት አፈግፍገሃ ፤ሸሽተሃል ፤

 

ቁጥቋጦ ወይ ድንጋይ ሥር ተደብቀህ ተገኝተሃል እየተባለ በብዛት ሲረሸንበት ( በጥይት ሲገደል ) ወቅት በመለስ ዜናዊ ላይ አልሰራም ።የመለስ ዜናዊ የፍርሃት ሽሽት በዚሁም አላበቃም ፤ ነሓሴ ወር 1970 ዓ.ም. ከዓዲ ዳዕሮ ጦርነት  ፤  ሰኔ  ወር 1970 ዓ.ም ውጊያ ዕዳጋ ረftእ  ፤ ጥቀምት ወር 1971ዓ.ም. ውጊያ ፈረስ ማይ

፤ መስከረም ወር 1971ዓ.ም ጦርነት ማይቅነጣል      ፤በዙም ማንሳት ይቻላል ከእነዚህ የውጊያ ቀጠናዎች ፈርቶ የሸሸ መለስ ዜናዊ እንጂ ሌላ አልነበረም ፤የዚሁ ሰው ዛሬ የጦር መሃንዲስ የደርግ ጦር ያሸነፈ ማርሻል ወ.ዘ.ተ. ሆዳሞችና ለከርሳቸው ያደሩ የወያኔ አሽከሮችን ቅጥሮኞች ጌታቸው መለስ ዜናዊ ስንት ጉድ የተሸከመ ፈሪ ሽንታም መሆኑን የሚያውቁ ያውቃሉ የማያውቁ ደግሞ የመለስ ዜናዊ ማንነት ይወቁት ።ይህ ሁሉ ፍርሃትና ሽሽት በመለስ ሲታይ የወቅቱ ፖሊት ቢሮ ዳግም ወደ ጦርነት እንዳሄድ ወሰነለት ለመለስ ዜናዊም ትልቅ ድል ፈጠረለት ። መለስ ዜናዊ በቅርበት የማውቀው እንዲያውም ካሉ በትግሉ አብረን በነበርንበት የጠበቀ ግኑኝነትና ፍቅር የነበረን ነበርን አሁን ያሉት ምድረ ሆድም ሸቃጭ መለስ ከኔ በላይ አያውቁትም ፤ዛሬ በመለስ የሚያመልኩ ፤መለስ ማለት እኮ ፤የውጊያ አይሮፕላን ሲመጣ መሬት አፍዋን ከፍታ ልትደብቀው የሚመኝ በዓለም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ፈሪ ነው፤እንኳን ከደርግ ጦር ፊት ለፊት ጦርነት ሊገጥም ቀርቶ የወያኔ ሠራዊትም ፊቱ አያውቀውም ፤መለስ የሚያውቁት እነ ሳሞራ ጻድቃን ሰዓረ ታደሰ ወረድ ወ.ዘ.ተ. ናቸው ፤ በተረፈ የህ.ወ.ሓ.ት. ሰራዊት ፊቱም አይቶት አያውቀም መልስን አያውቅም እውነቱ ይህ ነው ።ለአረጋዊ በርሄ ሁሉ ያውቀዋል በየግዳጁ ከስራዊቱ አይለይም ፤በማንኛውም ጊዜ ከሰራዊቱ አብሮ ስለሚንቀሳቀስ ።መለስ ዜናዊ ግን ይህን አድርጎት አያውቅም ፤

መለስ ዜናዊ >አንባቢ ፀሃፊ ተማራማሪ ጠበብት የሚሉ ተስፈኞች አሉ ፤የመለስ ትምህርትና እውቀት ከላይ በመጠኑ እንደተገለፀው ሲሆን መለስ ለመዋሽት ለማጭበርበር ለማስመሰል የሚጠቅሙት ህዝብ የሚያወናብድበት ህዝብ ለህዝብ የሚያጋጭበት ተፈጥራዊ መሰሪነት አለው፤ በዚሁም ነው ህ.ወ.ሓ.ት. በስልጣን ኮረቻ በዥዋዥዌ ተንጠልጥሎ ያለው ፤ ይህ ጭራቅ ስርአት ሌላው ምክንያትም ህ.ወ.ሓ.ት.ሲፈጠር ጀምሮ ህዝባዊነትያልተላበሰ ፤ ያልተፈጠረበት የባዕዳን አሽከር የባዕዳን ዲቃላ ፀረ እትዮጵያና ፀረ ህዝብዋም ሆኖ የመጣው ፤የመለስ ሆነ የሌሎቹ ፖለቲካ በዚሁ የታጠረ ሆኖ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ማውደም ግንባር ቀደም ተግባራቸው ነው ፤።ይህ ደግሞ ግንባር ቀደም መሪው መለስ ዜናዊ ነው ።ፀረ ኢትዮጵያ የውጭ ሃሎችም መለስን ይረዳሉ ።

ሌላው መለስ ዜናዊ በስፋት የሚታወቅበት >›መለስ ተንኮለኛ እና ከፋፋይ ነው ።ይህም ትግሉን ከተቀላቀለ ጀምሮ በተግባር ሲጠቀምበት ተው ያለው የለም ፤አመራር ከአመራር ታጋይ ከታጋይ የመከፋፈል ዘዴው ሲጠቀም ፤በየእለቱ ታጋዮች መለስ የሚሰራው ያለ ታጋዩን እየከፋፈለ እርስ በራሱ እንዲጠራጠር አለመተማን እየፈጠረብ ፤እንዴት አታርሙትም ይህ ሰው በድርጅቱ አደጋ ይፈጥራል ፤ የሚል ተደጋጋሚ ሪፖርት የሚደርሰው አረጋዊ በርሄ ፤ሪፖርቱን በማጥላላት ይህ የራሳችሁ ፈጠራ ውሽት ነው ፤እያለ ታጋዮችን እያሸማቀቀ እስከ መረሸን መግደል የደረሰበት ሁኔታ በሂወት ያለ ነባር ታጋይ የሚያውቀው ሃቅ ነው ። በአመራርም እንደዚሁ ብዙ አመራሮች መለስ የሸረበው ተንኮል ከሃላፊነታቸው ተባረዋል ፤ገሰሰ አየለ ( ስሑል

)የተገደለው ሸሸቢት በርሃ ፤ftምበት በአዋአሎም ወልዱና በአሰፋ ማሞ የተረሸነው መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ በሸረftት ተንኮል ነው ። ። እድሜ ለአረጋዊ በርሄ መለስ ዜናዊ የፈለገው እየሰራ የህ.ወ.ሓ.ት. ኮከብ እየተባለ የመጣው ፤ውስጡ ግን ባዶ ጣሳ ።መለስ ለራሱም ለአረጋዊ ከስንቱ ታጋይ ፤ነው ያጋጨው እንዲጠላ እንዲናቅ ያደረገው ፤መለስ ዜናዊ ነው ፤ ወዳጅ የሚባል አያውቅም መለስ ዜናዊ ለራሱ የምትጠቅመው ካልሆነች ።

መለስ ዜናዊ በጣም የከረረ ጥላቻው በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ መጠነ ሰፊ ትላቻን ቂም አለው ። ስብሃት ነጋም ፤በዚሁ ጥላቻና ቂም በቀል የተነሳም ገና ከትግሉ መነሻ ጀምረው በግልፅ ያንፀባርቁት ስለነበር ለድርጅቱ ሊቀ መንበር ለሆነው አረጋዊ በርሄ በተደጋጋሚ ቢነገረው ፤በውሸት እነዚህ ሁለት ታጋዮች አትክሰሱ ለድርጅቱ በጣም ጠቃሚ ብዙ አስተዋጻኦ የሚያበርክቱ ስለሆኑ እናንተ የሥልጣን ( በወቅቱ አነጋገር ፤የመዝነት ሠኞች ) ናችሁ ተብለው ክተወገዙ ብዙም አልቆዩም ፤ ከያሉበት በብስራት አማረ ተለቅመው ተረሽነው ተገደሉ

፤ እነዚሁም ከላይ የተጠቀሱ እነ እቁባዝጊ በየነ እነ ፍስሃ ገብረዋህድ ወ.ዘ.ተ. ናቸው ። የመለስ ባህሪያት በሌሎቹ አመራርም የሚገኙ ናቸው ፤ሁሉ ከነ አረጋዊ በርሄ ጀምሮ እስከ አሁንው ስአት ያሉቱን የወያኔ

 

መሪዎች ኢትዮጵያ በመግዛት በስልጣን ላይ የሚገኙ ባህሪያት ነው ።ዛሬ ስልጣን ባኖራቸው የተባረሩ የህ.ወ.ሓ.ት.መሪ ነበር፤ የህ.ወ.ሓ. ውድቀት ለማየት አይፈልጉም ፤ ፤ተቃዋሚ ናቸው ለማስባል የሚጠቀሙበት ስዉር ዘዴ ፤እነ ስየ አብርሃ ፤አረጋዊ በርሄ ፤ግደይ ዘራጽዮን ወ.ዘ.ተ. ኢትዮጵያዊው ሕብረተሰብ ለማደናገር ፤ ለማጭበርበር የሚናገሩት  ዲስኩር ፤ላይኛው ሽፋን በማየት እውነት የመሰለው ሲያጨበጭብላቸው   ይስተዋላል

፤ይህ ግን በነሱ ለኡነት ለሃቅ አይደለም ፤ከሕብረተሰft ተቃዋሚ መስለው ለማደርና ለመታየት ያለመ እቅድ እንጂ ከልባቸው አንጻር ወያኔ ተነስተው አይደለም ፤ወያኔ በሚመሩበት ጊዜ አሁን መለስ ዜናዊ እየተከተለው ያለ ፀረ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ፤እነሱ እየሰሩት እየፈጸሙት የመጡት አደራ ተቀብሎ ነው ፤እያራመደው የቆየው ፤ እሱ ከሞተም፤ ተኪዎቹ የህ.ወ.ሓ.ት. ባለስልጣናት በተግባር እያዋሉት ያሉት ፤ስለዚህ በህ.ወ.ሓ.ት. የአመራር ለውጥ ሲከሰት ፖሊሲውና ፕሮግራማቸው ቅንጣት ታህል አይለወጥም ፤በነበረበት ባለበት የሚቀጥ ነው ። ለዚሁም ነው እኮ ህ.ወ.ሓ.ት. የማይለወጥ የማሻሻል ደረቅ አክራሪ ፀረ ኢትዮጵያና ህዝብዋ የሆነው ።. ጉሉቻ ቢለወጥ ጉሉቻ ነው ወጡ አያምርም ፤ በህ.ወ.ሓ.ት ውስጥም አመራር የነበረው ቢባረረ ቢሞት                                                                                                                  .ለውጥ ወይም ማሻሻል የሚባል ፈፅሞ የማይታሰብ የማይደረግ ጉዳይ ነው ። ይህ አፓርታይድ ሽብርተኛ ስርአት የሚያዋጣው ከስር መሰረቱ ነቅለህ መቅበር መደምሰስ ያለበት ፀረ ሃገርና ህዝብ መድሃኒቱ ይህ ብቻ ነው ።

ስብሓት ነጋ ማነው  ?

ስብሓት ነጋ እና መለስ ዜናዊ ቤተስብ ናቸው ሁለቱም የባንዳ ልጆች ናቸው የስብሃት አባት አቶ ነጋ የጣልያን ተላላኪ የነበሩ ሲሆኑ ቢያንቶኒ ነጋ ተብለው ይጠራሉ ቢያንቶኒ ማለት ተላላኪ ማለት ነው ፤እናቱ የኤርትራ ሰው ሲሆኑ፤ ታላቅ     ወንድማቸው ፀረ ኢትዮጵያ፤ የጣልያን ባንዳ ካራሚኘሪ ሹምባሽ ተክሉ መሸሻ የሚባሉ ናቸው ።በአጭሩ ታሪካቸው ካራሚኘሪ ተክሉ መሸሻ የስብሃት ነጋ ወላጅ እናት ታናሽ እህታቸው የአንድ አባት የአንድ እናት ታላቅና ታናሽ ወንድምና እህት ናቸው።ጣልያን በ1928 ዓ.ም ኢትዮጵያን እንደወረረ ሹምባሽ ተኽሉ መሸሻ ጣልያንን ተቀብሎ የወራሪው ፋሽሽት ጣልያን ምልምል ባንዳ ወታደር ሁኖ ወደ ደftብ ኢትዮጵያ ከፋሽሽት ጦር መሪዎች ጀኔራል አጎስቲን ጀነራል ናባሩ ጀነራል ናዚና ኢትዮጵያን ለመውጋት የዘመተ ባንዳ ነው

። በዚሁ ደftብ ኢትዮጵያ ጦርነቱ ከባድ ስለነበር አርበኞቹ በሱስት አቅጣጫ ተከፋፍለው ወራሪው ጣልያን ሲያስጨንቁት ከftር ራስ ደስታ ዳምጠው በነበሩበት ነገሌ የመርዝ ቦምብ የታጠቁ አይሮፕላኖች ጣልያን አሰማርታ ብዙ ጉዳት በአርበኞቹ ስለደረሰ ፤ራስ ደስታ ዳምጠውም በዚሁ ነገሌ ቆሰሉ ፤ይህን ለጣልያኑ ጀነራሎች ሹምባሽ ተኽሉ መሸሻም በአካባቢው ስለነበር ራስ ደስታ ዳምጠው መቁሰላቸው                                                                                                           ሪፖርት በማቅረብ ወደ ገftበት ተከታትሎ በሜሄድ ራሱ ቅላቸው ( ጭንቅላቱ) አንገታቸውን ጨምሮ በመቀረጥ ለጀኔራል አጎስቲኒ ትልቅ ጀግንነት እንደሰራ አቅርቦ ፤የደጃዝማችነት መአርግ ተሰጠው ። ታሪኩ የተገኘው ከታሪክ ባለሙያ የኢትዮጵያ ታሪክ ፀሓፊ ተክለ ፃድቅ መኩሪያ ።ይህ ፋሽሽት ባንዳ ተኽሉ መሸሻ የስብሃት ነጋ አጎት ነው ።ስለሆነም ስብሃት ነጋ በአባቱ በእናቱ ለክ እንደ መለስ ዜናዊ የባንዳዎች ልጅ ነው ።

የስብሃት ነጋ ባህሪ >>»ውሸታም ፤ የውሸት አሉባልታ አቀባባይ ፤ ሰካራም ፤ ዝሙተኛ ፤ ሲበዛም ተንኮለኛ ፤ ከፋፋይ አብረዉት የሚንቀሳቀሱ ፖሊት ቢሮውና ማእከላይ ኮሚቴው በመከፋፈልና በማጋጨት ተግባር ሁሉ ጊዜ እንደተጠመደ ፤ገዳይ ፋሽሽት በትግሉ በቆየበት ወቅት ከሓለዋ ወያኔ 06 የማይለይ በስው መግደል እድሜው ያሳለፈ ሽማግሌ ባንዳ ፤ታስረው የሚመጡ ሴቶች በማስፈራራት ወሲባዊ ግኑኝነት የሚፈጽም ሰው ነው ለነገታው የሚረሽናት የሚገድላት ይህ በተደጋጋሚ የሚሰራው ተግባሩ የወጣለት ፋሽሽት ባለጌው ስብሃት ነጋ ነው ።በትግሉ ወቅት ወሲባዊ ግንኙነት የፈጸመ ታጋይ በሞት የሚያስቀጣ ሲሆን ፤ የህ.ወ.ሓ.ት. ሕግና ስነስርአት በፖሊት ቢሮውና በአንዳንድ ማእከላይ ኮሚቴው ተግባራዊ ስለማይደረግ ልቅና አጉራ ዘለል ሙሰኞች ናቸው ፤ለምሳሌ እንደ እነ መለስ ዜናዊ ፃድቃን ገብረተንሳይ ብርሃነ ገብረክርስቶስ የማነ ኪዳነ ( ጃማይካ )ክንፈ ገብረመድህን ሳሞራ የኑስ ሓየሎም አርአያ ወ.ዘ.ተ. ከሴቶችም ድብቅ አመንዝራዎች ነበሩ፤እነዚህ ሴቶች የፖሊት ቢሮዎች ድብቅ የወሲበ ሥጋ አገልጋይ ናቸው ለምሳሌ አዜብ ጎላ፤ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር፤ ትርፉ ክ/ማርያም ፤መብራት በየነ፤ ሮማን ግ/ስላሴ ፤ሓድስ ባህታ ፤ለምለም ገሰሰ፤ወ.ዘ.ተ. ፤ በዚሁም የማእከላይ ኮሚቴው አሉ እነዚህ ግን እጣ ፈንታቸው በኋላ ኋል ሓለዋ ወያኔ ገብተው ይገድላሉ ።

 

የዚሁ ሁሉ መሪም ስብሃት ነጋ ነው ። ድብቅ ሙስና ብልግና በህ.ወ.ሓ.ት. ውስጥ እያደገ የመጣው ከትግሉ መነሻ ጊዜ ጀምሮ ነው ።       ስብሃት ነጋ እልም ያለ ፀረ ኢትዮጵያ ፀረ አንድነት ፀረ ህዝብ ነው ። ኢትዮጵያ በእጅጉ ይጠላታል ፤ለኢትዮጵያ ህዝብም አምርሮ ይጠላል ፤የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ፈፅሞ አይዋጥለትም ሲጠራውም ይህ አጋሥስ አበሻ ብሎ ነው የሚጠራ በየስብሰባው ። ስብሃት ነጋ በቀ.ኋ.ሥ.ተምሬ አለሁ ይላል ግን የደረጃ ትምህርቱ ዜሮ ነው ፤ከዚሁ ዝነኛ ዩኒቭርሲቲ ትምሮ አልወጣም የሚሉ በዛው የተማሩ ብዙ ናቸው

። ስብሃት ነጋ ክፉ ተኮለኛ ከመሆኑም የተነሳ መቀኝነት ቋጣሪ ነው ፤ሰው በሰውነቱ ይጠላል ፤ስብሃት የጠላውም አንዲት ሌሊት አያሳድረውም አንድ ሰው ይሁን መቶ ሺህ ሰዎችም ተረሽነው እንዲገደሉ ትእዛዝ ይሰጣል ይገደላሉ ፤ ከሁሉ በላይ አምርሮ የሚጣላው ለአማራው ህዝብ ነው ። አማራ ሲነሣ ጥርሱ ይጋጫል ከንፈሩ ይንቀ ጠቀጣል ፤ ፀረ አማራ ከምን ተነስቶ የአማራውን ህዝብ እንደሚጠላ ፤ መላ ምቶች አሉ የባንዳ ልጅ ከመሆኑ የተነሳ ነው የሚሉም አሎ ፤እሱም ብቻ አይደለም ሁሉ የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች በዚች ዓለም የመጀመሪያ ጠላታቸው አማራ ነው ።አላማቸውና ፖሊሳቸውም በቻሉት መንገድ የአማራ ህልውና ማጥፋት መደምሰስ ነውበለው የሚያምኑ አመራር ናቸው ።ሁሉ አመራር ለአማራው ህዝብ ሲጠሩት አህያ ፤አህዮች ብለው ይጠሩታል ፤ይህን ስም ያስተጋባ ለመጀመሪያ አረጋዊ በርሄ ሲሆን ለምመራው ትግል ይበጀዋል ያለው እስከ አሁን ወያኔና የወያኔ ደጋፊዎ ለአማራው አህያ በማለት ይጠሩታል ፤ ይህ አሳፋሪ ነገር መሪዎቹ ምን አይነት ሥር የሰደደ በህዝብ ጥላቻ ተመርዘው መፈጠራቸው በግልጽ የሚያሳይ ተግባር መሆኑ አረጋግጦ ያለፈ ነው ።

 

 

አረጋዊ በርሄ

አረጋዊ በርሄ ተውልዶ ያደገው ዓድዋ ከተማ እንዳ መድሃኒ ዓለም ሰበካ ውስጥ ነው ። በአባቱም በእናቱ የአርበኞች የጀግኖች ልጅ ነው ። በአጭሩ እንመልከት ።

የአረጋዊ ወላጅ አባት ቀኛ/በርሄ ገብረማርያም ይባላሉ ፤አባታቸው ፊታውራሪ ገብረማርያም ናቸው ትውልድ ዓድዋ ፤ቀኛ/በርሄ የቤተ ክህነት ትምህርታቸው ሙሉ በሙሉ በልጅነታቸው ያጠናቀቁ ሊቅ ናቸው ። ወራሪው ፋሽሽት ጣልያን በ1928 ዓ.ም. ኢትዮጵያን አንደወረረ ፊታውራሪ ገብረማሪያም የ20 ዓመት ልጃቸው በርሄ ገብረማሪያም አስከትለው ከኢትዮጵያ አርበኞች ጋር ተቀላቀሉ ፤በማይጨው ዘመቱ ፤ምድብ ቦታቸው አላጀ ግንባርም ነበር ፤የኢትዮጵያ አርበኞች በማስተባበርም ግንባር ቀደም መሪ በመሆን ወራሪው ጣልያን ያሽመደመዱ ጀግና መሆናቸው በህዝብ አድናቆት ያገኙ ናቸው፤በኢትዮጵያ ታሪክም የገድሉ ታሪካቸው በባህረ መዝገብ የተጻፈ ኢትዮጵያዊ ጅግና ናቸው ፤ ፤በመጨረሻ አላጄ ግንባር ለናት ሃገራቸው ኢትዮጵያ መስዋእትነት ከፍለው በፋሽሽት ጣልያን በተቶኮሰው የአይሮፕላን ቦምብ ተመተው ተሰውተዋል ።አይበገሬው ወጣቱ ልጃቸው በርሄ ገብረማሪያም እስከ መጨረሻው ከአርበኞቹ ሳይለይ ወራሪው ጣልያን እየተዋጋ ቆይቶ ፤ ጣልያን ተሸንፎ በድል አርበኝነት ኢትዮጵያ ሙሉ ነፃነትዋ ከተቀዳጀት ወጣቱ በርሄ ገብረማሪም አረንጓዴ ብጫ ቀይ የሚወዳት ሃገሩ ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማው ተሸክሞ ዓድዋ ገባ ።

አረጋዊ በርሄ በወላጅ እናቱም የአርበኛ ልጅ ነው ፤ የእናቱ ወላጅ አባት       ፊታውራሪ በዛብህ ፍላቴ ይባላሉ የዓድዋ ባላባት ፤ፋሽሽት ጣልያን በ1928 ዓ.ም .ኢትዮጵያን እንደወረረ  ከአርበኞች ተቀላቀሉ የዘመቻ ምድባቸው ማይጨው ስለነበር ፤ማይጨው ዘምተው ከራስ ካሳ ኋይሉ የጦር ቀጠና መሪ ሆነው 5ዓመት በአርበኝነት እናት ሃገራቸው ኢትዮጵያ ያገለገሉ የ5 ( የአምስት ) አርበኛ ናቸው ።ኢትዮጵያ ነፃነትዋ እንደተቀዳጀችም ፤በቀዳማዊ ኋይለ ሥላሴ ንጉሰ ነገሥት ዘ ኢትዮጵያ መልካም ፍቃድ አዲስ አበባ ድረስ ተጠርተው ሚያዝያ 27 ቀን 1945 ዓ.ም በክብረ በዓሉ ፤ በቦታው በመገኘት የልጅ መዓርግ ከነሙሉ የመዓርግ ልብስ ተሸልመዋ የአምስት ዓመት የአርበኞች የተለያዩ መዳሊያዎች የተሸለሙ አርበኛ ። በልጅ በዛብህ ፍላቴ ፍላጎት መሰረት የመንግሥት ሥራ ይቅርብኝ ልረፍ ስላሉ ፤ለሃገርህ ኢትዮጵያና ለንጉሠ ነገሥትህ ታማኝ ሆነህ አምስት ዓመት ሙሉ ከጠላት ተፋልመህ ለሃገርህ ነፃነት ጉልህ ሚና ያበረከት የአንድ አውራጃ ገዥ ደሞዝ

 

በየወሩ የሚከፈልህ የጡሮታ ክፍያ እድሜህ ልክ ከዛሬ ጀምሮ ተፈቅዶልሃል ተብለው በክብር የተሰናበቱ ጀግና ናቸው ።

አረጋዊ በርሄ በጥሩ ቤተ ሰብ ያደገ ፤ ተማሪ በነበረበት ሰው አክባሪ ትሁት ታዛዥ መኖሩን የዓድዋ ነዋሪ ህዝብ ያውቃል ። በትምህርቱ ጎበዝ ፤ወላጆቹ ተልቅ ተስፋ ያሳደሩበት ነበር ፤አያቱ ልጅ በዛብህ ፍላቴ ሲጠሩት ያይኔ ብርሃን ብለው ነው የሚጠሩት ፤በጠቅላላ ቤተ ሰft ሁሉ የሚኮራበት ነበር ።በመጨረሻው በረሃ ወጥቶ በፀረ ኢትዮጵያዊነት ተሰልፎ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን የትግራይ ዜጎች በመግደል መሰማራቱን በየቀኑ በሚደርሳቸው ዜና ረግመዉት ፤ውጉዝ ከመ ስይጣን ብለዉት ከዚህ ዓለም አልፈዋል ። ከዚህም የከፋ ነገር የለም ።

አረጋዊ በርሄ ከእነዚህ አብራክ የተፈጠረ ልጅ ፤360 ዲግሪ ተገልብጦ ለምን ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ሆነ ? የሚለው ጥያቄ ገና ክ1964 ዓ .ም የተነሳ ጥያቄ ነው ።መልስ ያላገኘ ፤ግን መልስ አለው ፤ በዙም ባይባሉም ጥቂት ምሁራኖች ለምን ኢትዮጵያን ጠላህ ? የሚሉትም ነበሩ የሚሉም አሉ፤መልሱ ደግሞ አረጋዊ በርሄ በባዕዳን ፀረ ኢትዮጵያ ኋይሎች በጥቅም የተገዛ በተክለ ሰውነቱ ባንዳ አተላ ዝቃጭም ነው ።

የአረጋዊ በርሄ ጥልቅ ባህሪያት ፤ 1ኛ  የወጣለት ፀረ አማራ ነው ። አማራን ይጠላል ፤አማራን ያወግዛል ; በዙ ጊዜ እኔ ራሴን የሰማሁት በትግሉ ወቅት አማራ ብሎ እንዳይጠራ ስሙን ስለሚጸየፈው ‹አህዮች ›እያለ ነው የሚጠራው ፤በስብሰባም ይሁን በተገኘው አጋጣሚ ።እነዚህ አማሮች ነፃነትዋ ጠብቃ ለብዙ ሺህ ዓመታት ትግራይ አፄ ዮሓንስ ከሞቱ በኋላ ትግራይ በሸዋ አማራ መንግሥት ቅኝ ግዛት ሥር ወድቃ ዛሬ በአማራ አገዛዝ እየማቀቅን እንገኛለን ፤አረጋዊ ይህ ለህዝብ በሚያስተምርበት እያለቀሰ ነው ፤የሚናገርው ።

2 ኛ ከሃዲ ውሸታም ነው ። ያደረጋት የሰራት በግልጽ የታየው የተሰራው ከተጠያቂነት ለማምለጥ ፤ በአፍጢምየ ድፍት ያርገኝ እኔ አልዋልኩበትም ብሎ ይክዳል ለምሳሌ የህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም አልጻፍኩም አላዘጋጀሁም ። ሰውም የገደልኩት የለኝ ንጹህ ነኝ ፤ይላል ።

3 ኛ አምባገነን ፀረ ዲሞክራሲ እኔ ያልኩት ይሁን እኔ የምለው ተቀብሉ እናንተ የምትሉት አያዋጣ እያለ በቀጥታ የሚክራከር ሰው ፡በውስጡ የያዘው ሃሳብ አለው ተቃዋሚ መስሎ በመቅረብ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ሙሉ በሙሉ በህዝብ እንዲወገዝና እንዲጠላ ከሥልጣኑ እንዲወገድ አይፈልግም ፤ምክንያቱም በትግሉ ወቅት በህዝብ ላይ በኢትዮጵያ ሏላዊነት የፈጸሙት ከባድ ወንጀሎች ሃገር ዛሬ ፈርሳለች ኢርትራ ተገንጥላለች ፤ሰፊ ለም ታሪካዊ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን መንግሥት ሽጠዋል፤ወ.ዘ.ተ. ይህን በከፍተኛ ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው ፤ ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራው ህዝብ ከባድ የዘር ማጥፋት ወንጀል አካሂደዋል ፤ይህ ራሱ በከባድ ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው ። ሊላም ብዙ አለ ከዚሁ ፍርሃትና ጭንቀት የሚከላከልላቸው የህ.ወ.ሓ.ት. ስርአት ሲኖር ብቻ ነው ። ስለዚህ ተቃዋሚ ቢሆኑም በተቃዋሚ ኋይሎች ሰርገው በመግባት ቢያንስ ቢያንስ ወያኔ ዕድሜውን ለማራዘም የሚያስፈልጉት ነገሮች ከማስተካከል ወደ ኋላ አይሉም ።

አረጋዊ በርሄ የህ.ወ.ሓ.ት. ዋናው መስራች ነው ፡ይህ ድርጅት የተመሰረተው በ1964 ዓ.ም. ነው ።በዛን ጊዜ ስሙ ብሄረ ትግራይ ድርጅት ነው ፤ተከታይ ግን አልነበረውም ብቻው አረጋዊ ነበር፤ከብዙ ውጣ ውረድ ክ3 ዓመት በኋላ መስከረም  ወር መጀመሪያ 1967 ዓ.ም. ሰባቱን ሰዎች ተሰባስበው ማ.ገ.ብ.ት. ፈጠሩ ሊቀመንበሩ አረጋዊ በርሄ ሆነ ፤የነበረው ሃላፊነት ።

1 ኛ የድርጅቱ ፕሮግራም ማዘጋጀት ይህ ግንባር ቀደም ሆኖ ወደ ሥራው ተሰማራ ፤ ፕሮግራሙ ከመነሻው እስከ መጭረሻው 1 ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፤ 2 ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፤ 3 ጎጠኛ ከፋፋይ ፤ 4 ኢትዮጵያ በዘር በቋንቋ ተከፋፍላ ተበታትና ከዓለም ካርታ ውጭ እንድትሆን በማድረግ ያዘጋጀው ፤ 5 በኢትዮጵያ ያሉት ብሔር ብሔረሰቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላምና አንድነት ፍቅር እንዳይኖር ህዝft በእርስ በርስ ግጭት እንዲተላልቅ ፤የሚፈጥር አርጎ ፕሮግራሙን ያዘጋጀ ። 6 ሙሉ በሙሉ ፀረ አማራ ፤ የአማራ ህዝብ የፈጀ ዘሩን ያጠፋ ።በዚሁ ፕሮግራም በሃላፊነት ተጠያቂው አረጋዊ በርሄ ነው ።

2 ኛ በፕሮግራሙ ውስጥ መስፋፋትና የመሬት ነጠቃ ያካተተ ሆኖም ተዘጋጀ ።በዚሁ መሰረት ሃላፊነት በጎደለው በጉልበት በኃይል ተግባራዊ የሚደረጉ ።

 

ሀ— የሰሜን ጎንደር የአማራ ለም መሬቶች ፤    ወልቃይት ፤ጠገዴ ፤ ጠለምት ፤ ቃፍታሁመራ ወደ ትግራይ ያጠቃለለ ፤ይህ መሬት አማሮች በስልጣናቸው በጉልበታቸው ከትግራይ ነጥቃው ወደ ግዛታቸው ያጠቃለሉት ነው ፤ብሎ በወሰነው አረጋዊ በርሄ ፤የትግራይ መሬት ነው ፤ትብሎ በፕሮግራሙ በእስትራቴጂ ደረጃ ወደ ፕሮግራሙ ገባ ። እነዚ ቦታዎች ግን ለስንት ሺህ ዘመናት የአማራ መሬትና ግዛት እንጂ የትግራይ ሆነው አያውቁም ፤በአማራነታቸው የሚታወቁ ዋናው የሁሉ የአማራ ህዝብ መሰረት እዚሁ ነው ።

ለ—- ሰሜን ወሎ ፤በሰሜን ወሎ የሚገኙ መሬቶች የወሎ ህዝብ መሰረታዊ የኑሮው የሂወቱ ምንጭ የሆኑት አለውሃ ምላሽ በመባል የሚታወቆ ፤ ራያና ቆቦ ፤ ኦፍላ ደራ ፤ ወልድያ ፤አላማጣ ወ.ዘ.ተ. ወደ ትግራይ በፕሮግራሙ ገባ ። እነዚህን ሰሜን ጎንደር ሰሜን ወሎ በተመለከተ ያካተተው አረጋዊ በርሄ መቅድም በሚለው አርእስት ገጽ v ወይም ገጽ 5 ማለቱ ነው ፤በራሱ የእጅ ፅሁፉ ይገኛል ፤ፕሮግራሙን ተመልከቱ ።

<‹ <የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ድርጅት >» በዋናነት ያዘጋጀው ፕሮግራም ወይም የአቋም ፖሊሲ                                                                                                                    አረጋዊ ብርሄ በየካቲት 5 ቀ 1968 ዓ.ም .በዲማ ኮንፈረንስ የፀደቀው ፤ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ሕገ መንግሥት የሆነው ። የአማራ ህዝብ ማንነት የነጠቀ ፕሮግራም አማራው በገዛ ሃገሩ ሁለተኛ ዜጋ የሆነባት ኢትዮጵያ ፤ያደገበት እትብቱ የተቀበረበ ወልቃይት ጠገዴ ጠለምት፤ ውጣ ይህ የትግራይ መሬት እንጂ ያንተ አይደለም ተብሎ አማራው የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ለስደትና ረሃብ ችግር የተዳረገበት ዘመን ነው ፤ ይህ ሁሉ መከራን ሲኦል የወረደውም በህ.ወ.ሓ.ት. መስራቹና የፕሮግራሙ አዘጋጅና ፈላስፋው በአረጋዊ በርሄ ነው ።

አረጋዊ በርሄ የውልቃይት ጠገዴ ጠለምት ቦታዎች ለመያዝና ለመቆጣጠር ቀደም ሲል ከ1969 ዓ.ም. በትንሹ የተጀመረው ፀረ አማራ ዘመቻ             በታህሳስ ወር 1972 ዓ .ም. በከፋ መልኩ ተጠናክሮ አረጋዊ በርሄ በሚመራው ድርጅታዊ መዋቅር የዘር ማጥፋት ዘመቻው ሁሉ የተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ፤ 1 ስብሃት ነጋ 2 ግደይ ዘራጽዮን 3 አባይ ጸሃየ 4  ሥዩም መስፍን     5 መለስ ዜናዊ ከስየ አብርሃ ተደራቢ በመሆን የህ.ወ.ሓ.ቱ . ዋናው ወታደራዊ መሪ አረጋዊ በርሄ እነዚህን አመራሮች በወልቃይት በጠለምት በጠገዴ በየአቅጣጫው በማሰማርት ፋታ በማይ ሰጥ ሁኔታ የአማራው ሰሜን ጎንደር ህዝብ በተቻላቸው ሁኔታ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል።ይህ የዘር ማጥፋት ድርጊትም አማራው በተገኘበት እንዲገደል ፖሊት ቢሮው አረጋዊ በርሄ ስብሃት ነጋ  ግደይ ዘራጽዮን  አባይ ፀሃይ  ሥዩም መስፍን መለስ ዜናዊ ባሳለፉት ውሳኔ ገና ሲጀምሩት በ1968 ዓ .ም መጨረሻ . ማንም የትግራይ ተወላጅ ያልሆ ከትግራይ ይውጣ፤ትግራይ የመኖር መብት የለውም ትግራይ የትግራዊያን ናት ተብሎ ፖሊት ቢሮው ያሳለፈው ውሳኔ ለየርጅኑ ማለት ፤ርጅን 1 ሽሬ አውራጃ ሰመማና ጭላ ከፊል አክሱም ማለት ነው ርጅን 2 ከፊል አክሱም ዓድዋ ተምቤን ርጅን 3 ዓጋሜ፤ ሁሉት አውላእሎ እንደርታ ራያ ( ማይጨው ) በእነዚህ አካባቢ( ሓራ ) ነፃ መሬት በወቅቱ ይህን ያህል ነፃ መሬት ባይኖርም ግን በየቦታው ለሚገኙ ፤የህዝብ ግኑኝነት ትእዛዙ በማስተላለፍ አማራው በቀን በለሊት ከያለበት እየተለቀመ ሓለዋ ወያነ ( 06) እየተወሰደ የተገደለው አምላክ ይቁጠረው፤ በዚሁም ላይ ጠቅላላ ያፈራው ንብረት ሃብቱ ገንዘft እየተወረሰ በጡሮታ የወጣ በተለያየ መስክ ተሰማርቶ እየሰራ የሚኖረው አማራ በመሆኑ ብቻ የጥፋት ኖህ ወረደበት ። ይህም ለአመታት ዘለቀ በዚህ የግድያ መቅዘፍት ብዙ የትግራይ ሰው የአማራ ደጋፊ እየተባለ ታስሮ የተገደለው በጣም ብዙ ነው ፤ሃብቱ ንብረቱም እይተወረስ ቤቱ የፈረሰው የትግራይ ሰው አምላክ ይቁጠረው ።

ይህ ሁሉ ችግር የፈጠረው አረጋዊ በርሄ በመሪነቱ መሰረት ያወጣው ፕሮግራም የሰሜን ጎንደር መሬት በመስፋፋት የትግራይ ግዛት ለማድረግ ሰሜን ወሎ ጨምሮ ታላቅዋን የትግራይ መንግሥት ለመመስረት ፤ በፕሮግራሙ ወይም ፖሊሲ መሰረት በንፁሃን ኢትዮጵያውያን ላይ በወልቃይት ጠገዴ ጠለምት የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመ ወንጀለኛ መሪከነ ድርጅቱ ።

መስፋፋት<<‹ሕገ ወጥ ነው ፤በማንም ህብረተሰብ ተቀባይነት የለውም ፤ መስፋፋት ፀረ ማንነት ፤ፀረ ዜጋም ነው ፤የፋሽሽት መለያም ነው ፤መስፋፋት የሕብረተሰዉን ዘር ለማጥፋት ልዩ መሳሪያም ነው፤ የአማራ ግዛት ዳር ድንበር ተሻግረህ ራሱ የቻለ ታሪካዊ፤ ለስንት ሺህ ዘመናት በኢትዮጵያ ነገሥታት ተከብሮ የኖረው የግዛት ደንበር በጉልበትህ ተማምነህ     ባዘጋጀው ፕሮግራም ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ጠለምት ቃፍታ ሁመራ ወደ ትግራይ በማስገባት የራሳቸው መሬት ለማስፋፋት ነዋሪው ባለቤት በሆነው ህዝብ ዘሩን አጥፍተው መሬቱ በሃል

 

ተቆጣጥረዉታል ።ይህም በዓለም አቀፍ በከባድ ወንጀል ከማስጠየቁም በላይ ፤ተስፋፊነት የዘር ማጥፋት ወንጀልም ነው ።

የወልቃይት ፤ጠገዴ ፡ጠለምት ፤ቃፍታ ሁመራ ፤ በ1968 ዓ.ም. ባፀደቁ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ድርጀት ፖሊሲና የአቋም ፕሮግራም መሰረት፤ ዛሬ ማንነቱ የተገፈፈ ህዝብ ፤ የትውልድ ቀዩ መሬት ተነጥቆ፤ ተበታትኖ በስደትና ችግር ወድቆ የሚገኝ ፤ የአማራ ህዝብ ነው ፤ ከሞትና ከስደት የተረፈው እዛው የሚገኝ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ እንደሁለተኛ ዜጋ ተቆጥሮ ውጣ ከዚህ የትግራይ ቦታ እየተባለ ለመኖር እንኳን መብት የለውም ። ይህ ችግርና መከራም የፈጠረው ያመጣው አረሜኔው የናዚ ውላጅ አረጋዊ በርሄ ነው ።

በ1974 ዓ .ም. የሱዳን መግሥት በፕረዚዳንት ጃእፈር ኒመሪ የሚመራ የሱዳን መግሥት በወቅቱ በነበሩ የገዳሪ ጠ/ገዢ ከህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ተደራድረው በ1902 ዓ.ም.. በጊዜው የሱዳን ካርቱም አስተዳዳሪ የነበረው ሻለቃ ጋዊን የተባለ ካለመብቱ የኢትዮጵያን ሏላዊነት በመጋፋት በራሱ ፍላጎት ሱዳንን የለም መሬት ባለቤት ለማድረግ በሕገ ወጥ መንገድ የኢትዮጵያ መሬት ወደ ሱዳን ለማካለል ያዘጋጀው ፤ሕገ ወጥ ነው ተብሎ ማንም የማያውቀው ውድቅ የተደረገ ካርታ ፤የኒሜሪ መንግሥት ካርታውን ይዞ ከህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ተደራድረን በእነሱ እናገኘው ብሎ በላከው ደብዳቤ ፤በአረጋዊ በርሄ የሚመራው ፖሊት ቢሮ አመራር ተቀብሎ ፤አረጋዊ በርሄን ስብሃት ነጋ ግደይ ዘራጽዮን ሆነው ፤ለዳግማይ ቀጦሮ ተወስኖ ። በ1975 ዓ ም .ሱዳን ገዳሪፍ ተግናኝተው ፤የህ.ወ.ሓ.ት .መሪዎች 1 ዋናው የftዱኑ መሪ አረጋዊ በርሄ 2 ስብሃት ነጋ 3 ግደይ ዘራጽዮን 4 አባይ ፀሃይ 5 የውጭ ሃላፊ በመሆኑ አስተናጋጁ ሥዩም መስፍን 6 መለስ ዜናዊ ተባብረው የኢትዮጵያን መሬት ካለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሳልፈው ሰጡ መስከረም 1975 ዓ ም ። ወያኔም ለዚሁ ውለታ የስዳን መንግሥት ሙሉ እውቅና ሰጠ ሁሉ አስፈላጊ ነው የሚባል ለወያኔ ሙሉ እርዳታ እንደሚያደርግ ፤ሌሎች የአረብ ሃገራትም ለህ.ወ.ሓ.ት. እውቅና እንዲሰጡ አደርጋለሁ ብሎ በገባው ቃል መሰረት ግብፅ፤ሊብያ ;ኢራን

;ኢራቅ ;ወ.ዘ.ተ ከመቅፅበት እውቅና ሰጡ ።እላይ ያለዉን ካርታ ይመልከቱ ። ይህ በህ.ወ.ሓ.ት. ፈላጭ ቆራጩ መሪ አረጋዊ በርሄ አመራር በኢትዮጵያ ላይ የተፈፀመ የወንጀል ክህደት ነው ። የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ለጊዝያዊ ጥቅም የሸጡት የኢትዮጵያ መሬት ዛሬ በህዝft ፈጥሮት ያለውን ችግር ፤እነዚህ በፈጠሩት ሰበብ ነው ።

ባለፈው እየተፈጸመ የመጣው የዘር ማጥፋት ወንጀል የመሬት መስፋፋት ፤የአማራው ማንነት ባህሉ ተነጥቆ ከትውልድ ቦታው ተፈናቅሎ ተባሮ .ኢትዮጵያዊ ኩሩ ፤የሃገር መከታ ህዝብ ፤ ለሞተላት ኢትዮጵያ ፤ ከጠላት እየተከላከለ ሏላዊነትዋ ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያረካከበ የመጣ የአማራው ህዝብ ፤ዛሬ በህ.ወ.ሓ.ት.ወያኔ በጠላት ተፈርጆ ሁለተኛ ዜጋ ሆኖ ሲገደል ሲታሰር መኖሪያ ያጣ ህዝብ ሆኖ በችግር በሰቆቃ እየተገረፈ ነው ። እነዚህ ሰሜን ጎንደር፤ ሰሜን ወሎ በታሪክም የአማራ መሰረት ናቸው ። ፤ሌላው ኢትዮጵያዊ አኦሮሞው አፋሩ ወላይታው ጋምቤላው ቆቱው ሃረሬው ወ.ዘ.ተ.፣ አብሮ በወያኔው ፋሽሽቱ እየተጠቃ ነው ።ይህ ጥቃት የሁሉ ኢትዮጵያዊ ዘር ጥፋት የሁሉ ኢትዮጵያ ሞት ስደት ችግር ሶቆቃ ፤የሁሉ ኢትዮጵያዊ ማንነት ማጣትን መነጠቅም ነው ። ይህን ሁሉ በኢትዮጵያና በህዝብዋ እየደረስ የመጣው እየደረሰ ያለው ፤ኢትዮጵያና ህዝብዋ በአንድነት እንዳይ ኖሩ በታትነን እርስ በሩሱ አጋጭተን ትምክህተኛው ኢትዮጵያዊ ሃገር አልባ እንደርገዋለ ። ይህ ሁሉ ሤራም የኢትዮጵያ የውጭባእዳን ጠላቶች በእጅ አዙር እነ                                                                                                    አረጋዊ በርሄ በመያዝ ኢትዮጵያ በሞት አፋፍ አድርሰዋታል ።አረጋዊ ብርሄ በኢትዮጵያ እየደረሰ ላለው ችግር አሁንም ግንባር ቀደም ተጠያቂ ነው ።እሱ ገና ከትግሉ መጀመር አዘጋጅቶ ያመጣው ፕሮግራም ( ፖሊሲ ) አሁንም ሃገር እየፈረሰች ናት እስከ 1977 ዓ .ም . ህዝብ እያጠፋ የመጣ የዘር ማጥፋት ያስፈጸመው የፈጸመ የድርጅቱ ፈላጭ ቆራጭ የነበረ ሰው በሥልጣንሽኩቻ ቢባረርም ከያዙም በስፋት ቀጠሉበት እስከ 1977 ዓ ም . አረጋዊ በርሄ ሲስራቸው የነበሩ ወንጀሎች ሌሎቹ ተረክበው እየቀጠሉበት ይገኛሉ።

1  ግደይ ዘራጽዮን

ግደይ ዘራጽዮን የማ.ገ.ብ.ት. መስራች በሥልጣንም ሁለተኛ ሰው ነው ።ይህ ሰው በትውልዱ ኢርትራ ክ/ሃገር ነው ።ወላጆቹም በ1952 ዓ.ም. ወደ አክሱም በመምጣት የንግድ ሥራቸው በመቀጠል ክህዝብ ተፋቅረው ተስማምተው የሚኖሩ የቤተ ክርስትያን ሰዎች ጥሩ ኢትዮጵያውያን ናቸው ።

 

ግደይ ዘራጽዮን ልክ እንደጓደኛው አረጋዊ በርሄ 360 ዲግሪ ተገልብጦ ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፀረ ኢትዮጵያ አንድነት ፀረ ህዝብ ፀረ ዲሞክራሲ አረሜኔ ጨካኝ ርህራሄ የሚባል የማያውቅ ወዶ ገባ ባንዳ ሃገር አጥፊ ሰው ነው ።

ግደይ ዘራጽዮን በማ.ገ.ብ.ት. ምስረታ ም/ሊቀመንበር በየካቲት 11 ቀን 1967 ዓ . ም. ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ ( ተ.ሓ.ህ.ት. ) እንደተመሰረተም አረጋዊ በርሄ ሊቀ መንበር ሲሆን ግደይ ዘራጽዮን ም/ ሊቀመንበር በመሆን በሃላፊነት የነበረ ቀጥሎም በየካቲት 5 ቀን 1968 ዓ . ም .በተካሄደው የዲማ  ኮንፈረንስ (ጉባኤ ) የአመራር ምርጫ ሲደረግም ተመርጦ የም/ሊቀ መንበርነቱ እንዳለ በመቀጠል ሥልጣኑ ጨበጠ ፤ይህ በዚሁ እንዳለ የካቲት 5 ቀን 1971 ዓ . ም. በተካሄደው 1ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በተደረገው የአመራር ምርጫ ተመርጦ የድርጅቱ ስም ከተሓ.ህ.ት. ወደ ህ.ወ.ሓ.ት. ይህም ማለት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ፤በሆነበት የህ.ወ.ሓ.ት. ስብሃት ነጋ ሊቀመንበር ሲሆን ግደይ ዘራጽዮን ም/ሊቀ መንበር ሆኖ ተመርጦ እስከ 1977 ዓ. ም . የድርጅቱ ሃላፊ በመሆን የሰራ ቁንጮ መሪ ነው ።እምብዛም ፖለቲካዊ እውቀትና ችሎታ የሚያጥርበት ድሃ የንግግር ችሎታም የሌለው መሪ ።ጨካኝ አረሜነ ተብሎ የተነገረለት ።

በዚሁ ጉባኤ የተሰራው አ ሻጥር ድርጅቱን አጥብቀ በኢ- ዲሞክራሲ ለመቆጣጠር ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ህዝብ አንድነት የሆኑት መሪዎች ወደ ሃላፊነት የመጡበት ጊዜ ነው ።ይህ ሁሉ የተደረገውም በአረጋዊ በርሄ ነው።በዚሁ መሰረት ።

1 ስብሃት ነጋ                        የድርጅቱ ሊቀ መንበር                      ፖሊት ቢሮ

2 አረጋዊ በርሄ                     ወታደራዊ አዛዥ የድርጅቱ የበላይ ሃላፊ ፖሊት ቢሮ

3 መለስ ዜናዊ                     የማርክሲሲት ለኒኒስት አደራጅ ኮምሽን ሃላፊና የካድሬዎች አሰልጣኝ በየቦታው የሚመደft ካድሬዎች መዳቢና ተቆጣጣሪ ፤እንዲሁም በፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ምክትል ሃላፊ ። በማእከላይ ኮሚቴ ደረጃ ።

4 ግደይ ዘራጽዮን                    ም/ሊቀመንበር                 ፖሊት ቢሮ

5 አባይ ጸሃየ                           የፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ሃላፊ    ፖሊት ቢሮ

ተጨማሪ ያንብቡ:  የበደኖና የአሰቦት ገዳማት የ1984 አሰቃቂ ጭፍጨፋ በደብረሊባኖስ ሊደገም ነው እንድረስላቸው

6 ሥዩም መስፍን                   የውጭ ጉዳይ ሃላፊ             ፖሊት ቢሮ

እነዚ ሰው በላ አረሜኔ COLD BLOODED    መሪዎች ድርጅቱን የተቆጣጠሩት ።ይህ ሁሉ ቅንብርም የተዘጋጀው በተግባር የዋለው በአረጋዊ በርሄ ፀረ ዲሞክራሲ ሥራ ነው ። ወደ ግደይ ዘራጽዮን እንመለስ ፤

ግደይ ዘራጽዮን ሰው ሆኖ በሰው ልጅ ቀንጣት ርህራሄ የሌለው ጨካኝ አረሜኔ አውሬ ፍጡር ነው ፤ በተለያየ ጊዜ ፤የትግራን ህዝብ ለሰንሰለታዊ የአማር ቅኝ ተገዥ፤ ትግራይም የአማራ ቅኝ ግዛት ሆና ለድህነትና ለክፉ ስቃይ የዳረጋት አማራ ነው እያለ ሃቅነት የሌለው የውሸት ፕሮፓጋንዳው በየስብሰባው እንደ ገደል ማሚቶ እያራገበ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ወንድማሞች አማራና ትግራይ በደም ለማቃባት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረውም ፤ይህ ደካማ ፀረ ህዝብ ሃሳft ደግሞ ተቀባይነት አላገኘም የሚሰማውም አንድም አልነበረም ።ከዚህ ተነስቶ ግደይ አማራ በመጥፎ ውግዘት ያወግዘዋል ። በመሰረቱ ግደይ ዘራጽዮን አማራውን በሚገባ አያውቀውም ፤ይህን ያህል ውግዘት በሄደበት የሚወረውረው ።

ግደይ የህ.ወ.ሓ.ት. መሪና ም/ሊቀመንበር  ነው ፤በወቅቱ ተ.ሓ.ህ.ት. በ1968 ዓ.ም..በግንቦት ወር በftምበት

»ሸላሎ ታች አድያቦ ውስጥ >» የተቋቋመው 06<‹ሓለዋ ወያነ መሪና አዛዥ ምክትሉም አበበ ተክለሃይማኖትና ብስራት አማረ ጋር በመሆን ፤የፈጸመው ግድያ ለሰሚው ጀሮ ቀፋፊ እናም አስደንጋጭ ነው ። ይህ ftምበት በዚሁ ጊዜ ትልቁ የተ.ሓ.ህ.ት. 06 ነው፤ በዚሁ ጊዜ ከየትም እየተለቀመ ምንም ጥፋት ወንጀል ያልሰራ ንጹህ ዜጋ             ፤ተ.ሓ.ህ.ት. የሚቃወም ፤የኢድዩ አባል ነህ እየተባለ ፤የኢ.ህ.አ.ፓ አባል ነህ እየተባል ፤የደርግ ሰላይ ፀረ ኤርትራ ትግል ነህ እየተባለ የተ.ሓ.ህ.ት. መሪዎችና የህዝብ ግንኙነት ካድሬዎች ስም በመለጠፍ እዚሁ ጭር ያለ በረሃ ታስረው የሚሰቃዩ ቁጥራቸው ብዙ ሲሆኑ ፤በግደይ ዘራጽዮን

 

መሪነት ከባድ የሶቆቃ ቶርቸር ለመጥቀስ 1 1 ያለምግብ ውሃ ብርሃንም እንዳያዩ በጨለማ አፍኖ ለቀናት ማሰቃየት 2፤ወንድ ሴት እርቃናቸው በማውጣት ውጭ ከግንድ አጣብቆ በማሰር ቀን በፀሃይ ለሊት በብርድ ፤ 3 በጣም የፈላ ውሃ በታሳሪው ጭንቅላት ላይ በመድፋት ወይም መልቀቅ ፤ 4 በወንድ ብልት 5 ኪሎ አሸዋ ማንጠልጠል ፤በሴትም በግራና በቀኝ ጡትዋ የአሸዋ ከረጢት ማንጠክጠል ለረጅም ሰዓታት በማሰቃየት፤ 5 ጎማ በለበስ ወፍራም የኤለትሪክ ገመድ ሆድ እግሩና ጀርባው ቆዳው እስኪላላጥ ደብድቦ ማሰቃየት ፤ 6 ሴት እርቃንዋን ወጥታ ማህፀንዋ ላይ መግረፍ 7 በመርዝ መግደል ምግብ ላይ በሚጠጣ ወህ ተጨምሮ 8 በጋለ ብረት በሆድ እቃው ማስገባት፤ሰፊ ጉድጓድ ራሳቸው የሚረሸኑ ቆፍሮው ተመልሰው ጉድጓዱ ውስጥ በማስገባት በጥይት ተደብድበው ተረሽነው በጅምላ መግደል ፤ ወ.ዘ.ተ. ወደ ዚሁ ማሰቃያ ማእከል የገባም አይቆይም እጃቸው ላይ ይሞታል ። የአምላክ ፍጡር ያጠፋ መሪ ግደይ ዘራጽዮን ነው ።በዚሁ ሰቆቃ የተገደሉ አዛውንቶች ሰላማዊ ዜጎች ውስጥ ለአብነት ያህል ፤ አቶ ገብረሊባኖስ መዝገft ፤አቶ ተወልደ ገብረሥላሴ ፤አቶ አበበ ገብረማሪያም ፤አቶ ሙሉጌታ ደስታ ፤ወ/ሮ ሥላስ ፤ወ/ሮ መድህን ፤ አቶ ወልደ ንጉሥ ፤አቶ ገብረጻድቅ ፀጋይ ፤የ10 አለቃ ጥላሁን ፤ ቄስ ፅጌ አቶ በላይ ባህታ ይገኙበታል ፤በዚሁ ጊዜ የተገደሉት ገዳዮቹ በብስራት አማረና በአበበ ት/ሃይማኖት የሚመሩ ገዳይ ታጋዮች በለቀቁት ተባራሪ ውስጥ ለወስጥ እንዲታወቅ ብለው ያሰራጩት ከ4500በላይ ህዝበ አዳም በ10ቀናት ውስጥ በጅምላ ጉድጓድ ተረሽንው መገደላቸው የተረጋገጠበት ወቅት ነው ። ታጋዩ በሕንፍሽፍሽ ሰላማዊ ዜጋ ፀረ ወያኔ የሚል ስም እየተሰጠ ፤በግደይ ዘራጽዮን መሪነት ftምበት ውስጥ ተገድለዋል ።ይህ ሰው በሻዕብያ የትማረኩ ምርኮኞች ሻዕብያ ስንቀ ስጥቶ ወደ ትውልድ ቦታቸው አሸጋጉርዋቸው በማለት የላካቸው ግደይ ተቀብሎ 300 መቶ ምርኮኞች ረሽኖ መግደሉን ሕዳር ወ 1971 ዓ.ም. ጊዜ ሁሉ ታጋይ የሚያውቀቅ ሓቅ ፤በዚሁ ድርጊቱም ናዚ አዶልፍ ሂትለር ተብሎ መወገዙም ራሱ ግደይ የሚያውቀው የትናንት ትዝታው ነው ።

ግደይ ዘራጽዮን  የትግራይ ህዝብ ለማዳከም፤  የአማራ ህዝብ ዘሩን ለማጥፋት እቅዱን ለማሳካት በ1969 ዓ . ም. ድርጅቱን ከሚመሩ ጓደኞቹ በመተባበር ሁሉ 06 ሓለዋ ወያነ ከመሬት በታች 2 ሜትር ጉድጓድ ተቆፍሮ ከ150 እስከ 200 እስረኞች የሚይዝ ሆኖ መሰራት አለበት ብሎ ባቀረበው ሃሳብ ፤ሁሉ አመራር ተስማምተው ፤የftምበት ሓለዋ ወያነም ወደ ሱር ሽመልባ ሸራሮ ተዛውሮ ስለነበር ።

1  ሱር               2  ፃኢ             3 ገሃነብ ቃሌማ             4   ፍየል ውሃ

5 ወርዒ             6 ባኽላ              7   ዓዲ በቅሎ

በግደይ ዘራጽዮን ትእዛዝ ከመሬት በታች ተሰሩ በነብስ ወከፍ እስር ቤቶች በጣም ተንሽ ቀዳዳ መስኮት ያላት ሆነው በብዛት ተሰሩ ። እነዚህ እስር ቤቶች ለወልቃይት ጠገዴ አዋሳኝም ናቸው ፤ይህ የሆነበት ምክንያት የሰሜን ጎንደሩ አማራ በእነዚህ ማሰሪያ ቦታዎች እያጎሩ ለመግደል ለማጥፋት ለማሰቃየት አሰቃይቶ ለመግደል አስበው የሰሩት ነው ።

ግደይ ዘራጽዮን ወደ እነዚህ ሓለዋ ወያነ ከትግራይ ህብረተሰብ አነስተኛ ቁጥር ቢሆንም በአብዛኛው ግን አማራ ወንድ ሴት በአንድ ክፍል ጉድጓድ ከ200 መቶ በላይ እየታጨቀ በማሰር ሌላ በውጭ ጥልቀት ያለው ሰፊ ጉድጓድ ተቆፍሮ<‹ ዓየ >›ተብሎ የሚጠራ ዛፍ እየተቆረጠ በተቆፈረው ጉድጓድ አስገብተው በማቀጣጠል ጢሱ በትንሽዋ ቀዳዳ መስኮት እየገባ chamber smoke ሰዉ ሁሉ እየታፈነ አለቀ ፤የዓየ እንጨት እንደ ሌላው እንጨት አይነድም የሚተፋው ጢስ ብቻ ነው እንዳለም ረመጥ ነው የሚሆነው ። የዚሁ ፈላስፋና መሪም ግደይ ዘራጽዮን ነው ። ግደይ የአማራው ህዝብ የጨረሰው በዚሁ በጢስ አፍኖ ድምጽ የሌለው መሳሪያ የጨረሰው ።

አባይ ፀሃየ

ተውልዱ አኩሱም ነው ፤የቤተ ሰft ማንነት ብዙ አይታወቅም ፤አባይ ፀሃየ የማ.ገ.ብ.ት መስራች ነው ፤ በትግሉ መጀመሪያ በየካቲት ወር 1967 ዓ ም .ተ.ሓ.ህ.ት. ከመጀመሪያዎቹ አንዱ መሪ ነው ፤ቀጥሎም

 

በዲማ ጉባኤ የካቲት ወር 1968ዓ ም .ተመርጦ የፖሊት ቢሮ አባልም ነው ፤ቀጥሎም ተ.ሓ.ህ.ት. በየካቲት 5 ቀን 1971 ዓ. ም. በዓዲዳዕሮ ውስጥ ማይ አባይ ተብሎ በሚታወቀው ቦታ በተካሄደው 1ኛ ድርጅታዊ ጉባኤሲካሄድ ተመርጦ የህ.ወ.ሓ.ት. ፖሊት ቢሮ ሆኖ እስከ አሁን በማገልገል በከፍተኛ ሥልጣን ይገኛል ።

አባይ ጸሃየ ወላዋይ አቋም የሌለው መሪ ነው ፤እሥስት በደቂቃዎች ሃሳftን የሚለዋውጥ ተንሸራታች ፍጡር፤ በትግራይ ህዝብ ግፍ የፈፀመ ፤ስንቱ ንጹሃን ብስራት አማረ በሚያቀርብለት የውሸት ወንጀል ሪፖርት ብዙ የትግራይ አዛውንት ሴቶች ወጣቶች በመካከለኛ ዕድሜ የሚገኙ ሰዎች በተለያዩ ዘዴዎች ህዝብ የፈጀ ወንጀለኛ ከመሆኑ በላይ ፤በ1969 እስከ 1970 ዓ.ም አጋማሽ የቆየው የደርግ ቀይ ሽብር ተደናግጠው ወደ ተ.ሓ.ህ.ት. ሂወታቸውን ለማዳን የመጡ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በመውሰድ የደርግ ሰላዮች ናችሁ ተጋለጡ እያለ በመሪነት ስብሰባው እየመራ አስጨንቆ በመያዝ በማስጨነቅ በከባድ ፍርሃት የተነሳ የተሰብሳቢ ብዛት በማኸል ቁሞ በፍርሃት ያልሆነው ነኝ ሲል እየተያዘ 06 ሓለዋ ወያነ በማስገባት የስንቱን ሂወት ጠፋ ፤በዚሁም ላይ በሕንፍሽፍሽ ተበክለሃል ማን አስገባህ ምንስ ተነጋገራቹ የምታውቃቸው በዚሁ ሕንፍሽፍሽ የተበከሉ እነማን ናቸው ተናገር አውጣ እይተበለ ከደርግ ግድያ ያመለጠ የመሰለው ከድርግ የባሰ ተ.ሓ.ህ.ት. ገጠመው ስንትቱን ተገደለ ተረሸነ ናዚ ወንጀለኛው ወጣቱን የጨረሰው አባይ ጸሃየ ነው። ይህ በዚሁ እንዳለ በዚሁ ወቅት የተ.ሓ.ህ.ት. አመራር የፈጸመው ወንጀል ታሪክ ይቅር የማይለው ከወቅቱ ሊቀ መንበር አረጋዊ በርሄ፤ም/ሊቀመንበሩ ግደይ ዘርአጽዮን ስብሃት ነጋ ፤መለስ ዜናዊ ሥዩም መስፍን  በመተባበር   በፍርሃት ሸሽተው የመጡ በእድሜ ህፃናት ከ12 ዓመት እስከ 14 ዕድሜ የነበራቸው ህፃናት የበረሃው ኑሮ ከበዳቸው ርሃft ብርዱ በተለይ በወባ በሽታ ክፉኛ ስለተጠቁ የእናት አባት እህት ወንድም ናፍቆት በላዩ ተጨምሮ ለኧእምሮ ጭንቀት ስለዳረጋቸው ጥቂትም ታመው ሲተኙ እዛው ሞተው የቀሩ ፤ቀሪዎቹም በዛት ቁጥር ያላቸው ወደ ቤትየ ሊሂድ ቤተሰቦቼን እናቴ ናፈቁ ፤እያሉ ቀኑን ሙሉ ሲያለቅሱ በዚሁም ችግሩን ለመሸከም የማይ ችሉ ህፃናት ፤ከላይ የተጠቅሱ መሪዎች ለነዚህ አቅመ አዳም ያልደረሱ ደቂ እነይ >›የናቴ ልጆች >»በለው ስም በመስጠት፤ ሁሉ ተረሽነው እንዲገደሉ ውሳኔ በምስጠት በአባይ ጸሃየ እርምጃው እንዲፈጸም ተወስኖ እነዚህን አሰባስቦ ወደ ተለያዩ ሓለዋ ወያነ በብስራት አማረ እንዲከፋፈሉም ተወስኖ ገዳይ አስገዳዩ ብስራት አማረ ከፖሊት ቢሮው የተላለፈው ትእዛዝ በቶሎ ተግባራዊ እንዲሆን ተነገረው ። በዚህ ትእዛዝ መሰረት ብስራት አማረ ፤

1  ፃኢ ሓለዋ ወያነ   በስብሃት ነጋ መሪነት   ዋና ገዳዮች ሙሉጌታ አለምሰገድ ፤ወዲ ሻምበል( ዘአማኑኤል ለገሰ  ዘራይ ይህደጎ

2 ዓዲ በቅሎ 06 በአባይ ጸሃየ መሪነት አለምሰገድ ኢንቺ ተስፋየ ጡሩራ አበበ ዘሚካኤል

3 ዓዲ ጨጓር 06 በመለስ ዜናዊ መሪነት ብስራት አማረ ድልዊ ( ገድለዉታል በሂወት የለም አሰፋ ጉሬዛ ይህም ገድለዉታል በሂወት የለም

4 ሱር 06   በግደይ ዘራጽዮን መሪነት አበበ ት/ሃይማኖት ጀቤ፤ ዓወተ ተስፋይ

5 ባኽላ   06 በአረጋዊ በርሄ መሪነት ሙሉጌታ ፀጋይ፤ መኮነን ገብረማሪያም ( ወዲ ኾምበል )

6 በለሳ ማይሓማቶ 06 አዋአሎም ወልዱ ሓሰንሹፋ ተስፋየ አፈርሰው አረፋይኔ ጡሩራ

በእነዚህ የግድያ ቦታዎች ሌሎች ካላሽን ኮፍ የታጠቁ ገዳዮች በየቦታው የተመደft አሉ ፤ይህም የብስራት አማረ ሃላፊነት ነው ።የሁሉ አሰቃቂ ተግባር የደረሰው በአባይ ፀሃየ ምክንያት ነው ።ህጻናትም በስድስቱ ሓለዋ ወይነ ተረሽነው ተገደሉ

ይህ በህፃናቱ ለአቀመ አዳም ያልደርሱ የተፈጸመው ግድያ ከመቅጽበት በድርጅቱ በስፋት ተሰራጨ ፤ታጋዩም አሳዘነው አስቆጣው ከታጋዩም አልፎ በገጠሩም ወሬው ተሰራጨ ፤ቀስበቀስም በትግራይ አውራጃዎች ወረዳዎችም ወሬው ተስራጨ ፤የትግራይ ህዝብ በተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. ፋሽሽታዊ ተግባር ደም አለቀሰ ፤ በደርግ ስርአት ቁጠጠር በመሆኑ ያለው አማራጭ ቤቱ ዝግቶ ማልቀስ ብቻ ነው ።ህ.ወ.ሓ.ት. ተወገዘ በየከተማው ወረዳ የነበርው ህዋሳት ተበታትነው ወደቁ የከተማው ግንኝነቱም ፈረሰ ፤በከተማው አለኝ የሚለው አባል ሙሉ

 

በሙሉ አጣ ።ደርግ በዙ ደጋፊ አግኝቶ ነበር ፤ግን አያውቅበትም ፤ተመልሶ ያፈርሰዋል ወያኒም ይህች ይፈልጋል

የእነዚህ ህጻናት ግድያ በድርጅቱ ትልቅ ቀውስ እየፈጠረ ሲመጣ መሪዎቹም ለስጋት ስለጣላቸው ፤የፈጠሩት ዘዴ ስድስቱ አመራሮች 1አረጋዊ በርሄ  2 ግደይ ዘራጽዮን 3 ስብሃት ነጋ 4 አባይ ጸሃየ 5መለስ ዜናዊ 6 ሥዩም መስፍን በሱዳን ለሚገኙ አባላት ፤ተበታትነው በታጋይም በህዝብም ፊት እየቀረft ፤እርምጃው ወስደናል ነገር ግን ለድርጅቱ ህልውና ስንል ነው ፤እነዚህ ከለቀቅናቸው እንደገና ደርግን እየመሩ ሊያስመቱን ስለሚችሉ ለህ.ወ.ሓ.ት. ህልውና ስንል እንዲ ረሸኑ አድርገናል ፤እያሉ ሲማፀኑ በተለ በህዝብ በኩል ተቀባይነት አልነበርውም ፤የትግራይ ህዝብም ድሮውም እውቅና ሰጥቶ ስላልተቀበላቸው የህዝብ ነቀርሳ ፀረ ኢትዮጵያ መሆናቸው በሚገባ ስለሚያውቃቸው ወግዘቱም ቀጠለበት  ።

አባይ ጸሃየ ፕሮግራሙ በአረጋዊ በርሄ ሲዘጋጅም የድርሻው አስተዋጻኦ ሲወጣ የምጣ ነው ፤በዲማ ኮንፈረንስ በተደረገው ሰብሰባ የነበረው ታጋይ ሲቃወመው ፤ታጋዩን በማስፈራራት ውደዱ ጥሉ ይህ ፕሮግራም በዙ ወራት የጨረሰብን ፤ብናንተ ጭቅጭቅ ንትርክ አንዲት ፊደልም አትሰረዝም ፤የትግል ፖሊሳችን መመርያችን ነው ።

ስለ ወልቃይት ጸገዴ ስለ አለውሃ ምላሽም ያነሱ ጥቂት ታጋዮች አሉ ፤እንደ ወራሪነትም የተመለከቱትም ፤አሉ ተ.ሓ.ህ.ት. ወራሪ አይደለም ፤የሚሰጠን ጥቅም ብዙ ስለሆነ ነው ፤ወደ ሱዳን መውጫ ለም መሬት በመሆኑ ፤ የሚመሰረተ የትግራይ መንገሥት ፤እነዚህ ቦታዎች ካልተጨመሩ ሙሉ መንግሥት አይሆንም ስለዚህ ተነጋግረን አምነንበት የተዘጋጀ ነው ።አማራው መሬትየ ተቀማሁ ብሎ ከመጣ ድርብ ድርብርብ ጥቃቱ ተቀብሎ እንደ ጨው ይሟሟል ፤አማራ ማለት ክፉ ጠላት ነው ፤ነፃነትዋ ጠብቃ ለብዙ ዘመናት የቆየችው ትግራይ በምኒሊክ የሚመራው የአማራ መንግሥት አፄ ዮሓንስ ከሞቱ በኋላ በጉልበት ትግራይን ቅኝ ግዛታቸው በማድረግ ሆን ብለው በአማራው ሸዋዊ ዘዴያቸው የትግራይ ህዝብ ሙሉ ነፃነቱ ተገፎ ፤ለልመና ለስደት ለችግር ለበሽታ ተዳርጎ ቤቱ ፈርሶ እየተንከራተተ ያለ በዚሁ ጨቋኝ አማራ ነው ።በተ.ሓ.ህ.ት.የሚመራው የብረት ትግል አማራውን ዘሩን እንዳልነበር አድርገን ፤በአማራው መቃብር የትግራይ ዲሞክራቲክ መንግሥት በትግራይ ይመሰረታል ። ይህን በተመለከተ የተዘጋጀ ፅሁፍ ካስደመጠ ፤ከአጭር ቀናትም በወይን መፅሄት ለታጋዩ ተዘረጋ ።

ሥዩም መስፍን

ይህ ሰው ትውልዱ ኤርትራ ክ/ሃገር ዓዲ ቀይሕ ነው ወላጅ አባቱም የጣልያን ባንዳ እንደነበሩ ይታወቃል ፤ ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ነፃነትዋ እንደተቀዳጀች በመንግሥት ስራ ተቀጥረው ዓዲ ግራት ውስጥ ለብዙ ዓመታት ሰርተዋል ። ፤ሥዩም መስፈን ከዚሁ ተነስቶ የዓዲ ግራት ልጅ ነኝ የሚለው ።ግን አይደለም ።

ሥዩም መስፍን የህ.ወ.ሓ.ት. መስራችም ነው ፤ማ.ገ.ብ.ት. ሲመሰረት ከሰባቱ መስራቶች አንዱ ነው ፤በዛን ጊዜ ኢርትራ በጥር ወር 1967 ዓ.ም. ኢርትራ ሳሕል ወርደው የአንድ ወር ወታደራዊ ሥልጠና በሻዕብያ የተሰጣቸው አመራሮች 1 አረጋዊ በርሄ 2 ሥዩም መስፍን 3 አባይ ጸሃየ 4 ግደይ ዘራጽዮን 5 ሃይሉ መንገሻ 6 አስፍህ ሓጎስ 7 አጋዚ ገሰሰ ናቸው ። ሌሎች የማ.ገ.ብ.ት. መስራች ያልሆንትም እዛው ሳሕል ተገናኝተው የተቀላቀልዋቸው 1 አስገድ ገብረሥላሴ                         2 ካሕሳይ በርሄ ( ዶ/ር ግንፅል ) 3                                     ታከለ ወልደሚካኤል እነዚህም ተቀላቅለው በየካቲት ወር 1967 ዓ ም . ደደቢት በረሃ ወረዱ ፤መሪያቸው አረጋዊ ነው ።

ሥዩም መስፍን በተ.ሓ.ህ.ት. ፕሮግራም ዝግጅት ተሳታፊም ነበር ፤ጣልያንን የተዋጉ የትግራይ አርበኞች በጣም ያወግዛል ፤ይጠላል ።

ሥዩም ውሸታም ነው የተናገረው ይክዳል ቂመኛ ነው ለጠላው ታጋይ ሌሊት አያሳድረውም መግደል ነው ፤ ከምን እንደተነሳ ባይታወቅም ክፉ ቀናተኛ ነው ፤ ሥዩም አመንዝራ ሸርሙጣም ነው ገና በትግሉ መጀመሪያ በተደጋጋሚ እጅ ከፍንጅ የባላገር ሴቶች እያስገደደ ሲደፍር እየተያዘ የደረሰበት ነገር የለም ፤ሌላው ተራ ታጋይ ግን በጥይት ተደብድቦ ይገደላል ።

 

ሥዩም መስፍን ብዙ የሰው ሂወት ያጠፋ የገደለ አረሜነ ጨካኝ ነው ፤በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የፈጸመው የግድያ ወንጀል ዘግናኝ ቢሆንም ፤ይህስ ይቀር ተብሎ ሊታለፍ አይቻልም ፤በ1972 ዓ ም ሥዩምና አርከበ ዕቁባይ ፤ሥዩምና አረጋዊ በርሄ ፤ሥዩምና ግደይ ዘራጽዮን ፤ሥዩምና ሳሞራ የኑስ በተለያዩ ቀናቶች በተገናኙ ህፃን ሴት ወንድ ሽማግሌ ሳይሉ ቤት ውስጥ በማስገባት ሰዉ ወደ ኋላ ዘግተው እሳት እየለቀቁ ቤቱን በማቃጠል ህዝብ ፈጅተዋል ።

ሥዩም ሱዳን ውስጥ መሽጎ ፀረ ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. ናቸው የሚላቸው በሱዳን ውስጥ ሸቅለው ሂወታቸውን የሚገፉ ንፁሃን የትግራይ ሰዎች በህ.ወ.ሓ.ት. አባላት በለሊት እያስገደለ የስንቱን ሂወት በማያውቁት ሃገር ያጠፋ ወንጀለኛ ነው ።

ሥዩም በሱዳን ውስጥ የሚኖሩ የትግራይ ሴቶች በተለያዩ ስራ ተሰማርተው ያፈሩት ሃብት ለመዝረፍ ከሌሎቹ የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች በመነጋገር ይሁንታ ካገኘ በኋላ እዛው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ስብሰባ በመጥራት ራሱ በሚመራው ስብሰባ ያፈራችሁት ሃብት ንብረት እንዳይጠፋ ወርቃችሁ ገንዘባቹህ ለኛ አስረክftን በጥንቃቄ በአደራ ስም እናስቀምጥላቹህ ፤በምትፈልጉት ጊዜም ውሰዱ ፤ እያለ አስመሳይ በሆነ የማጭበርበሪያ ዘዴ ተጠቅሞ እህቶች ወንድሞች እውነት ስለመሰላቸው ፤ከባንክ ሳይቀር ያስቀመጡት ሃብታቸው አስወጥተው ለሥዩም መስፍን የህ.ወ.ሓ.ቱ መሪ አስረክበው ፤ሙልጭ አድርጎ ከሰበሰበ ወደ በረሃ በመለክ ፤የሚላከው ሃብት ስብሃት ነጋ እየተቀበለ ፤ስብሃትም በበኩሉ ወርቁ ከገጠር ከተማ እየተመለለሱ የሚነግዱ ነጋዴዎች በሚስጢር እየተገናኘ በመስጠት ወርቁ መቀሌ ሽሬ ወ.ዘ.ተ. እየተቸበቸበ የሱዳን ሴቶች ቀልጠው ቀሩ ።

ስብሃት ነጋ እና መለስ ዜናዊ እንዴት ለዚሁ ሥልጣን በቁ // ከትግሉ መነሻ ጀምሮ እስከ 1971 ዓ.ም .ሁለቱ ሰዎች በጊዜው በነበረ ታጋይ የተወገዙና የሚጠሉ እነዚሁ ናቸው

፤የሚስሩት ስራ ሁሉ ከአራጋዊ በርሄ በስተጀርባ ተጠልለው ነው ፤ታጋዩ አያምኑቱም ፤ስብሃትና መለስ ግን

ባገኙት መድረክ ታጋዩን መደፍጠጥ ነው ፤ስለ መለስ ዜናዊ ተደጋግሞ የቀረበ አብዮቱታ በአረጋዊ በርሄ ውድቅ እየተደረገ ፤አቤቱታ ያሰሙም የሥልጣን ሠኞች እይተባሉ ተረሽነዋል ።በስብሃትም እንደዚሁ ፤እነዚህ ሁለቱ ታጋዮች በፀረ ኢትዮጵያ አንድነት በፀረ ህዝብ አቋማቸው ግልጽ የማያጠራጥር ሆኖ እየታየ በወቅቱ በነበሩ አመራር እንደ ብልህ አዋቂዎች ለትግሉ አመራርነት ብቃት እንዳላቸው አድርገው በመስበክ ሁሉም ነገር ከነሱ ተማክረው ሲሰሩ የነበረው ታጋይ አጥብቆ ይከታተለው ስለነበር ፤ተወደደም ተጠላ ለሃላፊነት እንደሚያበቁዋቸው ለሁሉ ታጋይ ግልጽ ነበር ፤መክንያቱም አመራሩ የሚያቀርበው ይሾማል ለሚጠላው ይገድላል ፤እድሜ ለአረጋዊ በርሄ ተ.ሓ.ህ.ት.—ህ.ወ.ሓ.ት. ዘረኝነት ሽብርተኝነት ዘረኝነት ሲባልም የክልሉ ሰዎች በአብሮ አድግነት የትምህርት ቤት ጓደኝነት ስር በሰደደ መልኩ የተፈጠረ ድርጅት ነው ።በዚሁ መሰረት በዲማ ኮንፈረንስ በየካቲት ወር 1968 ዓ ም .ሲካሄድ የነበረው እቅድ ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ወደ ማእከላይ ኮሚቴው ለማምጣ ሲሆን በተካሄደው ጉባኤ ስብሃት ነጋ በዙ ዲስኩር ተነግሮለት አብዛኛው ታጋይ በግደይ ዘራጽዮን የተነገረው ውሸት መሆኑ ስለሚያውቅ አልተቀበለውም ነገር ግን ምርጫው ተካሂዶ በማጭበርበር ስብሃት በምርጫ አልፈዋል ብለው አጸደቁለት የስብሰባው መሪ አረጋዊ በርሄ ። በመለስ ዘናዊም በአረጋዊ በርሄ የተነገረው ዲስኩር መለስን ሰውነቱ ሁሉ በቅቤ ቀብቶ ሊቅ የተዋጣለት ታጋይ አድርጎ ሞናሊዛ አስመስሎ አቀረበው ይህ ሁሉግን እልም ያለ ውሸት ነበር ለምርጫም ቀርቦ ወደቀ ።አረጋዊ በርሄ ግደይ ዘራጽዮን አባይ ጸሃይ ሥዩም መስፍን መለስ ዜናዊ በመውደቁ ተናደው አቦራ አስነሱ ፤ላንቃቸው ተላልጦ ቀረ ያመጡት ለውጥ የለም ።በዚሁ መሰረት የተመረጡ;

1 አረጋዊ በርሄ የድርጅቱ ሊቀ መንበርና ወታደራዊ አዛዥ።

2 ግደይ ዘራጽዮን   የድርጅቱ ም/ሊቀመንበርና ዋና አስተዳዳሪ ።

3 ስብሃት ነጋ          የአረጋዊ በርሄ ረዳት ።

4 አባይ ጸሃየ           የፖለቲካ ሃላፊ ።

 

5 ሥዩም መስፍን      የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ።

6 አጋአዚ ገሰሰ          የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ

7 ሙሴ ተኽለ            በወታደራዊ ተብባሪነት ።

መለስን አሸንፎ የተመረጠው አጋአዚ ገሰሰ ነበር ፤አጋአዚ ደግሞ የማ.ገ.ብ.ት መስራች ነው ፤ነገር ግን የውቅሮ ሁለት አውላዕሎ ሰው በመሆኑ ፤ይህ የማ.ገ.ብ.ት. መስራች አግልለው መለስን የመተካት የአረጋዊ በርሄ ፕላን ታጋዩ ውድቅ አደረገለት ።ሙሴ ተኽለም በታጋዩ ሃይልና ብርታት ነው የተመረጠ በእነ ግደይ ዘራጽዮን የተጠላ ሰው ነበር ።የመለስ ዜናዊ አለመመረጥ ለአረጋዊ በርሄ እረፍት አልሰጠዉም አጋአዚ ገሰሰ እና ሙሴ ተኽለ በድርጅቱ አመራር በዘዴ አስገደላቸው ፤በ1968 ዓ ም መጨረሻ አመራሩ 5  ( አምስት ) ብቻ ስለቀሩ ለሥራችንም እንቅፋት ስለሆነብን በሚል የምክንያት ዘዴ ፤ 1 መለስ ዜናዊ 2 ስየ አብርሃ      3 አዋአሎም ወልዱ                                                                                       4 አጽብሃ ዳኘው ( ሸዊት ) መስከረም ወር መጀመሪያ በተለዋጭ ማ/ኮሚቴ ለከፍተኛ ሃላፊነት በቁ ፤ መለስም የፖለቲካ ክፍል ምክትል ዋና ሃላፊ በቃ ፤አረጋዊ በርሄም የሚፈልገው ሰመረለት ።

ስለዚህ ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ለዚ የሥልጣን ሃላፊነት ያበቃቸው ያደረሳቸው አረጋዊ በርሄ ነው ። ማንነታቸው የሚታወቁና እየታወቁ የመጡ ስብሃትና መለስ ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፤ ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ድብቅ ሳይሆን በግልጽ እየተንቀአቀሱ እሱም ራሱ እየተንቀሳቀሰ ሃገርና ህዝብ እዲያጠፉ ተንከባክft በመያዝ እዚህ ደረጃ ያደረሳቸው በዋናነት ተጠያቂው ሃላፊነቱን የሚሸከመው አረጋዊ ብርሄ ነው ።

ይህ ብቻ አይደለም  1ኛ ፀረ አማራ  የሆኑ ንጥር ያለ አቋም ያላቸው ።

2ኛ ፀረ ኢትዮጵያ ሏላዊነት ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፈልፍሎ ብቁ ናቸው የሚላቸው

እየመለመለ በሚያስተማምን ደረጃ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ያጠፉሉ ብሎ ተስፋ የጣለባቸው እንደ ሓረግ እየመዘዘ ለሥልጣን ያበቃቸውም ።  1ኛ ስየ አብርሃ  2ኛ ገብሩ አስራት  3ኛ  አዋዓሎም ወልዱ         4ኛው መለስ ዜናዊን ጨምሮ ወደ ሥራ አስፈጻሚ ሃላፊነት አወጣቸው ፤ ከእነዚሁ ፀረ ህዝብ ባለሥልጣናት ስየ አብርሃ የተናገረው ወልጅ አባቴ ቀኛዝማች አብርሃ በአማሮች ስለተገድሉ እኔም በአማራው በቀሌን አወጣለሁ በሎ የተናገረ ሰው ነው ፤የተናገረውም በአማራ ላይ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመ ነው ፤።በዚሁ ተመርጠው የመጡ ፖሊት ቢሮ ( ሥራ አስፈጻሚ ) ይቀርባል ። ወደ ማ/ኮሚቴ ሥልጣን የሚደርሱ ከላይ የተጠቀሱ ሁለት መስፈርቶች የሚያሟሉ መሆናቸው አስቀድሞ የተጠና የተረጋገጠ በዚሁም ያሳዩት ተግባር ተንተርሶ ለማእከላይ ኮሚቴ ምርጫ የሚቀርበው ።

ከህ.ወ.ሓ.ት. በሥልጣን ሽኩቻ የተባረሩት ፤የመጀመሪያዎቹ 1 አረጋዊ በርሄ 2 ግደይ ዘራጽዮን በሓምሌ ወር 1977 ዓ.ም .መጨረሻ በማ.ለ.ሊ.ት ጉባኤ  ነው ፤ በጉባኤው በግልፅ የተነገረው እነዚህ ሁለቱም የሰሙት ያዳመጡት ፤በህ.ወ.ሓ.ት ፖሊሲ በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም ቅንጣት የምታክል ልዩነት የለንም ፤ከሃላፊነት የሚነሱ ያሉበት ዋና ምክንያት በብቃት ማነስ ብቻ ነው ፤ሲባል ግደይና አረጋዊ የሰጡት መልስ ወይም የተክራከሩበት ነገር አልነበረም ፤ባይኖርም ግን በግልጽ የታየው የስልጣን ሽኩቻ መሆኑ ነበር ።አረጋዊ በርሄ ገና ከየካቲት ወር 1967 ዓ.ም. እስከ ተባረረባት ሳአት ሓምሌ ወር 1977 ዓ .ም .ድርጅቱን በዋና ህላፊነት የመራ ፤ካለሱ ፈቃድ ውጭ ምንም የማይተገበር ፈላጭ ቆራጭ በመሆን ህ.ወ.ሓ.ትን የመራ ድርጅቱን የመሰረተ ፕሮግራሙን አርቅቆ ወደ ተግባር የለወጠ አንጋፋው መሪ ነው ።

አረጋዊ በርሄ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው በድርጅቱ አመራር ውስጥ በዙ ንትርክ መቆሳሰል እንደነበረ ይናገራል ፤ይህ ግን ሃቅነት የሌለው ደረቅ ውሸት ነው ፤ከፕሮግራሙ ጀምሮ ሲናገር ፤ፕሮግራሙ ያረቀቁ ሰዎች ይህ ስህተት ነው አንሱት ብንላቸውም አልተቀበሉንም በማለት ደጋግሞ ሲናገር ፤ ሃፍረት ሊሰማው በተገባ ነበር

፤ግን ሰውየው ማወናበድና ማጭበርበር እንደ ስልት ስለሚጠቀምብት “” ደጋግሞ መዋሸት ወደ ሃቅ ይለወጣል–

-የሚባለውን ዘዴ እየተጠቀመ ህዝብ ያወናብዳል ፤ሰሜን ጎንደር ወልቃይት፤ ጠገዴ ፤ጠለምት ፤ቃፍታ ሁመራ ሰሜን ወሎ አለውሃ ምላሽ ወደ ትግራይ ያካተተው እኮ አረጋዊ ብርሄ ነው ።

 

የሰሜን ጎንደር ፤የሰሜን ወሎ የህዝft ማንነት አማራነቱን ኢትዮጵያዊነቱን እንዲነጠቅ ያደረገው እኮ አረጋዊ በርሄ ነው ።ዛሬ ህዝft እንደ ሁለተኛ ዜጋ ተቆጥሮ በህ.ወ.ሓ.ት እየተሰቃየ ያለው ለዚሁ ሁሉ ችግር ህዝft የተዳረገበት እኮ በአረጋዊ በርሄ ነው ። ፀረ አማራ አማራ ይትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ነው ፤ብሎ ፀረ አማራ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳው ያስፋፋው እኮ አረጋዊ በርሄና፤ ስብሃት ነጋ፤ ግደይ ዘራጽዮን መለስ ዜናዊ ፤አባይ ጸሃይ፤ሥዩም መስፍን እነዚህ ናቸው እኮ አማራውን ያጠፉት ፤ማንነቱን ነጥቀው ፤አማራው ክትውልድ ወደ ትውልድ እይተሸጋገር የመጣ የአማራ መሬት ነጥቀው የትግራይ መሪርት ነው ብለው ወደ ትግራይ ያካለሉት ።

ስለዚህ በህ.ወ.ሓ.ት. በአመራሩ ውስጥ በፖሊሲ፤ በአቋም፤ ልዩነት ተፈጥሮ አያውቅም ሁሉ አማራር በዚሁ ተስማምቶ ተደጋግፎ ነው የመጣው ልዩነት የላቸውም ፤ እንደውርስ ሆኖ በመምጣቱም አሁንም እየቀጠሉበት ነው ።በህ.ወ.ሓ.ት ውስጥ እኔ በልጥ እኔ በልጥ እኔ አውቃለሁ ሽርሙጥና ለብቻው ተደብቆ መብላት ተደብቆ መጠጥ መጠጣት ይታያል ፤በአጋጣሚ በዚሁ ሲነጫነጩ ትሰማለህ ፤በዚሁም ደግሞ የድርጅቱ ታጋይ በመሆንህ ታፍራለህ ፤አመራሩ ሁሉ ሂስና ገለሂስ ፈፅሞ አያደርግም የድርጅቱ ፖሊት ቢሮ አመራር ወሰን የሌለው መብት አለው ፤ስድና ልቅ ነው ። ከዚሁ ተነስተውም ብዙ ወንጀል ይፈጽማሉ የሚፈጽሙት ወንጀልም በጠራራ ፀሃይ ነው ።

በየትኛውም ጉባኤ ትልልቅ ስብሰባዎች ወይም በካድሬ ስብሰባዎች ሁሉ ፖሊት ቢሮ ስለሚገኙ በእንደዚሁ ስብሰባ የሚያሳልፉት ውሳኔ ሁሉም ተደጋግፈው ተስማምተው ያሳሉፉታ ቅንጣት የሉዩነት ፍንጭ የለም አይታይም ።ይህ እየሆነ እየታየ ንትርኩ መቆሳሰሉ በየት ይመጣል ፤ከዚሁ ተነስተን የአረጋዊ በርሄ እና ሌሎቹ ራሳቸው አግዝፈው ለማሳየት ወንጀላቸው ለመደበቅ የሚፈጥሩት የወደቀ ተረት ነው ።

ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ኢትዮጵያን ወሮ በቅኝ ግዛቱ መዳፍ እጅ ከወደቀች ከግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ. ም.እንኳን የሚመራው በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም ነው ፤አረጋዊ በርሄ ያዘጋጀው ፤ሌላው በረሃ በነበረበት የሚወጣ ፖሊሲ እቅድ በአረጋዊ የሚዘጋጁ ነው የነብረው አሁንም በድሮው ስታሊናው ፋሽዚም የሚጠቀሙት የአረጋዊ ብርሄ  እቅዶች  ናቸው  ።//////////////////////////////////////////////////////////////////////

ሕብረት ምን ማለት ነው ? ጥቅሙስ ?

ሕብረት ማለት ሰፊ አመለካከት ያለው ሃገራዊ አድማስ ነው ። ሕብረት በጥቂት ሰዎች ስብስብ የሚጀምር ሆኖ ግን ደግሞ በፍጥነት እያደገ የሚሄድ ነው ፤ሕብረት ወንዝና ተራራ፤ ቋንቋና ሃይማኖት አይደርተውም ፤ሕብረት ጠባብ ብሔርተኝነት ወገናዊነት አይቀበልም፤ ግft ኢትዮጵያዊነት ነው ።ሕብረት ከጥቂት ስብስብ ወደ ብዙሃን ስብስብ ፤ከብዙሃን ስብስብ ወደ አንድነት ከአንድነት ወደ ኢትዮጵያዊነት የሚያሸጋግር ሰፊ ጠንካራ ድልድይ ነው ።በምሳሌነት ለመጥቀስም  1ኛ ልሳነ ግፉአን             2ኛ  ጎንደር ሕብረት     3ኛ  ጎጃም ሕብረት                                                            እንደ ምሳሌነት ብንወስድ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ኢትዮጵያዊነት ማእከል ያደረገ የግባቸው እስትራተጂ ኢትዮጵያዊነት ነው ፡የሚመሩት ህዝባዊ እንቅስቃሴ ለጎንደር ወይም ለጎጃም ህዝብ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን አድማሱ በማስፋት ሞላው ኢትዮጵያ የሚሸፍን ነው ።ይህ እንቅስቃሴ በትኩረት ስንመለከተው ከዘር ከቋንቋ ከሃይማኖት የፀዳ ነው ፤ ዋናው እስትራተጅው ፀረ ክልል ሲሆን                ይደመስሰዋ መሰረቱ ያጠፈዋል ፤ በእነዚህ ሕብረቶች ቦታ የለውም ፤ያወግዙታል አይቀበሉትም ፤ሌለው ትልቁ ራኢያቸው በሁለገብ ትግል ያምናሉ ይቀበላሉ ፤ይተባበራሉ ፤ይህ ደግሞ ኢትዮጵያዊ አመለካከታቸው በመስፋቱ በሃገር ውስጥም በውጭም የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የማሰባሰብ ብቃታቸው ከዳር እስከ ዳር ሊያሰባስበው ይችላል ።ጠባብ ብሔርተኝነት በጎሳ መሰባሰብ ለጎሳህ መቆርቆር እነዚህ አደገኛ ፀረ ህዝብ ዝንባሌዎች በጣጥሶ የሚጥላቸው ይህ የአንድነት ሕብረት ነው ።

ኢትዮጵያና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ //

ኢትዮጵያ እና የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ድርጅት( ህ.ወ.ሓ.ት.) የሚገናኙበት መንገድም ሆነ ዓላማ የላቸውም፤አይገናኙም ። ኢትዮጵያና ህ.ወ.ሓ.ት.ያላቸው ልዩነትም የመሬትና ሰማይ ርቀት ነው  ፤ የትግራይ

 

ህዝብ ነፃ አውጪ ድርጅት በፕሮግራሙ በአቋም ፖሊሲው ትግራይን ከኢትዮጵያ አስገንጥሎ የትግራይ ዲሞክያቲክ መንግሥት ለመመስረት ነው፤ወደ በረሃው ትግል የተሰማራው ።<<ፕሮግራሙ ይመልከቱ ።>>» ህ.ወ.ሓ.ት. በፀረ ኢትዮጵያ ሉአላዊነት በፀረ ኢትዮጵያ አንድነት የተሰለፈ ድርጅት ፤እንደመሆኑ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ሲታይ በእጅጉ ተቃራኒ ናቸው ፤የትግራይ ህዝብም ለህ.ወ.ሓ.ት. በእውቅና አልትቀበለውም ፤ በሃይሉ በጉልበቱ ብቻ ነው እንደ መዥገር በትግራይ ህዝብ ተለጥፎ የመጣው ፤ህ.ወ.ሓ.ትና የትግራይ ህዝብም በአንድ ዓይን የማይታዩ የተለያዩ ናቸው ፤ህ.ወ.ሓ.ት በጥቂት ማፍያዎች የተመሰረተ የተፈጠረ ፀረ ህዝብና ፀረ ሃገር ድርጅት ነው፤ጎጠኛ፡ዘረኛ በአንድ ክልል ስም የተነሳ የአፓርታይድ አካል ነው ።

በኢትዮጵያ ሉአሏዊ ግዛት የማያምን ፤የኢትዮጵያ ታሪክና ታሪካዊ አመጣጥ የካደ ፤የህዝብ ታሪክ የከዳ ፀረ ኢትዮጵያ ነው ፤ይህ ድርጅት በኢትዮጵያ ጠላቶች በነ ሱዳን ፤ግብጽ ፤ድጋፍና ሃይል የተመሰረተ ነው ፤በእነዚህና ሌሎች ድጋፍ ነው እዚህ ደረጃ የደረሰው ።ይህ ድርጅት ኢትዮጵያን ለማጥፋትና ለማዳከም ቆርጦ የተነሳ ከመሆኑ ባሻገር ፤በህዝብም ብዙ ችግር እያደረሰ የመጣ አሁንም እያደረሰ የሚገኝ ፀረ ኢትዮጵያ ነው ።

ጠባብ ብሔርተኛ ከመሆኑም የተነሳ በፕሮግራሙ ያስቀመጠው ኢላማ አድርጎ ያነጣጠረው          በፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ፤ በፀረ ኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛትና አንድነት ፤ ታሪካዊ ሃገራዊ እሴቶች ነው ።ከዚሁ በመነሳት ህ.ወ.ሓ.ት. ፀረ ኢትዮጵያ ወራሪ ሃይል ነው ።ይህ ድርጅት በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. ፤ኢትዮጵያን በመውረር በፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት ሃይሉን ተገን በማድረግ ኢትዮጵያና ህዝብዋ በቅኝ አገዛዝ ስርአቱ ተቆጣጠረ ።ይህ ቅኝ ገዢ ሃይል በኢትዮጵያ ውስጥ የዘረጋው ሕግ በበረሃ ውንብድና ጊዜ ሲጠቀመው የነበረው የህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም ኢትዮጵያን ለመበታተን ይጠቅመኛል ብሎ ስላመነ አንኳር የሕገ መንግሥቱ ምሶሶ በማድረግ አስቀምጦታል ።

የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ መሪዎች ነበርና አሁንም በሥልጣን ያሉት ሁሉ ተደምረው ህ.ወ.ሓ.ት. ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲን ለማስጨበጥ አምባገነኑ የደርግ ስርአት ለማስወገድ ፤ብሎ ከአምባገነኑ የደርግ ሠራዊት ትንቅንቅ የጀመረው ገና ከትግሉ መነሻ ጀምሮ ስንት መስዋእትነት እየከፈለ የመጣ ድርጅት ነው ፤ሲሉ ትንሽ ሃፍረት የማይሰማቸው ባንዳና የማፍያ ስብስቦች ፤በህዝብ የፈጸሙት አሁንም እየፈጸሙት የሚገኙት ወንጀል ለማድበስበስ የታሰበ የሌባ አይነ ደረቅ የገዳዮች ማደናገሪያ ነው ። ህ.ወ.ሓ.ት. ለኢትዮጵያ ህዝብና ሉአላዊነት ብለው የከፈሉት መስዋእትነት ፈፅሞ የለም መሪዎቹም አያስftትም ኢትዮጵያና ህዝብዋ በጠላት ከመፈረጅ በስተቀር የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያ ብለው መጥራት ስለሚቀፋቸው ለኢትዮጵያ ዓዲ ሓበሻ ( የአበሻ ሃገር ) ለህዝft ደግሞ (ሓበሻ ) በለው መጥራት የመርጣሉ ፤፤ወያኔ የኢትዮጵያ ግዛት እንኳን በቅጡ አያውቃቸውም ስልጣን እስከ ጨበጠ ድረስ ። ለመሆኑ ዲሞክራሲና ወያኔ፤ ኢትዮጵያና ወያኔ ፤የኢትዮጵያ ህዝብና ወያኔ ፤ ይገናኛሉ ? አይገናኙም ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ የሚባለው ድርጅት አያውቀውም ፤ ።ወያኔ ፀረ ዲሞክራሲ ነው ፤ወያኔ ፀረ ኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ነው ፤ወያኔ ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ነው ፤ወያኔ በዘር የተደራጀ ጎሳና ጎጥ ማእከል ያደረገ የአፓርታይድ ድርጅት ነው ፤የትግሉ አላማም ደደቢት በረሃ የገባበትም ትግራይ ነፃ ሃገር የነበረች በአማራው ( ኢትዮጵያ ) ነፃነትዋ ተገፋ ዛሬ የአማራው ቅኝ ግዛት ስለሆነች ፤ትግራይን ነፃ ለማውጣት ብሎም የትግራይ መንግሥት ለማቋቋም ነው ፤ስለዚህ ወያኔና ኢትዮጵያ አይገናኙም ።በዚሁ መሰረት ዛሬ ኢትዮጵያ ሃገራችን የወደቀችው ፤በክፉ ጠላቶችዋ ወያኔዎች ፤ቅኝ አገዛዝ ስርአት ወድቃለች ። ከጣልያን ቀጥሎ የመጣ ወራሪ ቅኝ ገዢ ህ.ወ.ሓ.ት. ነው።የደርግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ተፍረክርኮ ሲወድቅ ለወያኔም ምቹ አጋጣሚ ስለፈጠረለት በለሱን ቀንቶት ዘው ብሎ አዲስ አበባ ገባ ፤ኢትዮጵያና ህዝብዋ ተቆጣጠረ ፤ ይህ መንገዱም ለወያኔ ያመቻቹሁለቱ ሃያላን መንግሥታት አሜሪካና እንግሊዝ ናቸው ።

የወያኔ መሪዎች ነበርና አሁን ሥልጣን ላይ የሚገኙት ሁሉ ማለት ነው ፤የሚናገሩት ነገር ከተግባራቸው ጋር ይጋጫል ፤የሰው ልጅ ዘር ለማጥፋት የተሰማሩት ገና ከ1969 ዓ.ም. ጀምሮ ሲሆን የሰሜን ጎንደር ህዝብ መሬቱን ለመውረርና የትግራይ ግዛታቸው ለማስፋፋት በከፋ መልኩ ደግሞ ከ1972 ዓ ም በህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች በአረጋዊ በርሄና በቀሩት ፖሊት ቢሮ ሠራዊታቸው እየመሩ በህዝft ላይ የዘር ማጥፋት ከባድ ወንጀል እየፈፀሙ የመጡ እስከ አሁን ካለማቋረጥ በአማራው እየተፈጸመ ያለ የወንጀል ድርጊታቸው ፤በአኝዋክ ሕብረተሰብ የፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፤በኦሮሞው ህዝብ የፈጸሙት እየፈጸሙት ያሉት ገድያ ጭፍጨፋ

 

በእስር ቤት ምንም ባላጠፋ ኢትዮጵያዊ ዘጋ በቶርቸር በተለያዩ አፍኖ የማጥፋት ዘዴዎች ኦሮሞው አልቀዋል እያለቀም ነው ፤ከባድ የግፍ ወንጀል እየተፈጸመበት ነው ፤ኦሮሞው ዛሬ ከመሬቱ እየተፈናቀለ በገዛ ሃገሩ ኢትዮጵያ ልክ በአማራው የደረሰው ሃገር አልባ መሬት አልባ እጣ ደርሶት ከርታታ ዜጋ አድርገዉታ ወያኔዎች ፤ በዚሁ መልክ የሰሜን ወሎ ህዝብ መሬት በግፍ የተነጠቀው የማንነቱ መግለጫ የሆነው አለ ውሃ ምላሽ ወ.ዘ.ተ.ተነጥቆ ወደ ትግራይ ተጨምሮ መሬቱ ብቻ ሳይሆን ማንነቱም የተነጠቀ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ዛሬ መሬት አልባ አድርገዉታል ፤ ጋምቤላውም ይህ ችግር ደርሶት መሬቱ ተነጥቆ ለትግሬው ባለሃብት ታድሎ ዛሬ የጋምቤላ ህዝብ የወያኔ ባለሥልጣናት ህዝft እንደ አገዳ እያጨዱ በዘር ማጥፋት ተሰማርተው የጋምቤላ ህዝብ በሚፈጸምበት ግድያ አፍኖ ማጥፋት ፤ለመጥፎ ስደት ተዳርጎ በኬንያ ደftብ ሱዳን እየተሰቃየ ይገኛል ፤ በአፋሩም ይህ የስቆቃ ድርጊት እየተፈጸመበት ነው ፤መሬቱ ተነጥቆ የትግራይ ክልል ነው ተብሎ ከኖረበት ትውልድ ቀዩ ተፈናቅሎ የመሬቱ ባላባት የነበረው ዛሬ እየተንከራተተ ይግኛል ፤እነዚህን ጭብጥ ከያዝን ፤ወያኔ ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ፍትህ ብለን ስንቱን መስዋእትነት ከፍለናል የሚለው ፤ውሃ የማይቋጥር ቀዳዳ አሮጌ ጣሳ ንግግራቸው ምን ያህል አጭበርባሪዎች አስመሳይ ውሸታሞች መሆናቸው በዚሁ ማረጋገጡ በቂ ነው ። ስለሆነም ወያኔ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ለማጥፋት የመጣ የባእዳን ቅጥረኛ ወራሪ እንጂ ለኢትዮጵያ በሎ የምጣ አይደለም ።በሥልጣን ያለው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ቁንጮ የማፍያ ስርአት በጉልበቱ የመጣ ወራሪ ቀኝ ገዢ ከመሆኑም ባሻገር በሃገሪቱ ያስቀመጠው ሕገ መንግሥት በሎ ወያኔ የሚጠራው፤ ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት በ1928 ዓ. ም. ከጣልያን ሃገር ይዞት የመጣ ከወያኔ ተመሳሳይ ፖሊሲ ከፋፋይና በታኝ ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ አልቀበልም ብሎ ጣልያንን እንዳሳፈርው ፤የወያኔ ሕግ መንግሥትም ለኢትዮጵያ ህዝብ ሕገ መንግሥት ሊሆን አይችልም ፤ህዝብም አልተቀበለዉም ።

ለማጠቃለል …. ህ.ወ.ሓ.ት. ለኢትዮጵያ ብሎ የታገለለት ወቅትና ጊዜ ፈፅሞ የለም ፤በረሃ ወርዶ ለ17 ዓመታት የታገለው ትግራይን ለመገንጠል ብቻ ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ት. የሚከተለው ፕሮግራሙ ፤ፖሊሲው ራሱ ባዘጋጀው በስፋት የሚገልጸው በፀረ ኢትዮጵያ በፀረ ህዝብ አንድነት ከፋፋይ ጎጠኝነት ማእከል ያደረገ ፀረ ህዝብና ፀረ ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ት. ለራሱ የዲሞክራሲ ሕግጋት የማያውቅ ፀረ ዲሞክራሲ ድርጅታዊ ስርአት ፤ለሌላው ህብረተሰብ ዲሞክራሲ ያመጣል ብሎ ማመን የማይታሰብ ከመሆኑም በላይ ወያኔም ከተፈጥሮው ጀምሮ ፀረ ዲሞክራሲ ሆኖ ነው የተፈጠረው ።

ህ.ወ.ሓ.ት. ለኢትዮጵያ ብሎ የከፈለው መስዋእትነት በፍጹም የለም በአፈጣጠሩ ታሪክም ይህንኑ የማያሟላ ዘረኛ ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ት. በዘር ማጥፋት ወንጀል የተሰማራ ፤የለም ሰፊ መሬት ወራሪ ተስፋፊ ፤ለሚመሰርተው የትግራይ ግዛት የሰሜን ጎንደር ፤የሰሜን ወሎ ፤የአፋር ፤እጅግ ሰፋፊና ለም መሬቶች በጉልበቱ የነጠቀ ወደ ትግራይ ያካለለ ፀረ ኢትዮጵያ ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ት. ኢትዮጵያዊ ሊሆን የማይችልበት በዙ መስፈርቶች ማንሳት ይቻላል ፤ነገር ግን ባጭሩ ህ.ወ.ሓ.ት. ለኢትዮጵያ ሲል ታገልኩ የሚለው አስመሳይ የወሸት ማጭበርበሪያ ጋጋታው ኢትዮጵያን የሚመለከት እንኳን ያወጣው ፕሮግራም የለውም ፤ በምን መልኩ ነው ለኢትዮጵያ ታገልኩ የሚለው ፤ ይህ በትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት ህ.ወ.ሓ.ት. ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ፖሊሲው በፕሮግራሙ በማያሻማ መልኩ ገልፆታል፤ አስቀምጦታልም ራሱ በራሱ ፀረ ኢትዮጵያ ድርጅት ሆኖ መፈጠሩ በራሱ ፕሮግራም ( ፖሊሲ ) ፅሁፍ ይጋለጣል። ስለዚህ ወያኔ ለኢትዮጵያ ብሎ የከፈለው መስዋእትነት የለም ።፤ለኢትዮጵያ ብሎም የታገለለ ጊዜም የለም ። ፤የኢትዮጵያ ሃብት ንብረት ፤የህዝብ ሃብት ነብረት መዝረፍ ፤ታሪካዊ ቅርሶች ፤ታሪካዊ መዛግብት በመሸጥ በማቃጥጠል የተሰማራው ህ.ወ.ሓ.ት. ከ1969 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ዛሬ ፤በምን መልኩ ብሎ ለኢትዮጵያ መስዋእትነት ይከፍላል ፤ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ሲሰራው የነበረ በከፋ መልኩ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት.እየሰራው እይፈጸመው ይገኛል ፤ዘር ማጠፋት፤ ግድያ ፤ ዜጎች አፍኖ ማጥፋት ፤የህዝብ መብት

 

መንጠቅ ፤ማገድ የህዝብ ማንነት መንጠቅ ፤የኢትዮጵያ ግዛቶች ለባዕዳን መሽጥ በዘረኛውና ሽብርተኛው ፖሊሲው ህዝብ ማሰቃየት።ስለዚህ ወያኔ ፀረ ሃገርን ፀረህዝብ ፤ቀኝ ገዢ ስርአት ነው ።

 

ኢትዮጵያ ዛሬ

ኢትዮጵያ  በአሁኑ ጊዜ ህወሓትን እና እኩይ ሥራውን የማያውቅ ኢትዮጵያዊ አለ በሎ ለማመን ያስቸግራል። ህወሓት ሲፈጠር ኢትዮጵያን ለመበታተን፣ ሕዝቧን በዘርና በቋንቋ ለመበታተን የተፈጠረ የኢትዮጵያና የሕዝቧ ደመኛ ጠላት ነው። ዓላማው ኢትዮጵያን በታትኖ መሬቷን በመውረር ታላቋን የትግራይ ሪፓብሊክ መንግሥት ማቋቋም ነው። የድርጅቱ መሪዎች በኢትዮጵያ በህዝብዋ         መራር ጥላቻ ያላቸው ናቸው። ሊፍቁት ሊያስወግዱት የማይፈልጉት በፖሊሲና በአቋም መሰረት ያደረገ ። ለዚህ ትልቁ ማስረጃ በፕሮግራማቸው ላይ የተቀመጠው የፖሊሲ አቋማቸው ነው። ኢትዮጵያን የሚመሩበት ሕገ መንግሥትም ሌላው ማስረጃ ነው።

ህወሓት ገና በረሃ ሳይወርድ በፀረ-ኢትዮጵያ የውጭ ሃይሎቸ፣ ማለትም፣ ጣልያን፣ ሊቢያ፣ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ሲማሊያ፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ ሶሪያ ወዘተ በመጠኑም ቢሆን ድጋፍ እያገኘ የተፈጠረ ድርጀት ነው። አሁንም የእነሱ ድጋፍና ማበረታታት አልተለየውም። በአንጸሩ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃገራችን አትፈርሰም፣ አትበታተንም፣ ለወራሪ ባእድ አትሸጥም፣ አትለወጥም ብሎ በኢትዮጵያ አራቱም ማእዘን በተነሳው አመጽ የወያኔ እቅድ ግftን ሊመታ አልቻለም።ሱዳኖች ግን ወያኔ በሸጠላቸው ሰፊና ለም መሬት የኛ ነው ብለው በጎንደር ክ/ሃገር ህዝብ ላይ ከወያኔ ተባብረው በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጥቃትና ማፈናቀል እያደረሱበት ይገኛሉ ። መላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሃገሩ ዳር ድንበር በሱዳኖች ተደፍሮ ሲወረር ኢትዮጵያ በጠላት ተወረረች ነው ። የኢትዮጵያ ህዝብም ስሜቱ የሚነካ ሃገሩ ኢትዮጵያ በወያኔዎች ትብብር እየፈረሰች የግዛት ድንበርዋን ተደፍሮ ፤ህዝብዋም ለሶቆቃ ሲኦል የተዳረገበት ጊዜ ነው ።በሕብረት የምንነሳበት ጊዜና ሳአት አሁን ነው ።

እኔ ትግሉን የጀመርኩት ከማገብት ጀምሮ ሲሆን፣ በረሃ በወጣሁበትም ጊዜ የህወሓት አመረር በሙሉ የቅርብ ጓደኞቼ ናቸው ። ሆኖም ግን አንድም ቀን ስለ ኢትዮጵያ አንድነትም ሆነ ስለታሪኳ ጥሩ ሲናገሩ ስምቼ አላውቅም። ሕዝብ ስብሰበው የሚሰጡት ትምህርትና ቅስቀሳ ስለኢትዮጵያ ወራሪነት፣ ስለታሪኳ መጥፎነት፣ ስለአማራው ጠላትነት ብቻ ነው። ስለትግራይ ሲያወሩ፣ በአማራው መንግሥት ነፃነቷን ያጣች በማለት መርዛማ በሆነው በሬ ወለደ ተረታቸው ሊያሳምኑት ጥረዋል። ፍላጎታቸውን ለትግራይ ሕዝብ ቢለፍፉም የትግራይ ህዝብ አልተቀበላቸውም ለዚሁም ከባድ መስዋእትነቱ የከፈለው የትግራይ ህዝብ ነው ፤በወያኔዎቹ ተገደለ ሃብት ንብረቱ ተወረሰ ቤቱ ፈረሰ ልጆቹ በሃይል እየተገደዱ ታገሉ ተብለው በየ በረሃው ወድቀው ቀርተዋል ። ዛሬ ከድረጅቱ በሥልጣን ሽኩቻ የተገለሉት ህወሓቶች የሚነዙት በሬ ወለደ የትግራይ የቅኝ አገዛዝ በአማራው መንግሥት እጅ መውደቅ የሚለው፤ ከፕሮግራሙ መነሳት አለበት ብለን ወስነን ፤ያንሱት አያንሱት በፅሁፍ አላየሁም ፤ብሎ የሚናገረው አረጋዊ በርሄ ፤ ማን ነው የድርጅቱ የበላይ መሪ እሱ ራሱ ፤አንሺውስ ማን ነው ? እሱ ራሱ ፤ የድርጅቱ ሊቀ መንበር ራሱ፤ የድርጅቱ ወታደራዊ አዛዥ ፤ሙሉ በሙሉ ትእዛዝ ሰጪ ራሱ ፤ ድርጅቱን ከላይ እስከ ታች የሚቆጣጠረው ራሱ አረጋዊ በርሄ ፤ማረም ማንሳት የነበርው ራሱ አረጋዊ በርሄ ፤ መቆጣጠር ማረም ብቻ ሳይሆን ፕሮግራሙ በሙሉ ፀረ ኢትዮጵያ ፤ፕሮግራሙ በሙሉ ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ፀረ አንድነት በመሆኑ ተቃጥሎ፤ ሌላ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ለህዝብ ይፋ መደረግ መሆን ነበረበት ፤ይህ አልተደረገም ፤ ታርሞ ከሆነም ለህዝብም ሆነ ለታጋዩ በመጀመሪያ ራሱ የፈጠረው ድርጅት ከነሃገር አፍራሽ ፕሮግራሙ ራሱም ቆሞ ሂስና ግለሂ አድርጎ ራሱ ያዘጋጀው ፕሮግራም በፅሁፉ የያዘው ስህተት መሆኑ አምኖ ተቀብሎ የፕሮግራሙ ፀረ ኢትዮጵያ መሆኑ ተቀብሎ መዘጋት ፕሮግራሙም መቃጠል ሲገባው ፤በግሉም ሂሱን አውርዶ ነጻ በወጣ ነበር ይህ ሁሉ ሳያደርግ መዋሸትና መመጻደቅ ። አሁንም በሃላፊነት መጠየቁ አይቀርለትም

፤ለዚሁ ሁሉ በኢትዮጵያ እየደረሰ ያለው አረጋዊ በርሄ የፈጠረ መዘዝ ነው ። ። በማሌሊት ምስረታ ጉባኤ ወቅት መለስ ዜናዊ ስለትግራይ በጉባኤው የተናገረውን፣ ማለትም፣ ኢትዮጵያዊነት አንቀበልም ብንል  መብታችን

 

ነው ፤ስለ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉባኤ የሚነሳበት ምክንያት የለም ፤ጉባኤው የሚያቶኩረው ስለመጪው ትግራይ ዕድገት ብቻ ነው ። ያለውን ማስታወሱ በቂ ነው ። በጉባኤው የነበሩ አባላት የሚያስታውሱት ሃቅ ነው ።

ዛሬ ኢትዮጵያ በካባድ አደጋ ላይ የወደቀችው በወያኔ ምክንያት ነው። ቀደም ብሎ እንደተገለጸው ድርጅቱ የተፈጠረው ኢትዮጵያን ለመበታተን ነው። ፀረ-ኢትዮጵያ ሆኖ መንቀሳቀስ ከጀመረ 44 ዓመት በላይ አስቆጥሯል። ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ስር ካደረጉ ዳግሞ 26 ዓመት ሆኗል።

በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይህ ነው የማይባል መከራና ስቃይ ባማድረሳቸው ተጠያቂዎቹና ለፍርድ መቅረብ ያለባቸው የህወሓት አባላት እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል። እነዚህ

 

እነዚህ ክየካቲት ወር 1967 ዓ.ም. እስከ የካቲት ወር 1968ዓ.ም. ተ.ሓ.ህ.ት. እየመሩ የመጡ

1   አረጋዊ በርሄ      የተ...ሊቀ መንበርና ወታደራዊ አዛዥ    ፖሊት ቢሮ

ግደይ ዘራጽዮን   የተ.ሓ፣ህ፣ት፣ ም/ሊቀ መንበር                    ፖሊት ቢሮ

ስብሃት ነጋ        የአረጋዊ በርሄ ረዳት የሓለዋ ወያኔ ( 06 ) ሃላፊ   ፖሊት ቢሮ

ሥዩም መስፍን   የውጭ ጉዳይ ሃላፊ                          ፖሊት ቢሮ

አባይ ጸሃየ      የፖለቲካ ክፍል ሃላፊ                           ፖሊት ቢሮ

መለስ ዜናዊ   ይህ ሰው በፖሊት ቢሮው ደረጃ ባይካተትም በማ/ኮሚቴ ተለዋጭ ሆኖ በማንኛው ውሳኔና ስብሰባ ከላይ ከተጠቀ አምስቱ ተለይቶ አያውቀም ። እድሜ ለነብስ አባቱ አረጋዊ በርሄ ።

ከየካቲት ወር 1968 ዓ.ም  በዲማ ኮንፈረንስ ጉባኤ .ስብሃት ነጋ ተጨምሮ  አምስት ፖሊት ቢሮ ሆኑ ፤ ሊቀመንበሩ አረጋዊ በርሄ ሲሆን ም/ሊቀ መንበር ደግሞ ግደይ ዘራጽዮን ነበሩ ።

ሁለት ማእከላይ ኮሚቴዎች ከላይ በዝርዝር የሚታዩ አመራር 1 አጋአዚ ገሰሰ          በሙሴ ተክለ በእጅ አዙር ዘዴ አስገደልዋቸው ፤መክንያቱም ከላይ ከተጠቀሱ አመራር በሚሰሩት በሚፈጽሙት ፀረ ሃገርና ፀረ ህዝብ ተግባራቸው ስለማይስማሙ ።

በተ.ሓ.ህ.ት 1ኛው ጉባኤ የተካሄደው የካቲት 5 ቀን 1971 ዓ፣ም ፣ ሲሆን ለውጦች ተደረጉ ፤የድርጅቱ ስም ከተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ ( ተ.ሓ.ህ.ት. ) ወደ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት. )ተለወጠ ጉባኤው የተመራው በአረጋዊ በርሄም ነበር ።

በዚህ ጉባኤ የተመረጡ ፖሊት ቢሮ ፤

1ኛ  አረጋዊ በርሄ          ፖሊት ቢሮ          ወታደራዊ አዛዥና የድርጅቱ የበላይ ተቆጣጣሪ ፤

2ኛ ስብሃት ሀጋ         ፖሊት ቢሮ            የድርጅቱ ሊቀ መንበር ፤

3ኛ   ግደይ ዘራጽዮን     ፖሊት ቢሮ          የድርጅቱ ም/ሊቀ መንበር ፤

4ኛ   አባይ ፀሃየ          ፖሊት ቢሮ           የፖለቲካ ክፍል ሃላፊ ፤

 

5ኛው ሥዩም መስፍን    ፖሊት ቢሮ            የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ፤እነዚህ አምስቱ ድርጅቱ በሃላፊነት እንዲመሩ ተመረጡ ።በሊቀ መንበርነት የተመረጠው አረጋዊ በርሄ ነበር ፤ቀደም ብለው ከላይ የተጠቀሰው በአረጋዊ በርሄ ስብሃት መለስ በድብቅ በተስማሙበት ውዲት መሰረት ፤አረጋዊ ሊቀ መንበርነቱ ለስብሃት ነጋ ስጡት ብሎ አንገቴ ለካራ በማለቱ ፤ስብሃት ሊቀ መንበርነቱን ተረከበ። ሆነም በዚሁ የነበሩ ማ/ኮሚቴ ስብሃት ብቃትና ችሎት የለውም ድርጅቱ ለመምራት አይችልም በማለት ተከራክረው ነበር ፤የአረጋዊ ፍላጎት ለመሻር ግን ስለማይችሉ አረጋዊ ባለው ፀደቀ ።

ቀጥሎ የመጣው 2ኛ ጉባኤ ነው ፤ይህም ተከዜ ውስጥ ፀሊሞይ ተብላ በምትታወቀው ቦታ ተካሄደ ፤ይህም ግንቦት ወር 1975 ዓ .ም .ነበር ።በዚህ ጉባኤ የተመረጡ ፖሊት ቢሮ ። በተጨማሪም በዚሁ ጉባኤ አራት ፖሊት ቢሮ የጨመረ ጉባኤ ነው ።የጉባኤው ሊቀ መንበር አረጋዊ በርሄ ።ምርጫው በሚከተለው ተፈጸመ ፤

1ኛ አረጋዊ በርሄ          ፖሊት ቢሮ        ወታደራዊ አዛዥን የድርጅቱ ዋና የበላይ ሃላፊ  ፤

2ኛ ስብሃት ነጋ          ፖሊት ቢሮ         የድርጅቱ ሊቀ መንበር ፤

3ኛ ግደይ ዘራጽዮን    ፖሊት ቢሮ         የድርጅቱ ም/ሊቀ መንበር ፤

4ኛ አባይ ፀሃየ        ፖሊት ቢሮ        የፖለቲካ (ፕሮፓጋንዳ ) ክፍል ሃላፊ ፤

5ኛ ሥዩም መስፍን    ፖሊት ቢሮ         የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ፤

6ኛ መለስ ዜናዊ       ፖሊት ቢሮ         የማርክሲሲት ለኒነስት ፓርቲ አደራጅ ኮሚሽን

ዋና ሃላፊና የፕሮፓጋንዳ ምክትል ሃላፊ ።

 

 

 

 

 

 

ተደላደሉ ።

7ኛ ገብሩ አስራት        ፖሊት ቢሮ ፤

8ኛ አውዓሎም ወልዱ   ፖሊት ቢሮ ፤

9ኛ ስየ አብርሃ           ፖሊት ቢሮ         በወታደራዊ ክፍል ፤ እነዚህ ተመርጠው

 

 

ከዚሁ ቀጥሎ የመጣው ምርጫ የማ.ሌ.ሊ.ት ጉባኤ ነው ፤ይህም ከሓምሌ 1 ቀን እስከ ሓምሌ 30 ቀን 1977ዓ.ም.  የረጅም ቀናት ጉባኤ፤ ይህ አንድ ወር የፈጀ ጉባኤ ለህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች መንደላቀቅያና  ፈንጠዝያ ነበር የተዘጋጀው ፤በሌላ ደግሞ ትግራይ በክፉ ድርቅ ተመታ የትግራይ ህዝብ የሚላስ የሚቀመስ አጥቶ በዚሁ ክፉ ድርቅ በየበረሃው በየመንደዱ እየ ሞተ ቀባሪ ያጣበት ክፉ ጊዜ ነው የነበረው ፤የሚረዳው ያጣበት ክፉ የምፀት ዓመት የወረደበት ወቅት ;በትግራይ ህዝብ ስም ተለምኖ የመጣ እርዳት በመለስ ዜናዊ በስብሃት ነጋ ከግብረ አበሮቻቸው ጋር ተባብረው በችግር ከወደቀው ህዝብ አፍ ተነጥቆ ፤ህዝብ እንደቅጠል እየረፈ ሲሞት የሚጠጣው ውሃ ወንዞች ጅረቶች ደርቀው ያፈራቸው የቤት እንስሣት አልቀው ፤መሬት ለትግራይ ህዝብ ጨለማ የሲኦል ነበልባል በሆነችበት ወቅት የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ፤                                   ይህ ጉባኤ ከ35 000 000 ብር ሚልዮን በላይ                                 ( ከሰላሳ አምስት ሚልዮን በር ) በላይ ወጪ በማድረግ ፤የተንደላቀቀ በምግft በመጠጡ                    እፁብ ድንቅ ተብሎ የተነገረለት የፈንጠዝያ ጉባኤ አካሂደዋል ።ሙሉ በሙሉ ለትግራይ ህዝብ ተብሎ በዓለም ሕብረተሰብ የተለገሰው መጠነ ሰፊ እርዳታ ነጥቀው ፤ዘርፈው ፤ይህ ጉባኤ አካሄዱ ። የትግራይ ህዝብ በወያኔ እጅ መውደቁ ከእግዚአብሄርር የመጣ ቁጣ ነው ።ገና ትግሉ እንደጀመሩ በዚህ ህዝብ ግፍ የፈጸሙት ታሪክ ይቅር አይለዉም ፤ሓለዋ ወያኔው እያስገft ገድለዉታል አርደዉልም ፤በዚ ክፉ ድርቅ ጊዜም ቂማቸው ይዘው አጠፉት ፤ለህዝብ ተብሎ የመጣው እርዳታ እየሸጡ ወታደራዊ መሳሪያ በየአይነቱ ከሱዳን ግብፅ ፤ሊብያ ፤ኢራን ኢራቅ ወ.ዘ.ተ.ገዙበት ፤በመስረቱም ይህ ድርጅት ሲፈጠርም ፀረ ኢትዮጵያ ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ ፀረ ትግራይም ሽብርተኛ ድርጅት ሆኖ ነው የተፈጠረው ።

 

በዚሁየማ.ለ.ሊት ጉባኤ የተመረጡ መርዎች በሥራ አስፈፃሚነት የተመረጡት የሚከተሉት ናቸው ;

በዚሁ ጉባኤ የተወገዱት ባልታሰበ ሁኔታ በድንገት ዱብ እዳ የወረደባቸው አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘርአጽዮን ስብሃት ነጋ ተነስቶ ከአረጋዊና ግደይ የአቋም የፖሊሲ ልዩነት የለንም ፤ገንዘብ እንሰጣቸው አለን ቢፈልጉ በተራ ታጋይነት በድርጅቱ ታቅፈው ሊታገሉ ይችላሉ ካፈለጉ ደግሞ ወደፈለጉበት ሊሄዱ ይችላሉ ፤በማለት አረጋገጠላቸው ፤በመጨረሻ 1980 ዓ.ም. ለአረጋዊ በሄ $35 000 ሺህ ዶላር ( ሰላሳ አምስት ሺህ ዶላር ) ለግደይ ዘርአጽዮን $ 30000 ሺህ ዶላር ( ሰላሳ ሺህ ዶላር ) አሸክመው መጀመሪያ ግደይ እስከ ገዳሪፍ ሱዳን አጅበው አደረሱት ዘግየት ብሎም አረጋዊ በርሄን እስከ ገዳሪፍ ሱዳን ሸኙት ;የመጡ ሥራ አስፈፃሚዎች።

1ኛ  አባይ ፀሃየ              ፖሊት ቢሮ          የማ.ለ.ሊ.ት ሊቀ መንበር

2ኛ ስብሃት ነጋ            ፖሊት ቢሮ         የህ.ወ.ሓ.ት ሊቀ መንበር እና የማሕበር ኢኮኖሚ ሊቀ መንበር

3ኛ መለስ ዜናዊ           ፖሊት ቢሮ         የፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ የማለሊት ኮሚሽነር

4ኛ ሥዩም መስፍን        ፖሊት ቢሮ        የውጭ ጉዳይ ሃላፊ

5ኛ ስየ አብርሃ            ፖሊት ቢሮ         ሙሉ የህ.ወ.ሓ.ት. ወታደራዊ አዛዥ አረጋዊ በርሄን ተክቶ

6ኛ ተወልደ ው/ማርያም ፖሊት ቢሮ        የህዝብ ግኑኝነት/ክፍል / ሃላፊ

7ኛ ገብሩ አስራት          ፖሊት ቢሮ        የርጅን 1 ሃላፊ እና የማሕበር ኢኮኖሚ ም/ሊቀ መንበር

8ኛ አውዓሎም ወልዱ      ፖሊት ቢሮ        የርጅን 2 ሃላፊ

9ኛ ጻድቃን ግ/ተንሳይ     ፖሊት ቢሮ        የርጅን 3 ሃላፊ ቢሆን የሥራዊቱ ኮሚሣር ተወስኖ ቀረ

10ኛ  አረጋሽ አዳነ           ተለዋጭ ፖሊት ቢሮ     ምድብ የለም

11ኛ አርከበ ዕቁባይ           ተለዋጭ ፖሊት ቢሮ በወታደራዊ ጽ/ቤት ምድብ ።ከዚሁም በስየ አብርሃ ተባሮ

፤በማሕበር ኢኮኖሚ ለትንሽ ቀናት ቢሰራም ከገብሩ አስራት ስለማይግባft ተገሎ ቆየ ።በትንሹ ስለ አርከበ ( የቤቱ ስም ዮሃንስ ነው ) አርከበ የሰከነ አእምሮ የሌለው ግራ የተጋባ ፍጡር እንደ አርከበ የለም በቀን አምስት ከዛ በላይም ፕላን ይቀይሳል ያወጣል ፤አንዲትም ሳይሰራ ይመሽበታ ፤ነገም እንደዚሁ ዛሬ እስራዋለሁ ያለው ማታ ይጥለዋል ፤ቁርሱ ሲበላ እቅድ ያወጣል ፤የተለያዩ ወረቀቶች ከሚጠቀምበት ጠረጴዛ ይከምራል ይህን በጣሙ ይወደዋል ፤ግን አንዲት ስራ ሳያከናውን ይመሽበታ ፤አርከበ እቁባይ ማለት ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ማለት ነው ፤አርከበ ወደ መለስና ስብሃት ወሬ ማመላስ ማቀበል ይወዳል ትንሽ ወሬ ካገኘም እስዋን አግዝፎ መልክ ሰጥቶ የሚዋሽ ውሸታምም ነው ፤ አርከበ ራሰ ወዳድ በምግብ ሳይቀር ስሥታም ምርጥ መርጡ ለኔም ባይ ነው። ለዚሁ ሃላፊነት ያበቃው በችሎታው ሳይሆ በመንደር ልጅነት አረጋዊ በርሄ ነው ፤ግን በማ.ለ.ሊ.ት .ጉባኤ ከመለስና ስብሃት ወግኖ አረጋዊ በርሄን ሰደበው አበሻቀጠው ።

3ኛው ጉባኤ የተካሄደው በ1981 ዓ.ም. ሲሆን የሥራ አስፈጻሚ ሆነው የተመረጡ እነዚህ ከላይ ተጠቅሰው የሚታዩ ተመረጡ የታየው ለውጥ መለስ ዜናዊ የህ.ወ.ሓ.ት. ማ.ለ.ሊት ሊቀ መንበር ሆነ ፤ስየ አብራሃም የህ.ወ.ሓ.ት. ማ.ለ.ሊ.ት ምክትል ሊቀ መንበር ወታደራዊ አዛዥ ሆነው ተሾሙ ። በአራተኛ ጉባኤም እንዚህ ነው የትመርጡት ።በ1993 ዓ. ም. በተፈጠረው ህ.ወ.ሓ.ት. በሁለት መሰንጠቁ የተለያዩ ታጋዮች ወደ ፖሊት ቢሮ ደረጃ መጡ እነዚሁም የታወቁ ፀረ ኢትዮጵያ ሉአሏዊነት ፀረ ኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት በዘር ማጥፋት ወንጀል እጃቸው በደም የታጠft ህዝብ የፈጁ የሃር ሃብት ንብረት የዘረፉ ሽብርተኞች ናቸው ፤ከተባረሩት ምንም ለውጥ ይላቸውም ፤በመሰረቱ በህ.ወ.ሓ.ት. ለውጥ ይመጣል ብሎ የሚጠብቅ ካለ ሞኝነት የተጠናወተው ብቻ ነው ። ህ.ወ.ሓ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. ነው ።

 

ይህ ድርጅት ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜ ወቅት ድርጅቱን እየመሩ የመጡ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ መሪዎች ፤በኢትዮጵያና በህዝብዋ እጅግ ከፍተኛ ወንጀል እየፈፀሙ የመጡ መሆናቸው ሁሉ ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው ሃቀና ኡነታም ነው ።

1 የዘር ማጥፋት ወንጀል በአማራው ገና ከ1969 ዓ ም. በትንሹ የጀመሩት በ1972 ዓ ም .ታህሳስ ወር በዘግናኝ መልኩ በመቅጠል በሰሜን ጎንደር ወልቃይት ፤ጠገዴ ፤ጠለምት ወዘተ.የሰው ልጅ ዘር አጥፍተዋል ፤ሃብት ንብረቱም በህ.ወ.ሓ፣ት ውርስ እየተደረገ ዘርፈዋል የዚሁ ህዝብ ዘር ማጥፋት አሁንም ወያኔ አላቆመም ቀጥሎበታል ፤በአኝዋክ ህብረተሰብም በዚሁ ተመሳሳይ ዘሩ በማጥፋት ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ተሰማርቶ አኝዋኮች ዘራቸው ጠፍተዋል በጋምቤላ ፤በአፋር የዘር ማጥፋት ጥቃት ተፈጽመዋል ።

2 የኢትዮጵያ ሉአላዊነት የግዛት አንድነትዋ በህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ኢትዮጵያን ለመዳከም ለማጥፋት ይዘዉት በተነሱት አቋም ፕሮግራም መሰርት በማድረግ ፤ ሃገር አፍርሰዋል ኤርትራን አስገንጥለዋ ኢትዮጵያን ካለ ባህር በር በማድረግ ዛሬ ኢትዮጵያ ባህር በር አልባ ዝግ ሃገር ሆናለች ።

3 የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች በኢትዮጵያና በህዝብዋ ምንም እውቅና ተቀባይነት ሳኖራቸው ባንዳና የማፍያ ስብስብ የኢትዮጵያ ሉአላዊነት በመፃረር በ1974 ዓ.ም. በሱዳን መንግሥት ተነሺነት ኢትዮጵያ በ1902 ዓ.ም. በተቀመጠው የመሬት ካርታ አልቀበልም ብላ መሬታች በሃይል ስለ ነጠቀችን የናንተ እርዳታና ተብብር ስለምንፈልግ በማለት ለወያኔ መሪዎች ደብዳቤ በመጻፍ በረሃ ድረስ በመላክ ፤ደብዳቤው ለአረጋዊ በርሄ ደረሰው ፤አረጋዊ በርሄም የነበሩ አመራር ሰብስቦ  እነሱም  ፤1 ስብሃት ነጋ  2  ግደይ ዘራጽዮን 3  አባይ ጸሃየ  4 መለስ ዜናዊ 5 ሥዩም መስፍን ፤ ተሰብስበው የደብዳቤ ይዘት በመሪው አረጋዊ በርሄ ከተብራራ የወያኔ አመራር በእልልታና በደስታ ተቀብለው በሃገርና በህዝብ የማይታወቅ የባንዳ ስብስብ በ1975 ዓ. ም. የሱዳን መንግሥት የጠየቀው በተግባር እንደሚፈፅም ከላይ የተጠቀሱ አመራር ስድስቱ በፊርማቸው አረጋገጡ ። እነዚህ የትግራይ ነፃ አውጪ መሪዎች የአማራው ለምና ሰፊ መሬት ዛሬ የሱዳን መንግሥት የሱዳን መሬት ነው እያለ በአማራው ህዝብ እየተፈጸመ ያለው ችግርና መከራ በእነዚህ የወያኔ መሪዎች የተፈጸመ ወንጀል ነው ። ፤ የሱዳን መንግሥትም ለህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ሙሉ እውቅና በመስጠትና በሙሉ እውቅና ይቀበላል ፤ በተጨማሪም በአረብ ሃገሮች በግብፅ ፤በሊብያ ፤ኢራን ፤ኢራቅ ፤ሶሪያ ፤ሳውዲ አረቢያ ፤ወ.ዘ.ተ ተቀባይነትና እውቅና እንድታገኙ ሙሉ በሙሉ እናስፈጽማለን ፤ከዚሁ በተጨማሪ የሱዳን መንግሥት ሙሉ ድጋፉ ማለት በሱዳን ግዛት የህ.ወ.ሓ፣ት ቢሮ ይከፍታል ወጪው በሱዳን መንግሥት ይሸፈናል ፤ማንም የህ.ወ.ሓ ት. አባል በሱዳን በነፃ ይንቀሳቀሳል ፤ለታጋዮች በነጻ ሙሉ ህክምና ፤አስፈላጊው ወታደራዊ ቁሳቁስ በእኮኖሚ ሙሉ ድጋፍ ያደርጋል ፤የሚል ቃል የሱዳን መንግሥት በመግባት ፤ የወያኔ መሪዎችም ለጊዚያዊ ጥቅም ብለው ሃገር ሽጠዋል ።ይህም በዓለም አቀፍ ሕግ በጣም የተወገዘ ወንጀል ነው ።የኢትዮጵያ ሉአላዊነት በመፃረር ሕጋዊነት የሌላቸው ሕገ ወጥ የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት የአማራ መሬት ከጥንት ሲወርድ ሲዋረድ የአማራው ግዛትና መሬት ለሱዳን ለጥቅማቸው ሲሉ ሽጠዋል ።በሕግም ይጠየቃሉ ።የሱዳንም እየፈጸመችው ያለች ከሕገ ወጥ የወያኔ ማፍያዎች በመተባበር በአማራው ህዝብ ከትውልድ መሬቱ ማፈናቀ መግደል ማጥቃት በሃይል መሬቱን መንጠቅ ወ.ዘ.ተ ከወያኔ ጋር ተባብራ የአማራው ህዝብ ግፍ እየተፈጸመበት ነው ።

4 የመሬት መስፋፋት ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የመጀመሪያው ስሙ ፤ ትግራይ ብሔር ድርጅት ፤ቀጥሎ ማሕበር ገስገስቲ ብሔር ትግራይ ( ማ.ገ.ብ.ት. ) ፤ቀጥሎ ትግሉ እንደ ጀመረ (ተ.ሓ.ህ.ት. ) ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ  በየካቲት ወር 1967 ዓ. ም.  ቀጥሎ በ1ኛ ጉባኤው በየካቲት 5 ቀን 1971 ዓ. ም. ስሙን በመለወጥ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ( ህ.ወ.ሓ.ት. ) ተብሎ ተጠራ ።ይህ ድርጀት ገና ወደ በረሃ ሳይወጣ ትግሉን ከመጀመሩ በፊት በፀረ አማራ ተሰልፎ ፤የአማራ ስም በማጥፋት ትምክህተኛ ፤ፀረ ህዝብ ትግራይ ፤ ተስፋፊ ፤ጨቋኝ ገዢ ፤ትግራይና ኤርትራ ነፃ ሃገራት በቅኝ ግዛቱ በሃይሉ የጠቀለለ ቀኝ ገዢ ወ.ዘ.ተ እያለ ፤ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር የተፈጠረችው በ19ኛው ክፍለ ዘመን በምኒሊክ መንግሥትነት ስትሆን ግዛትዋን በመስፋፋት ኢትዮጵያ ተብላ ታወቀች በማለት ታሪክዋን በማጉደፍ ፤የካደ ድርጅት ይህ ነው ።የኢትዮጵያ ስም

 

ያጠፋ ፤ወራሪ ፤ተስፋፊ ፤ሽብርተኛ ፀረ ኢትዮጵያ ፤ፀረ ህዝብ አንድነት ፤ሆኖ ተፈጥሮ የባእዳን ፀረ ኢትዮጵያ ሃይሎች ቅጥረኛ ሆኖም የመጣ ድርጅት ህ.ወ.ሓ.ት. ነው።

ህ.ወ.ሓ.ት. በረሃ ደደቢት ከመውረዱ በፊት የዘጋጀው የፕሮግራሙ ረቂቅ የዞ ደደቢት እንደገባ ፤ረቂቅ ፕሮግራሙ 1 አረጋዊ በርሄ ዋናው አዘጋጅ 2 ግደይ ዘራጽዮን ተባባሪ 3 አባይ ጸሃየ 4 መለስ ዜናዊ 5 ስብሃት ነጋ 6 ሥዩም መስፍን 7 ስየ አብርሃ 8 አውዓሎም ወልዱ ተባብረውም ፕሮግራሙን አዘጋጅተው ጽፈው በመጽህፍ መልክ ሰንደው ፤በየካቲት ወር 1968 ዓ . ም. ለህዝብ ተሰራጨ ።

የመሬት መስፋፋት የወያኔ መሪዎች ትልቅ ትኩረት የሰጠት የምትመሰረተው የትግራይ መንግሥት ሰፊና ለም መሬት በመውረር ወደ ውጭ መውጫ ከሱዳን የሚያገናኝ ኩታ ገጠም ጎረቤት መሆን ፤የሰፋፊ እርሻ ባለቤት መሆን ፤ወንዝ ፤ጫካ ፤በስፋት ያላት ትግራይ መፍጠር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ወያኔ ተ.ሓ.ህ.ት. ሰሜን ጎንደር በሙሉ በፕሮግራሙ በማስገባት ወልቃይት ፤ ጠገዴ ፤ጠለምት ፤ቃፍታ ሑመራ የትግራይ ነው ተብሎ ተካተተ።

ሰሜን ወሎ አለ ውሃ ምላሽ ራያና ቆቦ እስከ ታች ሶቆጣ የትግራይ ነው ተብሎ ተካተተ ። ከአፋርም እንደዚሁ በማአድን ሁብታቸው የሚታወቁ ብዙ ወረዳዎች

ከዚህ በታች ስም ዝርዝራቸው ቀጥሎ ያለው ከማ.ገ.ብ.ት. እስከ ተ.ሓ.ህ.ት. ቀጥሎም እስከ ህ.ወ.ሓ.ት. በከፍተኛ አመራር ፖሊት ቢሮ ደረጃ ሃላፊነት ድርጅቱን እየመሩ ከየካቲት ወር 1967 ዓ.ም. እስከ  ሓምሌ ወር 1977 ዓ

.ም. በዋና የድርጅቱ መሪነትና ፈላጭ ቆራጭ ሆኖው የመጡ አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘራጽዮን በስልጣን ሽኩቻ ብቻ ሲባረሩ ቀሪዎቹ ደግሞ በዛው የቀጠሉ ናቸው ።በፖሊሲም ሆነ በሚከተሉት የአቋም ፕሮግራም ልዩነት ሳይፈጠርባቸው አንድ አካል አንድ አምሳል ሆነው የመጡ ሁለቱ ዋና መሪዎች እንደተባረሩም የድርጅቱ ሥራና ተግባርም ምንም ሳይዛነፍ በነበረበት ሂደት  ቀጠለ ።ቀጥሎም በ1993 ዓ. ም. በስልጣን ሽኩቻ በመለስ ዜናዊ እና በስብሃት ነጋ የተባረሩትም በፕሮግራሙ አቋምና በፖሊሲ ልዩነት ሳይሆን በተፈጠረው የስልጣን ይገባኛል በዚሁ በመጣው አለመግባባት ስየ አብርሃ ፤ገብሩ አስራት ፤አውዓሎም ወልዱ ፤ተወልደ ወ/ማርያም ፤አረጋሽ አዳነ ከፖሊት ቢሮው ሲባረሩ ፤በሥልጣን በነበሩበት ጊዜ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ያጠቁ የገድሉ ዘር በማጥፋት ወንጀል በንጹህን ደም የታጠft አረሜኔ ጨካኞች ፤ሃገርና ህዝብ ለባእድ ሃገር የሸጡ ከሃዲ ናቸው ።በለንደኑ ስብሰባ በየካቲት ወር መጀመሪያ 1983ዓ.ም አሰብ ለኢትዮጵያ ነው የሚገባው ሲሉ አደራዳሪዎች መለስ ዜናዊ ይህን ሲቃወም መለስ ዜናዊ ደግፈው አስብ የኤርትራ እንጂ የኢትዮጵያ አይደለም ብለው ለአደራዳሪው ሂአርማን ኮሆን የተቃውሞ መልእክት ያሳለፉ እነዚህ ከሃዲዎች ናቸው ፤ዛሬ አዲስ ጭምብል ሰፍተው ኢትዮጵያዊ መስለው የሚታዩት ፤ልክ የነ አረጋዊ በርሄ ዘዴ ተከትለው እኛ ያባረሩን የኢትዮጵያ ግዛት መከበር አለበት ፤የታገልነው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲን ለማምጣት ነው ፤አሰብና ባድሜ የኢትዮጵያ ናቸው ብለን በተፈጠረው ክርክር አባረሩን በማለት የፈጠሩት ደርቅ ውሸት ፤ቀላል የማይባል ቁጥር ኢትዮጵያዊም አደናግረዋል፤ ይህ የሚለት የሚናገሩት ለምን በትግሉ በረሃ በነበሩበት አያነሱትም አይከራከሩም ነበር ? ኢትዮጵያዊ ስሜት ያልነበራቸው ቀንድ ያወጡ ፀረ ኢትዮጵያ ፀረ ህዝብ አንድነት ተሰልፈው ኢትዮጵያን ያጠቁ መሪዎች ናቸው ።እነ ስየ አብርሃ አረጋዊ በርሄ ወ.ዘ.ተ. በየስብሰባው በየመድረኩ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ሲያወግዙና እንደመስሣቸው አለን እያሉ የጉሮሮ ላንቃቸው እስኪ ሰነጠቅ፤ እያለቀሱ ድርጅቱን ሲመሩ ነው ያየናቸው ፤ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ለማደናገር ብለው የሚዋሹት ከተግባራቸውና ከመጡበት የ17 ዓመት የአመራር ጉዛቸው የፈጸሙት ግፍ ፤አድበስብሶ አደናግሮ ገበናቸው ለመደበቅ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለጥቂት ቢያታሉሉም በሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ተቀባይነት የለዉም ።ደደቢት በረሃ የወረዱት ኢትዮጵያና ህዝብዋ ለማጥቃት ለማጥፋት ነው ፤እንዚህ ጠላት እንጂ ወዳጅ አይደሉም                                                አሁንም ጠላት ናቸው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ላጠቃው ጠላቱ ምህረት መስጠት የለበትም ፤የጊዜ መጠብቅ ካልሆነ ። ፤ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ችግርና ውድቀት እነዚ መሪዎች የፈጠሩት ያመጡት ነው ። ዝም ብሎ ከሰማይ የወረደ አይደለም ።፤ዋናው መሪ አረጋዊ በርሄ ህዝብ የፈጀ ሃገር የሸጠ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶችና ታሪካዊ መዛግብት መጻህፍት ከየቤተክርስትያኑ በሃይል ዘርፎ የሸጠ ኢትዮጵያና ህዝብዋ ለዛሬው ሲኦል የዳረገ በየስብሰባው ይጠራል ፀረ

 

ኢትዮጵያና ፀረ ህዝብ ሰውየ መድረክ ወጥቶም ይናገራል ፤ ፤ይህ ትልቅ ስህተት ነው ፤የፈሰሰው የንጹሃን ደም ጋባዞቹ ረስተዉታል ። ለወደ ፊቱም ይወቀሳሉ ፤ሊወገዙም ናቸው ።የንጹሃኑ ደም እግዚአቢሄር ፊት ቆሞ እየጮኸም ነው /// ቀጥሎ ተፈላጊ ወጀለኞች ዋናዎቹ ስም ዝርዝሩን ከዚህ በታች ያሉትን ሲሆኑ ፤ ለኢትዮጵያውያን የሕግ አዋቂዎች እንስጥ ። እነዚህን ከያሉበት የሕግ ባለሙያ ኢትዮጵያውያን በሚከተሉት የሕግ አሰራርና መንገድ ለፍርድ ማቅረብ የነሱ ሙያ በመሆኑ አካሄዱ ለባለ ሞያዎቹ እንስጥ ፤እኛ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ግዴታችን ይህ ብዙ የገንዘብ ወጪ ስለ ሚጠይቅ በሁሉ ኢትዮጵያዊ እንዲ ሸፈን የኛ ጥረትና ሃላፊነቱን እንወጣ ።

 

 

 

1 አረጋዊ በርሄ       2   ግደይ ዘራጽዮን     3 ስብሃት ነጋ        4   አባይ ጸሃየ     5 ሥዩም መስፍን

6 መለስ ዜናዊ ሲሆኑ ። እነዚህ ስድስቱ አመራር ትግሉ ከመጀመሩ በፊትና ትግሉም እንደ ተጀመረ ተ.ሓ.ህ.ት. ህ.ወ.ሓ.ት. እየመሩ የመጡ ና የመሩ በከፍተኛ ሃላፊነት የነበሩ አሁንም ያሉ ትንሽ ዓመታት ቅየት ብሎም ስየ አብርሃ ፤ገብሩ አስራት ፤አውዓሎም ወልዱ የተቀላቀሉ ፖሊት ቢሮ ፕሮግራሙን በማሰናዳት ፤የስሜን ጎንደር ፤ የሰሜን ወሎ ለምና ሰፊ መሬት ወደ ትግራይ አስገብተው የነጠቁ ተስፋፊዎች የአማራው ህዝብ ዘር ያጠፉ የፈጸሙ ታሪካዊ ቅርሶች የሸጡ ፤ለምና ሰፊ የኢትዮጵያ ግዛት ለሱዳን የሸጡ ወ.ዘ.ተ. ግንባር ቀደም ተጠያቂ ናቸው ቀጥለው ያሉትን ፖሊት ቢሮ እየተከታተሉ የመጡ ሲሆኑ ከእነ አረጋዊ በርሄ የተቀበሉትን አደራ መስመር ተከትለው የኢትዮጵያ አንድነት እያዳከሙ የሃገርና የህዝብ ሃብት ነብረት በመዝረፍ እየዘረፉ ሃገርና ህዝብ ወደ ድህነት አዘቅት ያስገft ወራሪ ፀረ ሃገርና ፀረ ህዝብ ፤ብዙ ሚልዮን ህዝብ የፈጁ የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች

፤የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የሸጡ ሸጠውም ኢትዮጵያ የባህር በር አልባ ዝግ ሃገር ያደረግዋት ከሃዲ ባንዳ ፀረ ኢትዮጵያና ህዝብዋ እነዚህ ናቸው ፤

 

7 ስየ ሃብርሃ8  አውአሎም ወልዱ9 ገብሩ አስራት10  ፃድቃን ግ/ተሳይ11  ተወልደ
ወ/ማርያም12  አርከበ እቁባይ13  አረጋሽ አዳነ14    ክንፈ ገብረመድህን

15    ቴድሮስ  ሓጎስ          16     ፀጋይ በርሄ  (ሃለቃ )       17   አዜብ መስፍን      18  ገብረአብ ባርኖባስ

 

19ቴድሮስ አድሓኖም20 ዶ/ር ሰሎሙን እንቋይ21አባይ ወልዱ22ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል
23ትርፉ ክ/ማርያም24   ፈትለወርቅ ገ/እግዚአቢሄር25ዓለም ገብረዋህድ

26 ጌታቸው አሰፋ         27    አዲስ ዓለም ባሌማ          28 አባዲ ዘሞ           29    በየነ ምክሩ

30 ገብረመስቀል ታረቀ   31   ሙሉጌታ አለምሰገድ         32 ክንፈ ገብረመድህን 33 አበበ ተ/ሃይማኖት

የአመራሩ ቀኝ እጅ በመሆን ህዝብ የፈጁም ከሚፈለጉ ማእከላይ ኮሚቴ የነበሩ አሁንም ያሉ በኋላም ወደ ፖሊት ቢሮ የወጡ በሰቆቋ ህዝብ የፈጁ የሚከተሉት ናቸው

1 ዘርአይ አስገዶም             2 ሓሰን ሹፋ            3 ሕftር ገ/ኪዳን           4    ሳሞራ የኑስ

5 ብርሃነ ገ/ክርስቶስ         6 ሰሎሞን ተስፋይ ጢሞ    7 የማነ ኪዳነ ጃማይካ   8 ቢተው በላይ

9 ታደሰ በርሄ  ጋውና          10  ሃለቃ ጸጋይ በርሄ             11 አብርሃ ካሕሳይ        12 ታደሰ ወረደ

13 ወ/ሮ ሮማን ገ/ሥላሴ       14 ኢሳያስ ወ/ጀወርጊስ          15 ብርሃነ ኪ/ማርያም         16 ተክለወይኒ አሰፋ

17 ቅዱሳን ነጋ                   18  ኪሮስ ቢተው                  19 አስመላሽ ወ/ሥላሴ       20 ጌታቸው አሰፋ

 

21 ሙሉ ሰንደቅ                22 ሸዊት ገ/ክርስቶስ             23 ሕሽ ለማ                   24 አክሊሉ ደንበአርቃይ ፤እነዚህ ብቻ ሳይሆኑ በጠቅላላ ማእከላይ ኮሚቴው የህ.ወ.ሓ.ት ብዙ ከባድ ወንጀል የፈጸሙ ናቸው ከፍርድ አያመልጡም የጠየቃሉ ።

ከዚህ በታች ተዘርዝረው የሚታዩ ታጋዮች በንጹሃን ኢትዮጵያዊ ዜጎች ከፖሊት ቢሮው በሚሰጣቸው ትእዛዝ ህዝበ ኢትዮጵያ የፈጁ የሓለዋ ወያኔ ሃላፊዎች ናቸው ።

1 ብስራት አማረ           2 ሓሰን ሹፋ                3 ዘአማኗኤል ለገሰ ( ወዲ ሻምበል )

4 አበበ ዘሚካኤል          5 መኮንን ገ/ማሪያም ወዲ ኾምበል    6 አረፋይኔ ጡሩራ

7 ተስፋየ አፈርሰው(አጽብሃ     8 ተስፋየ መረሳ (ጡሩራ )     9 ታደሰ መሰረት

10 ዘርአይ ይሕደጎ                11  ካሕሳይ ቆራጽ                 12 መኮነን ገ/ማርያም ( ወዲ ኮምበል )

13  ዘአማኑኤል ለገሰ ( ወዲ ዛምበል ) 14  ሃይሉ በርሄ (ሃይሉ ሳንቲም )  15  ሕftር ገ/ኪዳን

16  ግደይ ወዲፉዳል           17  ተስፋየ ጡሩራ መረሳ                18  ተስፋየ አፈርሰው

 

19  ልኡል በርሄ20   ወልደሥላሴ ገ/ሚካኤል21 ገ/እግዚአቢሄ የአዲስ አበባ ፖሊስ
ኮሚሽነር የሆነው22አስመላሽ ው/ሥላሴ23 ፍሬ ጎይትኦም ( ሴት )አውስትራሊያ
ፐርዝየምትገኝ24 አራንሺ የአ.አ. ኮሚሽነር25 ቢተው በላይ

እነዚህ በሓለዋ ወያነ በተለያየ የሶቆቃ ዘዴዎች ህዝብ የጨረሱ ያሰቃዩ ዋና ዋናዎቸ ሲሆኑ ብዙዎቹ ግን ለምስታወስ አልቻልኩም በጣም ብዙ ናቸው ፤የእነዚህ ዋና መሪ ደግሞ ብስራት አማረ ነው ።የሞቱም ብዙ ናቸው ።

 

 

ገብረመድህን   አርአያ

ፐርዝ አውስትራሊያ

20/07/2017

5 Comments

  1. “ኢትዮጵያዊ ለመሆን የኣማራ ቆብ መልበስ ኣለብህ”፣ “ሱር ነቀል ለውጥ”፣ ሌሎችም የኣማራ ተወላጆች ሳይቀሩ ኣገዛዙን ለመግለጽ ይሉ እንደነበር እንዴት ይክዳል። የኦሮም፣ የኤርትራ፣ የወሎ፣ የቤጌምድር ሌሎችም የኣማራ ኣገዛዝ ይወገድልን ኣላሉምን? እንዲህ ማለት ግን ኣገዛዙን ለመግለጽ እንጂ ማንም ከኣማራ ህዝብ መጥላት እንዳልነበረ ግልጽ ነው።
    ስለዚህ ኣሁንም የኣማራ ህዝብ ጥላቻ እያላችሁ ኣታሰላቹን፤ የሚሞተው ያለው ኦሮማስ ደም ኣይደለምን? የሕግ የበላይነት ስርዓት ነው የምንፈልገው በዚህ ሊሳተፍ የሚችል ማሳተፍ እንጂ ከ40 ኣመት እንድህ ተባለ እያላቹሁ የባንዳዎች እድሜ ኣታራዝምሉን።

  2. Are you telling us Asseb was under wallo and adminstration
    Never been under Eritrea? You know what in todays technology
    You can’t run from the truth you just need to google
    The map of Eritrea even from 1902 then you can
    SEE WHERE ASSEB IS LOCATED. Don’t be stupid and fool
    Yourself and the reader’s.

  3. Are you telling us Asseb was under wallo and adminstration
    Never been under Eritrea? You know what in todays technology
    You can’t run from the truth you just need to google
    The map of Eritrea even from 1902 then you can
    SEE WHERE ASSEB IS LOCATED. Don’t be fool
    Yourself and the reader’s.

Comments are closed.

Share