February 6, 2017
1 min read

«አንተስ…?»

( ወለላዬ )

ዓይኔን  በዓይኔ  ያየሁበት፣

በስተእርጅና  ያገኘሁት፣

የትናንቱ  ማሙዬ፣

ያሳደኩት  አዝዬ

የንግሊዞችን  ወረራ

ሰምቶ፣

በቴዎድሮስ ሞት

ተቆጥቶ፣

ለምን?  ለምን  ሞተ?

ብሎ  ሲያለቅስ፣

የዓይኑን  ዕንባ  ላደርቅ-

የልቡን  መሰበር  ላድስ፣

ጀግኖቻችንን  ቆጥሬ-

ታሪካችንን  ባወድስ፣

ዕንባውን  ዋጥ  አድርጎ-

በአትኩሮት  ዓይኔን  እያየኝ፣

«አንተስ…?» አንተስ!-

ምን  ሰርተሀል?  በማለት  ጠየቀኝ።

እድሜ  ቢደራረብ  ተግባር  ሳይላበስ፣

እንደዚህ  እንደኔ  ያስጠይቃል  ለካስ!

 

 

 

1 Comment

Comments are closed.

his grace abune matyas
Previous Story

[ፓትርያርክ አቡነ ማትያስን] በማሸነፌ ተደስቻለሁ፣ በማሸነፌ አልተደሰትኩም !!

elias Gebru
Next Story

ምጧ የተራዘመባት- ኢትዮጵያ! – ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop