ኳሧ በእሳቸው እጅ ሣትሆን በሕዝብ ቁጥጥር ሥር ነች።

ከሎሚ ተራተራ !
መቼም የሰሞኑን ያገራችንን ጉዳይ ሁሉም በየጓዲያውና በየአደባባዩ እየመረመርና እያሰላሰለ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም። ማግኝትና ማጣት እንደሚያልፉ ሁሉ፤ መግፋትና መገፋትም አልፎ ታሪክ መሆኑ አይቀሬ ነው። እንደው እኔም በጓዳዬ ሆኜ ወደሖላ በመመለሰ የሀገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ መቃኝት ሰጀምር፤ አንድ አሰገራሚ ነገር ትዝ አለኝ፤ ይኸውም ትዝ ይላችሁ እንደሆን ከምርጫ 97 ሦሰት አመት በፊት በአዲሰ አበባ ዩንቨርሰቲ ማእከል ተከናውኖ በነበረው ሰብሰባ ሟቹን መለስን ያፋጠጠው ምሁር የተናገረው ቃል………እንዲህ ነበር ያለው፡ እንዲህ…….. “”አሁን ምንድነው ልናደረግ የምንችለው ? ኳሶ በእርሦ ቁጥጥር ሰር ሰላለች የእርሶን ቅንነት ብቻ እንዳይነፈጉን ነው።”” ነበር ያለው።
የኳሰ ነገር፤ ኳሦ ከሳችው እጅ በሚያሰደንቅ ሁኔታ ሁለተኛም እጃቸው ላትገባ ምላ ተሰፈንጥራ ወጣች:: የወያኔ መሪዎቸም የኳሰ ሜዳ አሰላለፈም ሆነ አጨዋወት ባለማወቃቸው አጀሬ ኳሰ ባደባባይ አይናቸው እያየ ኳሰ ከእጃቸው አምልጣ በህዝብ ቁጥጥረ ሰር ዋለች። በመዋሏ እጀግ ደሰ ብሎኛል እንኳን ደሰ አላቸሁ።
ታዲያ አሁን ምን ይደረግ? ? ቁምነገሩ እሱላይ ነው። አዎ ኳሰ አያያዝ ይጥይቃል፤ ያጨዋወት ቴክኒክና ያሰላለፍ ሰልት እጀግ አሰፈላጊ ነው። በተለይ አሁን ወያኔ በተለያየ ሁኔታ ማለትም ( በውሰና) ወዘተረፈ…”.ማኖ..”… እየነካ በመሆኑ አሰላለፉ ሁሉ ባለም አቀፍ ደረጃ ምንም አይነት የቡድን መሪ የሌለው ተራ ቡድን እየሆነ በመምጣቱ ሕዝብ የፍጹም ቅጣት ምት( እሪጎሬ) ማግኝቱ አይቅሬ ነው።
የፈጹም ቅጣት ምቱ ግን በምንም አይነት ሁኔታ መሳት የለበትም፤ (ከመረብ መዋል አለበት) ከወዲሁ፤ የፖሎቲካ ድርጀቶችም ሆኑ ደጋፊዎች የእርሰበርሰ መጠላለፍን አቁመው በሰከነ ኢትዮፒያዊነት መንፍሰ ሕዘብን በማሰትባበር ማሊያችንን የኢትዮጲያ ባንዲራ አጥልቀን አሰላለፋችንን አሳምረን የዋንጫውን ግጥሚያ ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መዘጋጀት አሰፈላጊ ነው።
የፍጹም ቅጣት ምቱን ማን እንደሚመታው ወሰነን መዘጋጀት ይጠበቅብናል እላለሁ። አራጋቢ…… ወያኔዎች ቢሆኑም የመሃል ዳኛው ግን ሕዝብ በመሆኑ ውጤቱ ያማረ…የነጻነት ጮራ እንደሚፈነጥቅ አልጠራጠርም እናንተም አትጠራጠሩ።.
አለማቀፍ የሚዲያ ዘጋቢዎች ሰለማይጠፉ ለዘገባው አታሰቡ በቻ ለውጤቱ እንዘጋጅ እያልኩ ይቺን አጭር የኳሦ በሕዝብ ቁጥጥር ሥር ነች መልክቴን አሳተላልፋለሁ። የዋንጫ ባለቤት ለመሆን ያብቃን እያልኩም….ነይ እርግብ አሞራ……ነይ እርግብ….ከሕዝብ,፣ድል..ጋራ…..ነይ..እርግብ…….በማለት እሰናበታለሁ።……..በቸር ይግጠመን፤
ከ ሎሚ ተራ,ተራ Wednesday, September-04-13 MWL200825@yahoo.com
ኳሦ…..በሕዝብ…..ቁጥጥር,,.ሥር ነች;;;;;;;;;;;;;;;;;;;;;;;;ኳሦ…በሕዝብ……..ቁጥጥር….ሥር….ነች !!!!!!!
አሰተያየትም ሆነ ጥያቄ ቢኖራችሁ፦በዚህ ኢሜል አድራሻ ብትልኩ መልካም ነው። MWL200825@yahoo.com
ድል ለኢትዮጲያ ሕዝብ!!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰለማዊ ትግል ፋይዳ (ከአብርሃ ደስታ)
Share