በወረባቡ የአንድነት አባላትን ጨምሮ 45 ወጣቶች መታሠራቸውን ፓርቲው ገለፀ

July 22, 2013

በደቡብ ወሎ ዞን በረባቡ ወረዳ በስግደት ላይ የነበሩ የአንድነት ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ አብዱ መሐመድ እና አቶ እንድሪስ አህመድን ጨምሮ 45 ወጣቶች መታሰራቸውን ምንጮቻችን ከስፍራው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ከታሰሩት መካከልም ወጣት ሱልጣን መሐመድ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየ እንደሚገኝና እስካሁንም የህክምና እርዳታ እንዳልተደረገለት ተጠቁሟል፡፡ መንግስት የወረዳውን ነዋሪዎች የደሴው ሼህ ኑሩ ይማምን መገደል በሰላማዊ ሰልፍ ካላወገዛችሁ የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ አይሰጣችሁም፣ ዘርና ማዳበሪያም አታገኙም የሚል ማስፈራሪያ በካድሬዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑንም ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡

በተለይ ከታሰሩት 45 ወጣቶች መካከል 3ቱ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች በመሆኑ የእድሜ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ እና ወጣቶቹ ከመስኪድ ውጭ በአካባቢው ሜዳ ላይ ሲሰግዱ ስለተወሰዱ አብዛኞቹ ቤተሰቦቻቸው እንደማያውቁና እስካሁንም እየፈለጓቸው መሆኑ ታውቋ፡፡ ወጣቶቹም ከታሰሩ ከሳምንት በላይ የሆናቸው ሲሆኑ እስካሁን ክስ እንዳልተመሰረተባቸው ተጠቁሟል፡፡ ይህን ዜና እስክናሰራጭ ድረስ ከታሳሪዎች መካከል  ከፊሉ በደሴ ቀሪዎቹ ደግሞ በሐይቅ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ እስር ላይ እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም ከወረዳውና ከደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደርና የፀጥታ ክፍል ስለጉዳዩ ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን በረባቡ ወረዳ በስግደት ላይ የነበሩ የአንድነት ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ አብዱ መሐመድ እና አቶ እንድሪስ አህመድን ጨምሮ 45 ወጣቶች መታሰራቸውን ምንጮቻችን ከስፍራው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ከታሰሩት መካከልም ወጣት ሱልጣን መሐመድ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየ እንደሚገኝና እስካሁንም የህክምና እርዳታ እንዳልተደረገለት ተጠቁሟል፡፡ መንግስት የወረዳውን ነዋሪዎች የደሴው ሼህ ኑሩ ይማምን መገደል በሰላማዊ ሰልፍ ካላወገዛችሁ የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ አይሰጣችሁም፣ ዘርና ማዳበሪያም አታገኙም የሚል ማስፈራሪያ በካድሬዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑንም ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡

በተለይ ከታሰሩት 45 ወጣቶች መካከል 3ቱ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች በመሆኑ የእድሜ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ እና ወጣቶቹ ከመስኪድ ውጭ በአካባቢው ሜዳ ላይ ሲሰግዱ ስለተወሰዱ አብዛኞቹ ቤተሰቦቻቸው እንደማያውቁና እስካሁንም እየፈለጓቸው መሆኑ ታውቋ፡፡ ወጣቶቹም ከታሰሩ ከሳምንት በላይ የሆናቸው ሲሆኑ እስካሁን ክስ እንዳልተመሰረተባቸው ተጠቁሟል፡፡ ይህን ዜና እስክናሰራጭ ድረስ ከታሳሪዎች መካከል  ከፊሉ በደሴ ቀሪዎቹ ደግሞ በሐይቅ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ እስር ላይ እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም ከወረዳውና ከደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደርና የፀጥታ ክፍል ስለጉዳዩ ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

– See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=5043#sthash.3wJCeMzM.dpuf

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop