ሰበር ዜና: በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

July 22, 2013

በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ዛሬ ሐምሌ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት በፕሬዘዳንቱ ቢሮ አካባቢ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ፡፡ ሰልፉን ያካሄዱት የዚህ ዓመት የክረምት የተፈጥሮ ሳይንስ የድግሪ መርሃ ግብር የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡ ተማሪዎቹ በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ ያካሄዱበት ምክንያት ቀደም ሲል ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት ትምህርቱን የሚከታተሉት ለ 6 ዓመታት እንደሆነ እና 4 ዓመቱን ከተከታተሉ በኋላ የባችለር ኦፍ ሳይንስ ድግሪ የምስክር ወረቀት እንደሚሰጣቸው፤ ቀሪው 2 ዓመት ደግሞ መምህር ለመሆን የሚያስችላቸውን የስነ ትምህርት ዘዴ(ፔዳጎጂ) እንደሚወስዱ መዋዋላቸው ተጠቁሟል፡፡ በዚህም ምክንያት 4 ዓመት የክረምት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችም በተዋዋሉት መሰረት ድግሪያቸው እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

የዪኒቨርስቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ክንዴ በበኩላቸው ተማሪዎቹ ሰልፉን እንዲበትኑ እና ከተወካዮቻቸው ጋር መነጋገር እንደሚቻል በገቡት ቃል መሰረት እንዳናገሯቸው ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም የተማሪዎቹ ተወካዮች ከፕሬዘዳንቱ ጋር ከተወያዩ በኋላ ፕሬዘዳንቱ አሰራሩን እንደማያውቁና በሌሎች የሀገሪቱ ዩኒቨርስቲዎችም ተመሳሳይ አሰራር ካለ አጣርተው ከ3 ቀናት በኋላ ምለማጣራትላሽ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ መያዛቸው ታውቋል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም የዪኒቨርስቲው ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት እና ፕሬዘዳንት ጽህፈት ቤት ስለ ጉዳዩ ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

 

 

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop