«ዉጡ ፤ በሰላማዊ ሰልፎች ላይ ተሳተፉ!» እስክንድር ነጋ

July 10, 2013

ሐምሌ 3 ቀን 2005 ዓ.ም

አቶ በትረ ያእቆብ በቃሊት አቶ አንዱዋለም አራጌን እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን በጎበኙበት ወቅት የሚከተለዉን መልእክት ከእስክንድር ነጋ ይዘው መጥተዋል። ተላናት ቅኝ የነበሩ የአፍሪካ አገሮች በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባት የትናየት እንደደረሱ የጠቆሙት አቶ እስክንድር «ትናንት የአፍሪካ መሪ እንዳልነበርን፣ ዛሬ ጭራ ሆነናል» ሲሉ በኢትዮጵያ ያለዉ የሕዝብን መብት የሚረግተ፣ አምባገናዊ ስር;አት መኖር ብሄራዊ ዉርደት እንደሆነም ገልሰዋል።

አቶ እስክንድር የአንድነት ፓርቲና ሌሎች እየመሩት ያለዉን ሰላማዊ እንቅስቃሴ በአገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገር የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲቀላቀለዉ ጥሪ አቅርበዋል። «ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጊዜና ቦታ ሳይገድበዉ በአንድነት ሊንቀሳቀስ ይገባዋል» የሚል አገር ወድድነት የተሞላበት መል እክስት አስተላልፈዋል።

«የጠባቂዎችን ግልምጫና ሀይለ ቃል ተቋቁሞ በዚያ ዉጥረት በበዛበት ሁኔታ እንዲህ ሲል ነበር እስክንድር ለመላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሁም ለዲያስፖራዉ መልዕክቴን አስተላልፉልኝ ያለዉ» ሲኡ አቶ በትረ የእስክንድርን መልእክት እንደሚከተለው አቅርበዉታል።

“አገራችን ኢትዮጵያ ትልቅ አጣብቂኝ ዉስጥ ትገኛለች ፤ እንደ አገር በመቀጠልና ባለመቀጠል አጣብቂኝ ዉስጥ፡፡ ይህ ደግሞ የህልዉና ጉዳይ ነዉ፡፡ በተጨማሪም እኛ ዜጎቿም በጭቆና ፍዳችንን እያየን እንገኛለን፡፡ ትናንት በአዉሮፓዉያን ተጠፍጥፈዉ የተፈጠሩ እንዲሁም እኛ ያዋለድናቸዉ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ዲሞክራሲን ሲጎናፀፉ እኛ እያደር ወደ ኋላ እያዘገምን እንገኛልን፡፡ ትናንት የአፍሪካ መሪ እንዳልነበርን ዛሬ ጭራ ሆነናል ፤ ይህ ብሔራዊ ዉርደት ነዉ፡፡”

“ስለሆነም ይህንን ችግር ከስሩ ለመቅረፍ የግድ ሰላማዊ ትግል ማካሄድ ይኖርብናል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አሁን በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ እንዲሁም በሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪነት የተጀመረዉ የትግል እንቅስቃሴ ይበል የሚያስብልና የሚያበረታታ ነዉ፡፡ ትግሉ በዚሁ ተጠናክሮ ከቀጠለ እንዲሁም የሁላችን ተሳትፎ ከታከለበት ያለምንም ጥርጥር ወደ ነፃነት ጎዳና ያደርሰናል፡፡ ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጊዜና ቦታ ሳገድበዉ በአንድነት ሊንቀሳቀስ ይገባዋል፡፡”

“አትፍሩ! የአንባገነኖችን ዛቻ አትቀበሉ! ፍርሐት የአንባገነኖች ዋንኛ የአፈና መሳሪያ መሆኑን በመገንዘብ ከልባችሁ አዉጡት፡፡ መቁሰል ፣ መታሰር እና መንገላታት ቢኖርም ይህ የምንከፍለዉ መስዋትነት አገር አልባ ከመሆን ያድነናል ፤ የተሻለች አገር ለመገንባት ይረዳናል፡፡ ስለዚህ ዉጡ! ፤ በሰላማዊ ሰልፎች ላይ ተሳተፉ፡፡”

እስክንድር አያይዞም ለዲያስፖራዉ እንዲህ አለ፡- “ዲያስፖራዉ ለሀገሩ ያለዉን ቀናኢነት የሚያሳይበት አጋጣሚ ይህ ነዉ፡፡ ለህዝቡ ያለዉን ፍቅርና ወገንተኝነት የሚገልፅበት መንገድ ነዉ፡፡ ይህንን በመረዳት አገር ወዳድ ከአገር ዉጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዉያን በጠቅላላ በሚካሄዱ የተቃዉሞ ሰልፎች ላይ በተለይም አዲስ አበባ ላይ በሚካሄደዉ በአካል በመገኘት ተሳታፊ ሁኑ፡፡”

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop