አራጣ በማበደር የተፈረደባቸው አየለ ደበላ (IMF) በማረሚያ ቤት አረፉ

July 10, 2013

(በፍሬው አበበ)

በቅጽል ስማቸው አይ ኤም አፍ በመባል የሚታወቁትና በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዐቃቤ ሕግ ከዛሬ አራት ዓመታት በፊት በአራጣ ማበደር ክስ ተመስርቶባቸው በማረሚያ ቤት ይገኙ የነበሩት አቶ አየለ ደበላ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቀብራቸው ስነስርዓት ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ትላንት በቅድስት ስላሴ ቤ/ክ ተፈጽሟል።አቶ አየለ ደበላ በሕመም ላይ እንደነበሩና የፌዴራል ማረሚያ ቤቱም አስፈላጊውን ሕክምና በአገር ውስጥ ሆስፒታሎች እንዲያገኙ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁሞ ሰኔ 30 ቀን 2005 ሕይወታቸው ማለፉን ለሰንደቅ ጋዜጣ አረጋግጧል። የአቶ አየለ አስከሬን ከማረሚያ ቤት ትላንት ቤተሰቦቻቸው በመረከብ የቀብር ሥነሥርዓቱን በቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን መፈጸሙን የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

ስለአቶ አየለ ደበላ የክስ ጭብጥ ዳራ

የኢትዮጽያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ከአራጣ ማበደር ተግባር ጋር ተያይዞ በአቶ አየለ ደበላ ላይ ክስ ያቀረበው ግለሰቡ ለባንክ ብቻ የተፈቀደውን አገልግሎት ሲሰጡ ተገኝተዋል፣ የገቢ ግብር አዋጅን በመጣስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሳይከፍሉ ቀርተዋል፣ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስለው በማቅረብ ገቢ ሰብሳቢ መ/ቤቱን አሳስተዋል በሚል ነው። የባለስልጣኑ ዐቃቤ ሕግ በአቶ አየለ ላይ 10 ያህል የወንጀል ክሶችን በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 11ኛ ወንጀል ችሎት በወቅቱ ያቀረበ ሲሆን ፍ/ቤቱም ክሱን ለአራት ወራት ያህል ሲመለከት ከቆየ በኋላ ሐምሌ 13 ቀን 2002 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሰጠው ቅጣት አቶ አየለ ደበላ በ22 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል። በተጨማሪም ለቀሪዎቹ ስምንት ክሶች በድምሩ 308 ሺ ብር ቅጣት እንዲከፍሉ፣ እንዲሁም በንብ ባንክ በዝግ አካውንት አስቀምጠውት የነበረ ብር 12 ሚሊየን፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ የሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት እንዲሁም ሁለት ተሸከርካሪዎች የሶስተኛ ወገኖች መብት ተጠብቆ እንዲወረሱ ሲል ውሳኔ መስጠቱ ይታወሳል።

ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ጁላይ 10 ዕትም።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop