Sport: የብሔራዊ ቡድናችን አጥቂ ጌታነህ ከበደ ዛሬ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጓዘ

June 28, 2013

ከጥሩነህ ካሳ (የወርልድ ስፖርት ጋዜጣ አዘጋጅ)

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግን በኮከብ ግብ አግቢነት እየመራ የሚገኘው ጌታነህ ከበደን ከደቡብ አፍሪካ ክለቦች የቀረበለትን የዝውውር ጥያቄ ተቀብሎ ዛሬ ወደ ደ.አፍሪካ አቅንቷል፡፡ ጌታነህን ለመውሰድ የደቡብ አፍሪካው ሰልቲክ ክለብ ከፍተኛ ፍላጎት አሳይቷል፡፡ በርካታ ደጋፊዎች ያሉት ሰልቲክ ከሌሎች ክለቦች የተሻለ ክፍያ ማቅረቡም ታውቋል፡፡
ጌታነህም በዛሬው ዕለት የጤና ምርመራ ለማድረግ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዟል፡፡ የጤና ምርመራውን ማለፍ ከቻለም አዲሱን የኮንትራት ውል ይፈራረማል፡፡ ጌታነህ ከደደቢት ክለብ ጋር ያለው ኮንትራት ውል የፊታችን ሰኔ 30 የሚጠናቀቅ በመሆኑ ዝውውሩን የተሳካ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop