Sport: የብሔራዊ ቡድናችን አጥቂ ጌታነህ ከበደ ዛሬ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጓዘ

ከጥሩነህ ካሳ (የወርልድ ስፖርት ጋዜጣ አዘጋጅ)

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግን በኮከብ ግብ አግቢነት እየመራ የሚገኘው ጌታነህ ከበደን ከደቡብ አፍሪካ ክለቦች የቀረበለትን የዝውውር ጥያቄ ተቀብሎ ዛሬ ወደ ደ.አፍሪካ አቅንቷል፡፡ ጌታነህን ለመውሰድ የደቡብ አፍሪካው ሰልቲክ ክለብ ከፍተኛ ፍላጎት አሳይቷል፡፡ በርካታ ደጋፊዎች ያሉት ሰልቲክ ከሌሎች ክለቦች የተሻለ ክፍያ ማቅረቡም ታውቋል፡፡
ጌታነህም በዛሬው ዕለት የጤና ምርመራ ለማድረግ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዟል፡፡ የጤና ምርመራውን ማለፍ ከቻለም አዲሱን የኮንትራት ውል ይፈራረማል፡፡ ጌታነህ ከደደቢት ክለብ ጋር ያለው ኮንትራት ውል የፊታችን ሰኔ 30 የሚጠናቀቅ በመሆኑ ዝውውሩን የተሳካ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሰሜን ጎንደር ጭልጋ ከተማ የደረሰኝ መረጃ 

3 Comments

  1. Our football players deserve the recognition from other clubs in Africa and the rest of the world. This is a big bonus to Ethiopian football. Our football brand is unique , un compromised by outside players.

Comments are closed.

Share