June 24, 2013
2 mins read

ምነዋ ! ማንዴላችን ? !

የግርጌ ማስታዎሻ : ከዘጠኝ አመት በፊት ያጣሁት አንድ ወንደም ነበረኝ ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ መጽሐፈ ሲራክ የሚባል። መጽሐፈ የሃገር ፍቅር ልክፍቱን ብቻ አልነበረም ጥሎብኝ እስከ ወዲያኛው ያሸለበው ፣ የዘመናቸን ታላቅ የጥቁር ህዝብ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላን አበክሬ እንዳውቀው የረዳኝ ፣ ለነጻነት ክብር ለዲሞክራ ከቆሙት ጎን እንድቆም ፣ ሰብአዊ መብት ሲዳጥ ዝም እንዳልል፣ የግፉአንን ድምጽ እንዳሰማ የህይወትን ውርስ ያወረሰኝ ወንድሜ ለጥቁር ህዝብ አርበኛው ለኔልሰን ማንዴላ የነበረው ክብር ከፍ ያለ ነበር ! መጽሐፈ “ማንዴላ” እያለ በቀድሞው ለገዳዲ እና የኢትዮጵያ ራዲዮ ተወዳጁ የእሁድ መዝናኛ ተቀኝቶላቸውም ነበር ። ነፍሱን ይማረው እና ዛሬ ያ ወንድሜ በአካል ከእኛ ጋር የለም ! ማንዴላም ሁላችንም እሱ ወደ ሔደበት መጓዛችን ባንቀርም የታለቁ አባትን በጸና መታመም ስሰማ ወንድሜን አስታውሸ ፣ ማንዴላን ለማዘከር በፍጹም ስሜት “ምነዋ ማንዴላ ! ” ብየ ገጠምኩ !
በማለዳው . . .ሰኔ 2005 ዓ.ም June 24,2013 E.c ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ተጻፈ
ከሰላምታ ጋር

ነቢዩ ሲራክ

ምነዋ ! ማንዴላችን ? !
ድምጽህ ቁርጥ ቁርጥ አለ አመመህ
ምነው ደከመህ በማረፊያህ ?
አፍሪካን ከአንባገንን ልጆቿ ጸድታ ሳታይ
ምነዋ መድከም ማሸለብህ ?
የኢትዮጵያን ስርየት ሳይበሰር
ምነዋ የመለየት ጉዞን መጀመርህ
ኢትዮጵያ ከደዌ ተላቃ ሳትጎበኛት
ምነዋ አትቀስቅሱኝ አልክ አንቀላፋህ ?
ምነዋ መልአከ ሞት ከበበህ
የስንብት መርዶ ጽልማሞት ግርማውን አለበሰህ
ምነዋ ጠንካራውን ጉልበትክን ፈተነብህ
የእማማን አፍሪካን ድህነት ማየቱ ታከተህ !
ምነዋ ማንዴላ?. . .

Previous Story

ስለኢሳት ለኢትዮጵያውያን የተላከ መልእክት!

ethiopian housekeepers
Next Story

አንዲት የኮንትራት ሰራተኛ በጅዳ ቆንስል በር ታንቃ ሞተች

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop