«ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ግንባር» የሚል ስም ይኖረናል – ሌንጮ ባቲ

June 21, 2013

የቀድሞ የኦነግ መስራችና አመራር አባላት በብዛት ያሉበት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፎረም በሚል ስም፣ አንድ ድርጅት መቋቋሙ ይታወቃል።  ድርጅቱ የመገንጠል ጥያቄ ጎጂና ጠቃሚ እንዳልሆነ በማተት የኢትዮጵያን አንድነትና ሉአላዊነት በጠበቀ መልኩ የሁሉም መብት የሚከበርባትን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንደሚታገልም ገልጾ ነበር። «ለኦሮሞዎች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የኢትዮጵያዉያን መብት እንታገላለን» ያለዉ ኦዴፍ ፣ የአመራር አባላቱ በተለያዩ ፎረሞች በመገኘት ፕሮፖዛሎቻቸውን እያቀረቡ ሲሆን፣ ከተለያዩ ድርጅቶችም ጋር እየተናገገሩ መሆናቸውንም ይናገራሉ።

 

ከጥቂት ቀናት በፊት፣ ሺሆች በሚያዳምጡት የሲቪሊቲ ፓልቶክ ክፍል ቀርበው አስተያየት የሰጡት፣  የኦዴፍ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ አቶ ሌንጮ ባቲ፣  የሚለያየንን ሳይሆን የሚያቀራርበንን ገመድ የበለጠ  ማጠናከር አለብን ብለዋል። ገዢው ፓርቲ በተለይም በአማራዉና በኦሮሞዉ መካከል የመጠራጠርና የመፈራረት ስመንፈስ እንዲኖር በማድረግ ለሃያ አመት በስልጣን ላይ ሊቆይ እንደቻለ የገልጸኡት አቶ ሌንጮ፣ አማራዉም ሆነ ኦሮሞው በመንቃት ፣ ሌሎች ብሄረሰቦችን በማቀፍ አምባገነንነትንና ጭቆናን መታገል እንዳለበት አሳስበዋል።

 

ኢትዮጵያዊ ፣ እንደ ኦሮሞ፣  አቶ ሌንጮ ይሰጡት በነበረዉ  ልብ የሚስብና የሚያረካ አስተያየት አስተያየት ደስ የተሰኙ አንድ አድምጫ  «ኦሮሞ ያልሆኑ  እናንተን እንዴት ሊቀላቀሉ ይችላሉ ? » በሚል  ላቀረቡላቸው ጥያቄ  አቶ ሌንጮ ሲመልሱ ፣ አሁን የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ቢባሉም ከሌሎች ጋር ተመካክረን ወደ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲአይዊ ግንባር እንደሚለወጡም አሳዉቀዋል። «እየሰራንበት ነዉ ፣ ትንሽ ታገሱን » ነበር አቶ ሌንጮ ያሉት።

 

ይሄንን ኦዲዮ ላቀረበልን የሲቪሊቲ ፓልቶክ ክፍል ምስጋናችንን እያቀረብን፣  ባለ 2 ክፍል የአቶ ሌንጮን ቃለ ምልልስን አቅርበንላቹሃል።

 

ክፍል 1

ክፍል 2

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop