ከመጻሕፍት አምባ: “ትውልድ ያናወጠ ጦርነት” (ቅኝት በአበራ ለማ)

መጽሐፉ ርእስ……………… ትውልድ ያናወጠ ጦርነት
ደራሲ……………………………. ንጋቱ ቦጋለ (ሻለቃ)
አሳታሚ…………………………. በግል
አታሚ……………………………. ኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ የሕትመት ሥራ
የገጽ ብዛት………………………. 341
ዋጋ…………………………………. 55 ብር
ቅኝት………………………………. በአበራ ለማ

ከደራሲው የጦር ሰው የደረሰ ጦማር
ለወንድሜ አበራ ለማ ከሁሉ አስቀድሜ የማክበር ሰላምታዬን አቀርባለሁ።
”የወገን ጦር ትዝታዬ” በሚለዉ የሻለቃ ማሞ ለማ መጽሃፍ ላይ ያቀረብከዉን የመጽሃፍ ግምገማ ጊዜ ወስጄ አነበብኩ ። ከሁሉም በላይ የሰራዊቱን ኑሮና ትግል ደስታና (ደስታ ከነበረ) መከራ አሳምረህ የምታዉቅ መሆንህን በመገንዘቤ በጣም ነው ደስ ያለኝ። የሚያስደንቀዉ ነገር በመስክ ላይ በስራ ላይ ሆነህ የሚሳየዉን ፎቶ ስመለከት አዲስ አልሆንክብኝም። በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ እንተዋወቃለን ብዬ አሰብኩ። ለነገሩ ከዚህ በላይ መተዋወቅስ ምን ፍይዳ አለዉ? ብዙ የምናዉቃቸዉ እንዳማናዉቃቸዉ ሆነዉ በመገኘታቸዉ ምነዉ ባለወቅናቸዉ አሰኝተዉናልና ነዉ።
ወድ አበራ !… የኔንም ሆነ የሌሎች መኮንኖችና ወታደሮችን የጦር ሜዳ ዉሎ መጽሃፍት ተከታትለህ ማንበብህ አልደነቀኝም። የስነ ጽሁፍ ሰዉ መሆንህ ብቻ ሳይሆን ታሪክ እያለዉ እንደሌለዉ ለሆነዉ፤ ጀግና እንዳልነበረ ሁሉ ፈሪ ተደርጎ ስለተፈረጀዉ፤ ለሀገሩ አንድነትና ዳርድንበር መከበር ለዓመታት መስዋትነት ክፍሎ ሳለ ጨፍጫፊ ተብሎ ተፈርጆና ተረግሞ ስለቀረዉ ሰራዊት ማንነት የምታዉቅ ብቻ ሳትሆን ኑሮዎን አብረህ የኖርክ የታሪክ ምስክር፤ በመሆንህ ጭምር ነዉ ። በድጋሚ ላመሰግንህ እወዳለሁ።
በእኔ አስተያየት የሰጠኽዉ ግምግማ ወደፊትም ለሚጽፉት ሶዎች ትልቅ ትምህርት የሚሆን በመሆኑ በተገኘዉ መገናኛ ብዙሃን ሁሉ ቢለቀቅ መልካም ነዉ እላለሁ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ዉስጥ መቼም የማላገኘዉ ትምህርት እንደተማርኩ ልነግርህ እወዳለሁ። ፍርሃትም ድፍረትም ሰጥቶኛል ። ግምገማህን ካነበብኩ በኋላ የፈራሁት አንተን የመሰሉ የስነጽሑፍ ሰዎች ያነበቡትን መጽሃፍ ጽፌ ለንባብ ባበቃም፣ ምን ያህል ገና እንደሆንኩና ምንስ ያህል ብዙ እንደሚቀረኝ እያሰብኩ ነዉ። ሰዉ አለማወቁን የበለጠ ሲያዉቅ ይፈራልም ይተጋልም። በሌላ በኩል ድፍረት የሰጠኝ ተግቼ እንድሰራ ግምገማህ የበለጠ የሚያበረታታኝ መሆኑ ነዉ። ለዚህ ነዉ ሁለቱንም ሆንኩ ያልኩህ።
ጊዜ ብታገኝ የእኔንም መጻፍ ብትገመግመው ደስታዉን አልችለዉም።
ሙያህን እግዚአብሄር ይባርክ
ወንድምህ ንጋቱ ቦጋለ (ሻለቃ)

(ሙሉውን ጽሑፍ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ምርኮኛ - አገሬ አዲስ
Share