ዶክተር በያን አሶባ ለዶክተር ፍቅሬ ቶሎሳ ግልጽ ደብዳቤ የላኩት መልስ (የአማርኛ ትርጉም)

ትርጉም – ይነጋል በላቸው

ዶር. በያን አሶባ

ውድ ዶክተር ፍቅሬ ቶሎሣ /ቶለሣ
(ዶ/ር በያን አሶባ)በስሜ አድራሻ የላኩት ግልጽ ደብዳቤ በበርካታ ድረ ገፆች በወጣበት ወቀት እኔ ጉዞ ላይ ነበርኩ፡፡ በዚያም ምክንያት ወዲያውኑ መልስ መስጠት በምችልበት ሁኔታ ላይ አልነበርኩም፡፡ በዚህ በምጽፍልዎ የደብዳቤዎ ምላሽ እኔን ስለሚመለከቱ ነጥቦች ብቻ አነሳለሁ፡፡ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር ስለአጠቃላዩ የደብዳቤዎ ይዘት መልስ ይሰጥዎታል ብዬ አምናለሁ፡፡
ውድ ዶክተር ፍቅሬ
አስተያየቴን መጀመር የምፈልገው በዚህ ግልፅ ደብዳቤዎ የአያትዎን ስም እንዴት ሊጨምሩ እንደፈለጉና ይህ ያልተለመደ አካሄድ ያጫረብኝን ስሜት በማስቀደም ነው፡፡ አቅም በፈቀደ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎችዎን ለመመልከት ሞክሬ ሁሉም ‹ፍቅሬ ቶሎሣ› እንደሚሉ አረጋግጫለሁ፡፡ ይህም አያትዎን ያለመጨመር የአጻጻፍ ይትበሃል እ.አ.አ በ1983 በብሬመን ዩኒቨርስቲ ለዶክትሬት ዲግሪዎ ማሟያ ያቀረቡትን ጹሑፍ ጨምሮ በሌሎች በርካታ ተከታታይ ጽሑፎችዎ አልተስተዋለም፡፡ በፌስቡክዎም የአያትዎ ስም አልተገለጸም፡፡ .እኔ እስከማውቀው ድረስ የራስዎን ስም ፍቅሬ ቶላሣ (Tolassa, not ከዚህ በፊት ይጠቀሙበት ነበር እንደሚባሉት Tolossa!) ብለው መጻፍ ብቻ ሣይሆን ‹ጂግሣ› የሚለውን የአያትዎን ስም ተጠቅመው የጻፉት በዚህ ግልጽ ደብዳቤዎ ብቻ ነው፡፡
እርስዎም እስካሁን ወደጎን ትተዋቸው እንደነበረው ሁሉ አሁን ‹ጂግሣ›ን ባሉበት እንዲያርፉ ለቀቅ እናድርጋቸውና አዘውትረው በሚጠቀሙበት ቶሎሣ/ቶለሣ በሚለው የአባትዎ ስም ላይ ትኩረታችንን እናውል፡፡ ‹ቶሎሣ› የሚለው ስም ‹ቶሎ› ከሚለው የአማርኛ ቃል ተወስዶ ኦሮምኛ እንዲመስል ‹ሣ›ን በመጨመር የተበጀ ቃል ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በሌላ በኩል ‹ቶላሣ› ከኦሮምኛው ‹ቶላ› የተገኘ እንደሆነ በርግጠኝነት ዐውቃለሁ፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ ስምዎን በሁለት መንገድ እየጻፉ ሁለት ተቃራኒ ማንነቶችን ለመላበስ መፈለግዎን መረዳት አይገድም፡፡ ይህን በማድረግ በአማራነትና በኦሮሞነት የማንነት አጥር ላይ ፊጥ ማለት ተመኝተው ከሆነ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልዎ፤ በአራዶች አነጋገር ‹ይመችዎ!›፡፡ ሊሆኑት ወይም ሊጠሩበት በሚፈልጉት ስምም ይሁን ማንነት የመጠራት መብትዎን ሙሉ በሙሉ አከብራለሁ፡፡
የኔ ጥያቄ ይሄውልዎ፡- እኔ የርስዎን የፈለጉትን የመሆንና በፈለጉት የመጠራት መብት ሳከብርልዎ ለኔስ ይህን መብት ለምን ይነፍጉኛል? ስሜ Bayyanaa Suba አይደለም፡፡ ስሜን ‹Beyan Asoba› ከሚለው ውጪ በሌላ መልክ በፍጹም ጽፌ አላውቅም፡፡ ይህ የሰጡኝ አዲስ ስያሜ አባል የሆንኩበትን የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባርን በአንድ ወይ በሌላ መልክ ለመንካት ካልሆነ በስተቀር እኔን በተመለከተ ያወጡልኝ ስም ሊሆን ይችላል ብዬ መቀበል ያቅተኛል፡፡ በግልጽ እንደሚገባኝ ለፖለቲካዊ ዓላማዎ ሲሉ ይህን አዲስ ስም ፈልስፈው ለኔ የሰጡኝ ይመስለኛል፡፡
ለፍጡሮቻቸው ስም ማውጣት የሚቻላቸው ፈጣሪዎች ብቻ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ወላጆች ለልጆቻቸው የተለያዩ ስሞችን እንደሚያወጡ ሁሉ የመኪና ፋብሪካዎችም ለምርቶቻቸው የተለያዩ ስሞችን ይሰጣሉ፡፡
እንደመጥፎ ዕድል ሆኖ ለኛ ለኦሮሞ ሴቶችና ወንዶች ልጆች የስቃይና የውርደት ምክንያት ሆኖ አበሣና መከራ ያሳየን የነበረው የሕይወት መሪር ተሞክሯችን ስማችንን እንድንቀይር ትምክህተኞች (አማሮች?) ያደርጉብን የነበረው ጫና ወይም የማስገደድ ተግባር ነው፡፡ ኦሮሞ የሚለው ብሔራዊ መጠሪያችን ከማንኛውም መዝገብ ተፍቆ በርካታ አንቋሻሽ የፍካሬ ትርጉሞች በተለጣጠፉለት ስያሜ እንድንጠራ ተገድደን ነበር፡፡ ተማሪ ልጆቻችን ሳይቀሩ የተዋጣለት ኢትዮጵያዊ መሆን ይችሉ ዘንድ ስሞቻቸውን (ወደ አማራ ስሞች) እንዲቀይሩ በመምህሮቻቸው የሚገደዱበት ሁኔታም ነበር፡፡
በዚያች ሀገር ውስጥ ዋናው የፖለቲካ ማጠንጠኛ ግለሰቦች በቅድሚያ ኦሮሞነታቸውን፣ ሲዳማነታቸውን፣ ወላይታነታቸውን፣ ከምባታነታቸውን፣ ሃዲያነታቸውን ወዘተ. እንዲገድሉና በውጤቱም ኢትዮጵያዊ የሚባል የጋራ ማንነት መገለጫ እንዲኖራቸው ጥረት ማድረግ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ኦሮሞነትና ኢትዮጵያዊነት አብረው ሊሄዱ ካልቻሉ ምርጫው ሁለት ነው፤ አንድም የእርስዎን ኢትዮጵያዊነት ባፍንጫችን ይውጣ ብለን መተው፣ አለበለዚያም በነበረው አካሄድ ነጻነትን ተነጥቀን እንደጥንቱ እያለቀስንና እየተሰቃየን መኖር፡፡
ለእርስዎና መሰሎችዎ በሚገባ ግልጥ አድርጌ ልነግራችሁ የምፈልገው አንድ ነገር አለኝ፡፡ ያም ኦሮሞዎች ማንነታቸውን ክደው በሚጣልባቸው የራሳቸው ያልሆነ ማንነት የሚንበረከኩበት ጊዜ አልፏል ወደፊትም አይመጣም፤ በዚህ ዕርማችሁን አውጡ፡፡ ኦሮሞነትን የሚጋፋ ኢትዮጵያዊነት አንቀበልም፤ ይህ ኢትዮጵያን ከኦሮሞ የማስቀደም አካሄድ እስካልቀረ ድረስም ትግላችን ይቀጥላል፡፡ ምርጫው የእርስዎና የቢጤዎችዎ ነው፡፡ እኛን ከነኦሮሞነት ማንነታችንና ከሌሎች ተዛማጅ መብቶቻችን ሙሉ በሙሉ መከበር ጋር ትቀበላላችሁ ወይም ከአደንቋሪ የኢትዮጵያዊነት ስብከታችሁና ከኢትዮጵያ አንድነታችሁ ጋር ጥንቅር ብላችሁ ልትቀሩ ትችላላችሁ፡፡ በኦሮሞዎች መቃብር ላይ፣ በሲዳማዎች መቃብር ላይ፣ በወላይታዎች መቃብር ላይ፣ በከምባታዎች መቃብር ላይ፣ በሃዲያዎች መቃብር ላይ፣ ወዘተ. የኢትዮጵያን አንድነት ለመገንባት ሲቋምጡ አንድ ዓይነት የሞራል ጉድለት አይታየዎትም ይሆን? ይህ ዓይነቱ ጉዞ መጨረሻው የማያምርና ከቆመለት ዓላማ የተለዬ መጥፎ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል መገንዘብ እንዴት አቃተዎት? ይህ ዓይነቱ ኢምክንያታዊና ኢሞራላዊ የጥፋት መንገድ በመጨረሻው ስክነትንና ማስተዋልን ተላብሶ የሁሉንም በግዛቲቷ የሚኖሩ ወገኖች ፍላጎት ባማከለ ሁኔታ ሁሉንም የሚወክል ማንነት እንደሚያብብ ታላቅ ተስፋ አለኝ፡፡
በመጨረሻም በዚህ ራስ ምታት የሚለቅ አስቸጋሪ ጉዳይ ዙሪያ ይህ የአጸፋ መልሴ የመጀመሪያየም የመጨረሻየም እንደሆነ ልገልጽልዎ እወዳለሁ፡፡
በያን ኤች አሶባ (Beyan H. Asoba 5/29/13)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሃይማኖታችን የደም ስራችን ናት

ከ‹ተርጓሚው› የተሰጠ አጭር አስተያየት
1. በአማርኛ ለተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ በእንግሊዝኛ መልስ መጻፍ ምን ማለት ነው? ዶክተሩ ከጋና ነው ወይንስ ከእንግሊዝ የተገኙት? እዚሁ ከቅኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ውስጥ አልተፈጠሩ ይሆን? (ኢሣይያስና መለስ ነፍሳችሁ አይማር – ጥቁር ውሻም ውለዱ!) ዶክተር በያን ከአማርኛና ከእንግሊዝኛ የትኛውን አጣርተው ሊናገሩ ዌም ሊጽፉበት እንደሚችሉ በእንግሊዝኛ በጻፉት መልሳቸው በውል ተረድቻለሁ፤ ታዲያ አማርኛ ላይ ያላቸውን ጥላቻ ለመግለጽ አውሮፓና አሜሪካ ድረስ ሄደው ለምን ትዝብት ውስጥ ይገባሉ?

2. የኢሣት የተለያዩ ባንዲራዎችን በኢትዮጵያ ስም ማስተናገድ ምን ማለት ነው? በጣም ይታሰብበት፤ በልክ ያልተያዘ ፍቅርና ጥላቻ መዘዝ አለው፡፡ ስንወድም ስንጠላም፤ ስንቀርብም ስንርቅም በምክንያት ይሁን እንጂ በስሜት አይሁን፡፡ የኢትዮጵያ ባንዲራ እንኳንስ ለአንድ ሕዝብ ለመላው ዓለም በቅቷል – የሌሎች ሀገራትን በተለይም የአፍሪካውያንን ባንዲራዎች ተመልከቱ፡፡ እኛ የምንጸየፋትን አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት ባንዲራ ከእኛ እየኮረጁ በተለያየ አቀማመጥ ይጠቀሙባታል፤ ነፈዞች ደግሞ የገዛ ባሏን የጎዳች መስሏት ገላዋን በጋሬጣ እንደሸነተረችው ሞኝ ሚስት እየሆኑ ያስቁን ይዘዋል፡፡ አትለማመጡዋቸው፤ ይልቁንስ የራሳችንን ሥራ እንሥራ፤ እውነትና ግልጽነት ያልተገባ ይሉኝታንና ፍርሀትን ያስወግዳሉ፡፡ እውነቱን ልባችን እያወቀው አንደበታችን በሀሰት ማባበልን ይተው፡፡ ለየትኛው ጊዜ…
የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልኝና በዚህ ጉዳይ ሰፋ ባለ ሁኔታ እመጣበታለሁ፡፡ በየወንዙ እንደሚማማል የማይተማን ጓደኛ ለማያዛልቅ ስትራቴጂ አንድ ጠረጴዛ ዙሪያ በአካል የተቀመጡ መስለው በምናብ ግን ተራርቀው መቀመጥ የሚያዋጣ አይደለም፡፡ እያፈረሱ ግንባታ የለም፤ እየጠሉ አንድነት የለም፤ የሚጸየፉህን ልመናና ልምምጥ የለም፡፡ የደነዘ አስተሳሰብ በምንም ዓይነት ሣሙና ቢታጠብ አይነጻም፡ ዐውቆ የተደበቀን ቢጠሩት አይሰማም፡፡ በጠላት ተቀፍቅፎ በበጎች ጋጣ ውስጥ የመሸገ ቀበሮና ተኩላ በልምምጥና እውነትን በመሸፈን በሚደረግ ልመና በረቱን ለቅቆ አይወጣም፤ የነገ ሰው ይበለን፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዶክተር ዐቢይ እርምጃ እንዳይወስዱ ምን እየያዛቸው ይሆን? - ዋቅወያ ነመራ

33 Comments

  1. Hey Freinds,
    Here another debtera No.3. came. Keep your Ethiopia in the Museum. Use your dirty badira to wrap tobacco (korendie) and smoke it.

  2. Dr Beyan Asoba I am sorry to say but you are talking just nonsense… የኦሮሞ ህዝብ አድዋ ድረስ በመሄድ ደሙን አፍሶ አጥንቱን ከስክሶ ካኖራት ከራሱ ቤት ከሆነችው በሰፊዋ ኢትዮጵያ ውስጥ ከወንድሞቹ ጋር በሳሎን ውስጥ እንዳይኖር ጠባቦቹ ኦነጎች የኦሮሞን ህዝብ ተገንጥለህ ሰላም በሌለበት ቁም ሳጥን ውስጥ ካልኖርክ እያሉ የሚጨቀጭቁት መቸም አይሳካላቸውም:: ኦነግ 150 አመት ታግያለሁ ይላል ግን እሽ የታለ ውጠቱ? እንደተማረ ሰው የወደፊት የህዝብን ጥቅም ያላስቀደመው የኦነግ አመራር ይህን ድንቁርናውን እንደተሸከመ ይኖራታል እንጂ እኛ የኢትዮጵያ ህዝቦች በዚህ የደከመ አስተሳሰቡ ኦነግ ከዋሽንግተን መጥቶ እንዲበጠብጠን መቸም አንፈቅድለትም::

    • Adwa dires hedo le Minilik ye tewagawu Oromo wedo sayhon meretu be Minilik serawit endaywesedi bet ferto new. Be wektu Oromo be Miniik serawit kutitir sir neberechi. Ende ahunu Woyane malet new.

  3. በጣም የገረምኝ እነዚህ የኦሮሞ ፖለቲከኞች የተለየ ሃሳብ ከመጣ ኦሮሞ አደለህም የሚሉት ነገር ነው፣ይህንንም ነገር ዶ/ር በየነ አሶባ ሲጠቀሙበት ማየት በጣም ያሳዝናል:: እዚ ላይ ለ ዶ/ር በየነ አሶባ መልክት ኧለኝ ቶሎሳ ብሎ የአማራ ስም የለም፣ ቶሎ ከሚለው ቃል የተወሰደ ነው ብለህ ዶ/ር ፍቅሪን ኧማራ ለማረግ የሞከሩት ኧልተሳካም ሌላ ይሞክሩ:: እኔ ተነስቸ ኦሮሞ ነኝ ብል ማንም ለከለክለኝ ኧይገባም ማን ነህ ኧንተ ዘር መዳቢ የኧደረግህ?
    ኧንድ ጓደኛ ነበረኝ university ተማሪ እያለሁ ኧንድ ቀን የኦሮሞ ተወላጆች ጋር ይቀርብና ሊኧናግር ሲሞክር ኧንተ እኮ ኦሮሞ ኧደለህም ኧሉት፣ ምነው ሲላቸው ስምህ መሃመድ ነው፣ ነገሩ ያልገባው ልጅ ምን ችግር ኧለው እና ሲል ኦሮሞ እስላም ኧይሆንም ኧሉት::
    እነዚህ ተማርን የሚሉ እንዲሁም በ ኧሜሪካና ኧውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያኖች ከኧካባቢኧቸው ኧለመማራቸው በጣም ከሚያሳዝነኝ ነገር ኧንዱ ነው ፣ በሰሞኑ ኧቶ ኦባማ (president Obama) ስለ ጓንታናሞ መዘጋት ሊናገሩ ኧንዲት ግለሰብ ተቃውሞዋን ኧሰማች ኧቶ ኦባማ በረጋ ኧንደበት እባክሽን ተናግሪ ልጨርስ፣ በመጨረሻም ሲመረው ይመስላል የመናገር መብት ቢኖርሽም ማድመጥ ኧለብሽ ሲሉ ተሰምተዋል:: በመጨረሻም ተይዛ እስከምትመጣ ድረስ ጠብቀው በሃሳቧ እስማማለሁ ምንም ኧብዛኛው የአለችውን ባልደግፍም በማለት ቀጠሉ( ኧወይ መለስ ቢሆን ???)::
    በ ኧሜሪካና ኧውሮፓ ፖለቲከኞች የተለያየ ፓርቲ ኧባል ሆነው ድብድብ ቀረሽ ክርክር ሲከራከሩ ቆይተው ኧብረው በሰላም ይሂዳሉ :: እኛ ኧገር እንደዚህ የለም::
    መቸ ይሆን ተስማምተን መወያየት የምንጀምረው?
    መቸ ይሆን ሰውን ከሰው ሃሳብ ለይትን የምናየው???
    መቸ ይሆን በሃሳብ አለመግባባት ጠላት የማያደርገን ???
    እባካችሁ ለኢትዮጵያ ህዝብ እናስብ !!!!

    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !!!
    Like · · Promote

    • @Z_Habesha

      An Oromo who are acting as a Habesha is not a full Oromo; he/she is a banda. An Oromo who is ashamed of using its language and exercising its culture is a banda. What matters is not only the blood/genes/. In fact no one makes DNA test to know whether sb is Oromo or not. The only test is the behaviour he/she is showing towards the oromo cause.

  4. ወትሮስ ከበያን ምን ይጠበቃል። እዛው የስደት ማኪያቶውን ሲያንጫልጥ እኛ ሀገራችንን እንገነባለን። በጥላቻ ፖለቲካው ታንቆ ሲሞት በድሪቶው ጠቅልላን እንቀብረዋለን ከነ ርካሽ አቀቅሙ። ዶክተር ፍቅሬ ቶሎሳ የኛ ኢትዮጵያዊ ሁላችንም ከጎንህ ነን።

  5. Ato Yinegal,
    Unless you live on another planet, you know pretty well that Dr. Beyan or anybody else could write in any language of his/her choice. Or could carry any flag of his/her choice. In our country Ethiopia diehard idiotic individuals like yourself remain a liability and albatross that destroys any reconciliation that we need very badly. I assume you live in the West and look at how diverse group of people who come to the West remain proud of their heritage, language and culture even after taking US or European countries citizenship. No one bothers them since it is their democratic right. So if say you as an Amhara could fly Ethiopian flag, teach your children Amharic in America/Europe, why can’t other non- Amhara Ethiopians use any other language of their choice or fly a flag that they believe symbolizes their aspirations. I’m not an Oromo but I believe that Oromos just like any other Ethiopians have the right to be free to advance whatever is right for them; let’s stop pontificating and preaching to non-Amhara Ethiopians about Ethiopian flag or Amharic. Ethiopia is a multi-ethnic and multicultural country that should recognise and encourage diversity if it is to survive.
    Long live Ethiopia that is for all its diverse peoples.
    The hell with Ethiopia of the Chauvinist Amharas

  6. D/r bayyanna betam betam yemiyasafrina ymiyasazin tuhuf new silewnet kehone yetemaru aymesilegnim ketemarum yetemarutin erestewtal min yahil zeregna enidehonu yerekese tuhuf enidetafu melisew yanibibut yasafral lezawm D/r negn kemil sew asibubet eriswo enikuwan sew limeru betesebwonim yemimeru aymeslegnm ymlagn lebetesebwo

    • Minu new betam yasaferesh? Esti nigerin etiye Ayelech. Bado chachata meftihe aydelem. Mikiniyatawi hugn.

  7. የቀበናው
    ይድረስ ለይነጋል በላቸው
    በመጀመሪያ የዶ/ር በያን አሶባን የመልስ ፅሁፍ ከኢንግሊዘኛ ወደ አማርኛ በመተርጎምህ አመሰግንሃለሁ። ይኹን እንጂ የተረጎምከውንም ሆን ኦሪጅናል ፅሁፉን በደንብ ያነበብከው ወይም የተረዳኸው አልመሰለኝም። አለበለዚያ አትዮዽያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ በአግባቡ የተረዳኸው አየደለም። በመጀመሪያ ደረጀ አትዮዽያ ውስጥ ያሉ ሠዎች በሙሉ አማርኛ መናገር ወይም መፃፍ ይችላሉ ብሎ ማስብ በጣም የጠበብ አስተሳሰብ ነው። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አማርኛ መናገር አና መጻፍ ሁልት የተለያዮ ነገሮች ናቸው። በመጨረሻም አንተም ሆንክ ብጤዎችህ ልትገነዘቡት የሚገባው ነገር አናንት የምትፈልጓት ኢትዮዽያ (አንድ ሀገር፥ አንድ ቛንቛ፤ አንድ ሐይማኖት፤ አንድ በንዲራ) ላትመለስ ጠፍታልች። ለዚያች ሀገር አና ሕዝብ የሚበጀ ነገር ቢኖር አሁን ከለንበት ግዜ ጋር የሚጣጣም አስተሳስብ እና ከግዜው ጋር የሚሄድ የአገዛዝ ስርዓት ብቻ ነው። አሁን አንደሚታየው ለዚያች ሀገር መፈራረስ እና ለህዝቦቿ መጐሳቆል ምክንያት እየሆን ያላችሁት በዋናነት አሁን በስልጣን ላይ ያሉት ጥቂት የትግራይ ልጆች እና ከአረጀ አስተሳሰብ አንላቀቅም ብሎ የሙጥኝ ያለው ጥቂት የአማራ ተወላጅ የሆነው ተቀዋሚ ተብዬው ማህበረሰብ ነው። የሚገርመው ነገር ይኽ ጥቂት የአማራ ተወላጅ የሆነው ተቀዋሚ ተብዬ፤ የኢትዮዽያ ህዝብ ዐይንና ጆሮ ነኝ የሚለውን ኢሳትን እንኳን ከወቅታዊ የኢትዮዽያ ሁኔታ ጋር የተገናኘ ስራ እንዲሰራ እንኳን አለማበረታታት ዋናው ተግባራቸው መሆኑ ነው። ለዚያች ሀገር የሚበጀው ነገር ሁላችንም ከወቅታዊው ሁኔታ ጋር እራሳችንን ማጣጣም እና ግዜው የሚፈልገውን የአደረጃጀት ሁኔታ ተከትለን ህዝባችንን ከሌሎች ህዝቦች ጋራ በጋራ በማታገል አንድ የሁሉም ሀገር የሆነች ኢትዮዽያን በአዲስ መልኩ መመስርት ብቻ ነው። አለበለዚያ ሁላችትም ለዚያች ሀገር መፈረስ የራሳችንን ድርሻ አየተወጣን ነው ማለት ነው።
    የቀበናው።

    • @Ye Kebenaw Dereje

      Your comment is very good. It reconciles the two camps: unionist vs separatist. The multifaceted problems the empire is facing needs such mentality. God bless U bro!

    • ”ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሰዎች በሙሉ አማርኛ መናገር ወይም መጻፍ ይችላሉ ብሎ ማሰብ በጣም የጠበበ አስተሳሰብ ነው” ብለህ ለጸሃፊው መልስ ሰጥተሃል:: በመጀመሪያ ደረጃ ጸሃፊው እንደዚህ ብሎ አላሰበም (በተጻፈው ጽሁፍ አንጻር ካየን):: በልቡ ውስጥ ያለውን ደግሞ ከራሱና ከፈጣሪ በቀር ማንም አያውቅም:: እንደው እንደዛ ብሎ ቢያስብ እንኳን (ልብ በል አላሰብም) ግን ቢያስብ እንኳን አንተና ዶ/ር በያን ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሰዎች ከአማርኛ ይልቅ እንግሊዝኛ ይችላሉ ብላችሁ ካሰባችሁት 100% ይሻላል:: ማብራሪያ የሚያስፈልገው አይመስለኝም:: ባጭሩ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ አማርኛ መናገርም ማንበብም ይችላል:: ኦሮምኛም እንዲሁ:: ብዙዎቹ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችም የማርኛና የኦሮምኛን ያክል አይሁን እንጂ ከእንግሊዝኛ በተሻለ የሚነገሩ ጥቂት አይደለም::

  8. Yinegal Belachew,

    Beyan Assoba is rejecting your language. Instead he used a neutral language to convey his message. None of what the Neftegnas nor their errand boys like Fikre Tolessa do change the fact that the language issue you want to portray is going to change the direction we are on. He did not answer in Afan oromo. I wish he did that. We’ve known Yinegal is waiting for the rise of the day when Amhara domination will revive. That is a dream in the sky.

  9. betam yemyasazin ..bizo ye Oromo hizb yalekew bendenzh aynet be kureja dr. yehone kehadi aynet bemewenabed new ..endenezh aynetoch tikit teketayoch linorachew ychilal,gin talakon ye Oromo hizb liwekilo aychilom .enem and Ethiopiawi Oromo negn

    • What kind of flamoboiant idea is Beyan Asoba wrote down about Oromo . Did he realy know the history of Oromo in deapth more than Fikre Tollosa ? He looks like a wolf in sheeps . The other thing what surprised me is why those people write their educational title in their article . Do they think they get respection for that ? Never

  10. Thank you Mr.Yengal Belachew for UR transilation, and UR comment too. Beyan,lencho, ena lelochem cheger alebachew kelegenetachew jemero, E/R yemarachew

    • @Dereje
      Do not mention the name of God in vain. Please be objective. Argue logically and with evidence. What are your justifications to tarnish the image of the Oromo politicians whose names U have mentioned above?

  11. Dr Fikere , May God bless you. You have given the answer he deserves to this so called Oromo by the name Beyan. I don’t think he represents, by any means the millions of Oromos (ethiopians,whether he likes it or not)who live harmoniously with their brothers in Ethiopia. On the name of the people,so called intellectuals cannot manupilate the majority. Let them stay abroad eating their cakes. What is sad is they are so blinded by hatrad,they couldn’t see the naked truth. Ethiopia will prevail. Oromos with their brothers and sisters Ethiopians will live forever.

  12. Yinegal,

    I don’t belive for a moment that you will see the day light you are dreaming of. You have allowed some Amhara dogs who cannot communicate in English to use their Amharic language to tarnish an Oromo scholar and the oromo people on this page while you deny the same right of using Afan Oromo by Oromo scholars. Shame on you. You are sitting in the west and planning a “solution for Oromos” in Ethiopia. What a joker. Do you really know the Oromo people you are talking about. Yes, Dr. Beyan and his group gave you a window by declaring agents of democratic change for Ethiopia knowing well that Moresh, Gasha, AAPO and the likes are working hard to turn Ethiopia into an Amhara enclave once more. It was a strategic mistake again. Amharas do not know compromise. History proves it. Their poltical leaders are stone-headed. Eritrea left the country because the Amhara leaders could not see what was coming. They are blind. It is hard to lead a blind person who does not know or accept his blindness. He would rather fall into the dish and die. Our journey is filled with the blood of thousands of Oromo youth that are singing for freedom. There is no other way. The train is moving. Yinegal is dreaming that the Oromo train stopped some where because Lenco and Beyan decided to change their course. How fool can they be. The Amharas are happy since they got an errand boy, Fikre Tolessa. Fikre was never part of us. He denied his self long time ago. We never knew him as an Oromo. He cannot speak for the Oromo people, but he can speak for his masters. But I do not know why he serves them as a middle man.

  13. Dr beyan astewayna hodesefi slehona newe kenante gar yawerawe, weyem bedenb ayawqachu yhonale ena ena abzagnawe ye oromo hzeb selemiyawqachu Ethiopia yemteluwaten sem Amara ena ortodox becha newe yemweklew, woyane le hezboch be quna sefro yesetaten mebet enkuan enante bezabachewe belachu ye dero seratachehun lememeles stasebu Gonder ena kefil gojamen atabachu bechachehun letqeru newe.

  14. This is the realty that the OLF leaders were living in the past 40 years- preaching hatredness and living in illusion, nothing else. Let alone liberate the oromo pople, they can not liberate them selves from mind enslavement. Why this guy has resorted to attack Fikre Tolossa than focus on the substance of his writing is becuase he does not know the history of the Oromo people nor has the ability to respond to the issue at hand or defend his cause with evidence in a civilized manner. He might be good at dislike and animosity to the Amhara and Amharic speakers, but poor at defending the cause he claims stands for though he stayed in the struggle as much as his years. Who is he after all deciding one as Oromo and the other not. Is becoming an Oromo decided by his and his few anti-Ethiopia cronies ill will or by who we know we are or by the whole of the Ethiopian Oromo people. Is he the giver and taker of the identity of other Oromos who do not agree with his ill will ideas?

    In what ever Oromo political names these old school OLF guys comes in, they can’t be free of thier illusion and animosity to others.

  15. FROM GETACHEW REDA;
    Dear Dr. Yingeal Belachew;

    As always, you are one of the greatest bright Ethiopian who argued efficiently in the current Ethiopian politics. Your writings always gave me so much knowledge. Your Amharic writing is fluent, your argument is best. These OLF thugs are completely bankrupted ideologically.

    Your Beyan’s translation to Amharic gives so many of us the clear intention what Beyan thinks in his mind about Ethiopia. Oromo comes first Tigre comes first is what narrow nationalist always think. This is what Beyan is telling us. This sis what Fuhrer /Nazi believe “white first”! if white can’t come first before anything, let German destroyed is what the Nazi ideology teaches. Beyan and his likes or TPLF and their likes always preach their people first. They are the Ethiopian Fuhrer ideologue.

    They want us to suffer from one Fuhrer to another Fuhrer by continuing preaching the ideology of hate. The yolk of hate must stop once for all in Ethiopia. Let these thugs live where ever they are living now and let them not spread their hate to Ethiopia. There is enough hate out there thy TPLF and their OLF seed it. These are completely savages of the 16Th Century narrow thinkers with a modern PhD education. They stopped thinking like human. They think like animal. Mine first, let the rest go second. Their mirror neuron stopped seeing dual. They only see their people, they do not bother to see if there are other humans surrounding them who also are part of their flesh and soul as citizen of a one country.

    Thanks Dr. Yinegal Belachew. Yes, the sun will shine with Ethiopia shining again under the burial of hate mongers. Thanks for that beautiful translation that can help us to save it for the record. Thanks Getachew Reda

  16. Yinegal, the English expert. While you were rushing to belittle Dr. Beyan’s ‘deficiency’ in English you forgot to correct your own erroneous translation. Dr Beyan wrote ‘I would not have recognized that this new name actually refers to me if it were not used in context of commenting on the Oromo Democratic Front, of which I am a member.’ your translation is way off. Unfortunately I can’t copy your translation here because I don’t have the software, which may be one among many possible reasons Dr. Beyan didn’t use Amharic for the response. Yerasuan semay seqla wusha be fiyel chira tisiqalech yemilut aynet.

  17. From Getachew Reda
    To Mul’ata
    Did you see how your hate exposed here? German Nazi used to hate the Jew literature, scripts and hate and kill if any German hold book written in Hebrew. Similarly, you seemed to have similar hate to Amharic language, because you do not have software. You do not need soft ware. All you need to do ids download it freely from any Ethiopian media. You knew that, You do not even want to just do to copy and paste it – because you think Amharic is live Amhara coming in contact to your computer as human? wheeeew! This is getting bad on those elements head. Don’t you think you are behind so many information what is written in Amharic besides on the Habesha websites that present and post on words format? You and Eritreans are so ignorant of Ethiopian news, books, magazines what they have in them. I have a friend who is highly educated Eritrean- when he told me how ignorant they are on news and books written in Amharic, because they do not want to read Amharic for reason they hate Amharic as enemy language- he simply referred them as “first grade racists”

    You hate to read Amharic and you do not want to download Amharic software that is there for all of you to use it for free.

    Believe me if I knew OromiNnga, I could have download software and read books and so forth. But, since you are all into Latin, we read many of them what you guys write in English. But us, you need to deal with our language and download free. If not leave with your hate for ever. your option is to go back and download Geez for free and show us what you want to show us. Over all, it is not your fault Lencho taught you to hate Amharic language. He responses in English when the media people talks to him and interviewed him in Amharic- regardless he knew Amharic better than English. How pathetic and backward mind these elements possessed -it is beyond me. By the way, That is the only error you find from Dr.Yinegal Belachew? That means he did a good job with his final remark on the Beyan’s remark. Thanks Getachew Reda

  18. I donot want to comment on individual issues. The only thing that I understood is the Amhara’s and thosa whose mind has been colonized by this thinking have always one dream: one Ethiopia, One language, One culture, one flag. Please go to developed countries see how they have respect for all their people. If you go to Singapore, where the official language is English, Everybody is obliged to learn his mother tongue first in primary school: Malay, Chinese, and Hindu. Then, they believe as Singaporean. But you are telling/dictating everybody not to mention who he is. You have ruled this country for more than 100 years and you ended up with poverty hit people. Your thinking was to eat fatty food, drink tej and sing about Ethiopia. What did you bring for Ethiopian people? Even what did you bring for the poor Amhara whom you are boasting. Please, sit a while and think for a second. Donot rush to blame somebody and make hasty generalization. There are a lot of Ethiopians who cannot express themselves in Amharic. You are expecting a Somali person to write in Amharic like somebody from Gojjam? You want a person from Gambella region to write using all Amharic proverbs and Amharic words to express his idea? When you say Ethiopia, remember you are always thinking about all Ethiopians living in the territory of Ethiopia. I know when I write this letter, you will rush to judge that I am Woyane or its cadre. I am not and even if I am, that is not shame.

  19. በል ወዲያ ደግሞ ስለወላይታ ከንባታ ወዘተ ሊያወራ ዪፈልግል እንዴ አንድ የፖለቲካ መሪ ስም ጠርቶ አንድን ዘር አይዘልፍም ፡ታዋቂ የሆነ ሌላ ኢትዮጵያዊ በድፍረት ሲሳደብ ወይም ሲዘልፍ አልታየም፡ደግሞ ለቀሪ ተከታዮቻችሁ ፍቅርን ጨዋነትን እውነትን አስተምሩዋቸው

  20. Getachew Reda

    you out of all people talk about hate? Come on man? Every one knows that you hate Oromo, probably more than the Germans used to hate Jews? Why? I don’t know, but you have demonstrated that time and again.

    I do not hate Amharic at all sir; it’s a language I grew up speaking and a language I learnt in schools. I speak more and better Amharic than Afan Oromo or English. I have more Amhara friends than any other nationals, who unfortunately speak only Amharic, so I use it to communicate with them. On the contrary I write better English than Amharic or Afan Oromo; simple. When it comes to reading I read all languages but prefer English more than the remaining two. And I’m pretty sure I’m not alone in this category.

    Now how is it then that you conclude that I or other Oromos hate Amharic? How many Oromos, who grew up in cities, have you met and talked to? Was my last sentence not Amharic for you? Or you didn’t read it? Let me copy it again because I think it applies to you too – yerasuan semay seqla wusha befiyel tisikalech. Yemanew denez benatachihu?

  21. i am oromo and so what ? we live 21 century,what talking about?oromo tigray ,amara all talk shit!, we are all one ethiopia pired.

  22. @Kiekie

    kkkkkkkkkkk!
    Is 21c time when nations and nationalities become extinict and countries flourish?

Comments are closed.

Share