May 22, 2013
2 mins read

(IMF) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 እንደሚወርድ ተነበየ

IMF LOGO KNN

በፀጋው መላኩ

አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሰሞኑን የየሀገራቱን የኢኮኖሚ አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት እ.ኤ.አ በ2014 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 የሚወርድ መሆኑን አስታወቀ።
የገንዘብ ድርጅቱ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያም ሆነ አፈፃጸም ከመንግስት ጋር የሚለያይ ሲሆን የኢትዮጵያን መንግስት የባለሁለት አሀዝ እድገትን ባለአንድ አሀዝ እድገት መሆኑን ሲገልፅ ቆይቷል። እ.ኤ.አ በ2011/12 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሁለት አሀዝ እድገትን የሚያስመዘግብ መሆኑን በገለፀበት ወቅት የገንዘብ ድርጅቱ በበኩሉ እድገቱ ሰባት በመቶ እንደሚሆን በትንበያው ያስቀመጠበት ሁኔታ ነበር።
የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባለፈው የካቲት ወር በለቀቀው መረጃ የኢኮኖሚ እድገቱን ቀመር ለመስራት ቀደም ሲል ሲጠቀምበት የነበረውን ብሄራዊ የአካውንቲግ ሲስተም በተሻሻለ የሂሳብ ስሌት እንዲቀየር መደረጉን በመግለፅ ብሔራዊውን የኢኮኖሚ እድገት መጠን ወደ 8 ነጥብ 5 በመቶ ያወረደበት ሁኔታ ነበር። በዚህም ወቅት የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ6 ነጥብ 5 በመቶ እድገትና የኢትዮጵያ መንግስት የእድገት ቀመር ቢቀራረብም ሰሞኑን የወጣው የገንዘብ ድርጅቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ ደግሞ የቀጣዩን ዓመት እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 በመቶ አውርዶታል። የኢትዮጵያ መንግስት ለተከታታይ ዓመታት የባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት ሲያስመዘገብ መቆየቱን ሲገልፅ የቆየ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ነዳጅ አምራች ካልሆኑ ሀገራት መካከል ከፍተኛ እድገት እያስመዘገበ ነው ተብሎ ሲጠቀስ ቆይቷል።n

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የሜይ 22 ዕትም

Addis Ababa
Previous Story

የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15 አመራሩን አገደ

Next Story

በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ ሳንቲም መቀነሱ አነጋጋሪ እየሆነ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop