May 22, 2013
2 mins read

(IMF) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 እንደሚወርድ ተነበየ

በፀጋው መላኩ

አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሰሞኑን የየሀገራቱን የኢኮኖሚ አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት እ.ኤ.አ በ2014 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 የሚወርድ መሆኑን አስታወቀ።
የገንዘብ ድርጅቱ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያም ሆነ አፈፃጸም ከመንግስት ጋር የሚለያይ ሲሆን የኢትዮጵያን መንግስት የባለሁለት አሀዝ እድገትን ባለአንድ አሀዝ እድገት መሆኑን ሲገልፅ ቆይቷል። እ.ኤ.አ በ2011/12 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሁለት አሀዝ እድገትን የሚያስመዘግብ መሆኑን በገለፀበት ወቅት የገንዘብ ድርጅቱ በበኩሉ እድገቱ ሰባት በመቶ እንደሚሆን በትንበያው ያስቀመጠበት ሁኔታ ነበር።
የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባለፈው የካቲት ወር በለቀቀው መረጃ የኢኮኖሚ እድገቱን ቀመር ለመስራት ቀደም ሲል ሲጠቀምበት የነበረውን ብሄራዊ የአካውንቲግ ሲስተም በተሻሻለ የሂሳብ ስሌት እንዲቀየር መደረጉን በመግለፅ ብሔራዊውን የኢኮኖሚ እድገት መጠን ወደ 8 ነጥብ 5 በመቶ ያወረደበት ሁኔታ ነበር። በዚህም ወቅት የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ6 ነጥብ 5 በመቶ እድገትና የኢትዮጵያ መንግስት የእድገት ቀመር ቢቀራረብም ሰሞኑን የወጣው የገንዘብ ድርጅቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ ደግሞ የቀጣዩን ዓመት እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 በመቶ አውርዶታል። የኢትዮጵያ መንግስት ለተከታታይ ዓመታት የባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት ሲያስመዘገብ መቆየቱን ሲገልፅ የቆየ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ነዳጅ አምራች ካልሆኑ ሀገራት መካከል ከፍተኛ እድገት እያስመዘገበ ነው ተብሎ ሲጠቀስ ቆይቷል።n

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የሜይ 22 ዕትም

Addis Ababa
Previous Story

የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15 አመራሩን አገደ

Next Story

በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ ሳንቲም መቀነሱ አነጋጋሪ እየሆነ ነው

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop