May 10, 2013
2 mins read

ዴቪድ ሞይስ ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን ተኩ

fergusen davids moyes

አብርሃም አያሌው

ማንችስተር ዩናይትድ ስኮትላን ዳዊውን ዴቪድ ሞይስን የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ምትክ አድርጐ ሰየመ።
የቢቢሲ ዘገባ እንዳ መለከተው የ50 ዓመቱ ዴቪድ ሞይስ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ዓመታት ክለቡን እንዲያሰ ለጥኑ ተቀጥረዋል።
ሞይስ የኤቨርተን ክለብን እ.ኤ.አ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ላለፋት 11 ዓመታት አሰልጥነዋል።
ያልተጠበቀውን ከአሠልጣኝነት የመሰናበት ዜና ከትናንት በስቲያ ይፋ ያደረጉት የ71 ዓመቱ ሰር አሌክስ «በዴቪድ ሞይስ ሁላችንም ያለልዩነት ተስማምተናል» ሲሉ ተናግረዋል።
«ዩናይትድን ሊያሰለጥን የሚገባው አንድ አሠልጣኝ ሊያሟላው የሚገባው ብቃት ሁሉ ከሞይስ ዘንድ አለ» ሲሉም ተሰናባቹ አሰልጣኝ አዲሱን የኦልድ ትራፎርድ መሪ አሞካ ሽተዋል።
በክለቡ ቦርድ የተሾ ሙት ሞይስ በበኩ ላቸው «ይህ ታላቅ ክብር ነው፤ ሻምፒዮን ቡድንን ለማሰል ጠን በታላቅ ሰው ተመ ራጭ መሆን ያስደ ስታል፤ ሥራው እንደሚ ከብድ አውቃለሁ ፤ ያም ሆኖ በሆነው ሁሉ ተደስ ቻለሁ» በማለት ሃሳባ ቸውን ገልጸዋል።
27 ለሚጠጉ ዓመታት ዩናይትድን ያሰለጠኑት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ክለቡን ለ13 የፕሪሚየር ሊግ ፤ አምስት የኤፍ ኤ ካፕና ለሌሎችም ለበርካታ ዋንጫዎች ክበር አብቅተዋል።
ከመጪው የውድድር ዘመን ጀምሮም በክለቡ ዳይሬክተርነትና አምባሳደርነት እያገለገሉ በኦልድትራፎርድ እንደሚቆዩ ታውቋል።

Previous Story

በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ የከረሙት አነጋጋሪው መ/ር ግርማ ወንድሙ እንዳያጠምቁ ታገዱ

melaku fenta
Next Story

ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ ፈንታን እና ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን አሠረ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop