“ኢሕአዴግን ጥለን እኛ እዚህ የምንቧቀስ ከሆነ ኢሕአዴግ ባይወድቅ ደስ ይለኛል” – ግርማ ሰይፉ (የፓርላማው አባል)

(ዘ-ሐበሻ) ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የማተሚያ ማሽን መግዢያ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ወደሚኒያፖሊስ የመጡት ብቸኛው ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ 3 ጥያቄዎች ከሕዝብ ቀርበውላቸው ነበር።
1ኛ. 33ቱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአንድነት ቆመዋል። በተለይም ምርጫውን ቦይኮት በማድረግ። እነዚህ 33 የሚባሉት ፓርቲዎች የራሳቸው አባል አላቸው ወይንስ ፈቃድ ብቻ ስለያዙ ነው ፓርቲ የተባሉት?

2ኛ. ኢሕአዴግ እርስ በራሱ ተጠላልፎ ወደ መውደቅ ደረጃ ላይ ያለ ይመስላል። ኢሕአዴግ ድንገት ቢወድቅ ሃገር ለመምራት የሚያስችል ብቃት አላችሁ ወይ?

3ኛ. ከሰሞኑ በአማራው ሕዝብ ላይ እየደረሰው ያለውን መፈናቀል በተመለከተ አንድነት ፓርቲ መግለጫ ሲያወጣ “የአማርኛ ተናጋሪዎች” እያለ ነው የገለጸው፤ እርስዎም ዛሬ ሲናገሩ “በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ የደረሰ መፈናቀል ሲሉ” ተደምጠዋል። የ”የአማራ ሕዝብ” ለማለት የማትፈልጉት ለምንድን ነው? – ነው ወይስ አማራን በአማራነቱ ካለመቀበል ነው?

አቶ ግርማ ሰይፉ ለነዚህ ጥያቄዎች የሰጡትን አነጋጋሪ ምላሽ ዘ-ሐበሻ በምስል ቀርጻ ይዛዋለች ይመልከቱት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የፋሲካ ዕርቅን ከሰሜን አየርላንድ ብንማርስ?
Share