May 1, 2013
1 min read

“ኢሕአዴግን ጥለን እኛ እዚህ የምንቧቀስ ከሆነ ኢሕአዴግ ባይወድቅ ደስ ይለኛል” – ግርማ ሰይፉ (የፓርላማው አባል)

(ዘ-ሐበሻ) ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የማተሚያ ማሽን መግዢያ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ወደሚኒያፖሊስ የመጡት ብቸኛው ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ 3 ጥያቄዎች ከሕዝብ ቀርበውላቸው ነበር።
1ኛ. 33ቱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአንድነት ቆመዋል። በተለይም ምርጫውን ቦይኮት በማድረግ። እነዚህ 33 የሚባሉት ፓርቲዎች የራሳቸው አባል አላቸው ወይንስ ፈቃድ ብቻ ስለያዙ ነው ፓርቲ የተባሉት?

2ኛ. ኢሕአዴግ እርስ በራሱ ተጠላልፎ ወደ መውደቅ ደረጃ ላይ ያለ ይመስላል። ኢሕአዴግ ድንገት ቢወድቅ ሃገር ለመምራት የሚያስችል ብቃት አላችሁ ወይ?

3ኛ. ከሰሞኑ በአማራው ሕዝብ ላይ እየደረሰው ያለውን መፈናቀል በተመለከተ አንድነት ፓርቲ መግለጫ ሲያወጣ “የአማርኛ ተናጋሪዎች” እያለ ነው የገለጸው፤ እርስዎም ዛሬ ሲናገሩ “በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ የደረሰ መፈናቀል ሲሉ” ተደምጠዋል። የ”የአማራ ሕዝብ” ለማለት የማትፈልጉት ለምንድን ነው? – ነው ወይስ አማራን በአማራነቱ ካለመቀበል ነው?

አቶ ግርማ ሰይፉ ለነዚህ ጥያቄዎች የሰጡትን አነጋጋሪ ምላሽ ዘ-ሐበሻ በምስል ቀርጻ ይዛዋለች ይመልከቱት።

Latest from Blog

እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
Go toTop