ወደ ቤንሻንጉል የተመለሱት የአማራ ተወላጅ ተፈናቃዮች እጅግ በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን የመንግስት ሃይሎች የአካባቢው ነዋሪዎች አማሮቹን እንዲያገሉ በተዘዋዋሪ መንገድ እየተወተ እንደሚገኝ ፍኖተነፃነት ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ።
እንደ ጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተፈናቅለው በፍኖተሰላምና በተለያዩ አካባቢዎች ተበትነው ከቆዩ በኋላ ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው እንዲመለሱ የተደረጉት የአማራ ተወላጅ ተፈናቃዮች እስካሁን እርሻ አለመጀመራቸውን አስታውቀዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ እንዳስታወቁት ወደ ቀድሞው ቦታቸው እንደሚመለሱ ተነግሯቸው ቢመጡም፣ ስፍራው ሲደርሱ የአካባቢው አስተዳዳሪዎች ለህብረተሰቡ አስቀድመው የተከራየነውን መሬት እንዳያስረክቡን በመቀስቀሳቸው ሊቀበሏቸው እንዳልፈለጉ አስረድተዋል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች በመንግስት አካላት “ተመልሰው የመጡት መሬታችሁን ሊቀሟችሁ ነው እንዳታቀርቧቸው” ተብለዋል የሚሉት ተፈናቃዮቹ “እርሻችንን እንዳትነኩ ወደ መሬታችንም እንዳትደርሱ” መባላቸውን ለጋዜጣው ተናግረዋል።
“በዚሁ ምክንያት እጅግ ለከፋ ችግር እንደተጋለጡ የሚናገሩት ተፈናቃዮቹ መንግስት በአካባቢው በአማራ ተወላጆች ላይ የሚፈፃመውን ግፍ እንዲያስቆም ተማፅነዋል፡፡” ያለው ዘገባው አክለውም “እኛ ያለ ባለመሬቱና ያለ መንግስት ፈቃድ የሰው መሬት አንነካም፤ ይህንን የአካባቢው የመንግስት አካላት ለህብረተሰቡ ሊያስረዱልን ይገባል፡፡ ሰርተን ለመኖ ተቸግረናል” ብለዋል ሲል ዘገባውን አጠናቋል።
“መሬትህን ሊቀሙ ነው የመጡት” በሚል የቤንሻንጉል ነዋሪ ተመላሽ አማራዎችን እንዲያገል በመንግስት ተላላኪዎች እየተሰበከ ነው
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!
1 Comment
Comments are closed.
we have to force on this discrimination