November 20, 2023
1 min read

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ከቅዱስ ላልይበላ ካህናትና ህዝብ ጋር የነበረው ውይይት

187204

 

 

አቡነ ኤርሚያስ ላይ አብይ ያቀደው አደገኛው የሞት ሴራ የገዳሙ አስተዳዳሪ የተደበቀውን እወነት ይፋ አደረጉ

4 Comments

  1. ሀ) የሃይማኖት ተቋማት የእረኝነት ሳይሆን የለየለት ምንደኝነት ሰለባ ከሆኑ ዓመታት ተቆጠሩ!

    ለ) እንዲህ አይነት ከጨካኝ (ከገዳይና አስገዳይ) የፖለቲካ ሥርዓት ካድሬዎች (ባለሥልጣናት) መካከል ተቀምጦ እና ከእነርሱ ባልተናነሰ ግልብና አደገኛ ስሜት እየተናጠ አገር ማለት ሰው እንዳልሆነ ሁሉ የገዳዮችን የጦር ሃይል ተዳፈራችሁ በሚል እረኛው ነኝ የሚለውን ህዝብ የሚያጎሳቁል አባት ተብየ አኳኋን የሚነግረን የገጠመንና እየገጠመን ያለውን ውድቀት አስከፊነት ነው!

    ሐ) እነዚህን አይነቶች አሳፋሪና ወራዳ አባቶች ተብየወች ከቻሉ ንፅሃ ገብተው ይቅርታ እንዲጠይቁ ካልሆን ግን የጨበጡትን መስቀል አርክሰውታልና ቢያንስ ባለመሳለም እውነተኛ አማኝነትን ማሳየት የግድ ነው!

    ሐ) አዎ! የአድርባይነት ክፉ ልክፍትን/ሰብእናን በሃይማኖታዊ አልባስ እና በንዋየ ቅድሳት ሸፍኖ (ተኩላነትን በበግ ለምድ ለብዶ/ሸፍኖ) መከረኛውን ህዝብ የማታለሉን አስቀያሚ ሰብእና ፈፅሞ ማስቀረት ባይቻልም ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ በቋፍ ላይ ያለውን ትውልድ ጨርሶ ከማበላሸቱ በፊት መገታት አለበት!!

  2. አዎ! የዚህ መከረኛ ህዝብ መከራና ውርደት ፍፃሜ ካጣባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ በሃይማኖት ስም የተደላደለ ዓለማዊ አኗኗር በመፍጠርና በማመቻቸት ክፉ ደዌ በተለከፉ አባት ነን ባዮች (እበትም ትል ይወልዳል እንዲሉ) እና የዘመናችን የቴክኖሎጅ ውጤቶች ለህዝብ ደህንነትና እድገት ሳይሆን ለተንቦረቀቀ የግልና የቡድን የአኗኗር ስልት መሣሪያነት በሚጠቀሙ አክቲቪስትና ኮሜዲያን ተብየ ወገኖች ምክንያት ነው!

  3. “…የጴንጤዎች የአቡነ ኤርሚያስን ፎቶ ፕሮፋይል ፒክቸራቸው ማድረግ። የኦሮሞ እስላሞች፣ እነ ኩሽ ሚዲያ፣ እነ ኦኤምኤን ጭምር ሰውየውን ማወደስ፣ እንደ እውነተኛ፣ ሃቀኛ፣ ትክክለኛ አባት ቆጥረው ለእርሳቸው መሟገት፣ የኦሮሞ አክቲቪስቶች “ቅዱስ አቡነ ኤርሚያስ” ብሎ ማሽቋለጥ፣ እነ ዳንኤል ክብረት ያን የዶሎዶመ የዛገ ብዕር አንስተው አቡነ ኤርሚያስን ለማንቆሎጳጰስ መጋጋጋጥ ሲታይ አገዛዙ በብፁዕ በአቡነ ኤርሚያስ ለገሰ በኩል ዐማራን ሙቀቱን በመለካት የእኛን ለዘብ ማለት አይቶ የተረዳው አብይ ጁላ ቡድን መሰል ውይይቶች በመላው ዐማራ እንዲካሄዱ ከባድ ጥድፊያ ላይ እንዳለ ከሁኔታዎች መገመት ይቻላል። ስለዚህ ፋኖ በሚችለው ሁሉ ስብሰባዎች እንዳይካሄዱ ማደናቀፍ ላይ ቢበረታ መልካም ነው። እኛ ደግሞ በፕሮፓጋንዳው በኩል መለብለብ ነው። ማስነጠስ ነው።

    ” …አቡነ ኤርሚያስ እንዳይወድቅ እጸልይለታለሁ ያሉት መንግሥታቸው ፀረ እምነት፣ ፀረ ዐማራ፣ ፀረ መላው ኢትዮጵያዊ ቡድን ነው። በዚህ ወቅት ይሄን አረመኔ አራጅ ቡድን እንደ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መስቀል አውጥቶ ያወግዙታል፣ እኔ ነኝ ያለ ሃይማኖተኛም ይህን መስክሮ ይሞታል እንጂ ዝም ሊል አይገባውም። የጾምና የጸሎቱን ሲኖዶሳዊ ዐዋጅ ጥቅም ስላለው ባንነቅፈውም፣ ነገር ግን የቅዱስ ሲኖዶሱን ምንነቱና ምንጩ ያልታወቀ የተፈጥሮ አደጋ (ቁጣ) የገጠመን ይመስል፤ አደጋውን ደብቀው ጾምና ጸሎት ማወጅ በአራዳ ሰፈር ገብቶ አራዳ አራዳ እንደመጫወት ይቆጠራል። እንደ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለዚህ ለአረመኔ ከጣሊያን ፋሽስት የከፋ ልቡሰ ሥጋ ጋኔል እንዳንገዛ መገዘት ከፈሩ ቢያንስ ቢያንስ ወንድ ከሆኑ ቢያንስ በስሱ እንኳ ወስላታ መንግሥት ገጥሞናልና እግዚአብሔር መፍትሄ ሰጥቶ እንዲያወርድልን ጸልዩ ማለት ማንን ገደለ። ይሄ ሁሉ ጭንቀት እነሱ ብልጥና አራዳ ሆነው ከደሀ መቀነት ፈትተው ያጠራቀሙትን ሚልዮን ቢልዮን በስባሽ ጥለውት እንደ አቡነ ሰላማ ለመንገደኛ ተናዘው የሚሄዱትን የደም ሀብት አሳስቷቸው ነው።

    From Zemedkun Bekele’s Telegram page

  4. እኝህ መልካም ሰው ሳያውቁ ተበሉ ያሳዝናል አሁንም እሳቸውን እንደ ብርሃኑና ዳንኤል ክብሪት ልናያቸው ነው? ይሄ ሰውዬ ምን አዚም እንዳለው እንጃ የነካው ሁሉ ይረክሳል አሁን በለጠ ሞላንና ካምፓኒውን ትላንት ያየ ማን እነሱ ናቸው ብሎ ይገምታል? ምንድነው የሚያቀምሳቸው? አይ ህዝቡ ሆድ ብሶታል ካሁኑ ጀምሯቸዋል እሳቸውም ከመካረር ብልጽግናም ሆነ ኦሮሙማ ስለማያድኗቸው ክህዝብ ጋር እልህ ባይያያዙ መልካም ነው ነገር ሳይካረር ወደ ህዝብ በቅንነት ይመለሱ አያዋጣም ብልጽግና ከሚያከብራቸው የህዝብ ክብር ይበልጣል፡፡ ፋኖ ውጣ ወራሪው የአብይ ጦር ይጠብቀን ማለት ምን ማለት ነው? ሁለቱንም ባይናቸው አይተዋል ለአብይ ጦር ልባቸው ለምን ስስ ሆነ ወልቃይትና ራያን አስበልቼ በሰላም እቆያለሁ ብለው አይገምቱም መቼም፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

2
Previous Story

አብይ አህመድ የገጠመው ተቃውሞ፣ ለ2 የከፈለው የድርድር ነገር፣ መከላከያ ይውጣ በተባለበት ብዙዎች ተገደሉ፣ ያወዛገበው የአቡነ ኤርሚያስ

keberowech 1 1 1
Next Story

የፋኖ ቀበሮዎች ስብሰባ በዛምበራ!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop