ጥንብ ባለበት ጂብ ይሰባሰባል

ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም ማለት ድሮ ነበር ፡፡ ዛሬ ላይ ግን ሰማይ በጭለማ መሬት በጭቃ በሆነበት ሀምሌ ወር ተደጋጋሚ ጉድ ይሰማል፡፡ ይህ ሀምሌ አስራ ዘጠኝ ቀን በጯሂት በዕለተ ዕረቡዕ በሬ አርዶ የኢትዮጵያን ኃይማኖት እና ታሪክ ማራከስ አዲስም ድንገተኛም አይደለም ፡፡ ከሁሉ በፊት ወያኔ/ ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም. በሰሜን ምዕራብ ህዝብ ተጋድሎ እና ፊታዉራሪነት ከደደቢት በርኃ ቀበሮ ጉድጓድ ስቦ በማዉጣት ለመኃል አገር እና ለማዕከላዊ መንግስት አብቅቷል፡፡

ሆኖም ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ እንዲሉ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ኢትዮጵያን ፣ ኢትዮጵያዊነትን እና መገለከጫዎችን ዕዉነታ እና ይሁንታ ማሳከር እና ማደናቆር ታሪክን ፣ዕምነትን እና ባህልን በሀሰተኛ ትርክት በማመሰቃቀል በጥላቻ እና በበታችነት ልክፍት ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ማሳዘን እና መበቀል እንደነበር ከደደቢት የተቀዳ የጥፋት ጎርፍ ነበር ፡ ለዚህም ብዙ የሚነገሩ ቢኖሩም የህወኃት ታጣቂዎች ደብረ ማርቆስ በወርኃ ሁዳዴ የነስኃ እና የትንሳዔ ፆም ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ላይ በንቀት እና በማን አለብኝነት በሬ አሳርደዉ አሻሻ ገዳሜ ሲሉ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ሞት ለዉያኔ ብሏል በዚህም ብዙ ሠዉ በጭካኔ ተገድሏል፡፡

ያኔ ነበር ህጻናት ሳይቀሩ አ.ህ.አ.ዴ.ግ የልጂ ልጂህ አይደግህ በማለት አምርረዉ አዉግዘዋል፡፡

ይኸዉና አበዉ ጠላት በመቶ ዓመቱ የወተት ጥርስ ነዉ እንዲሉ ዛሬም በግላጭ በጎንደር ጯሂት ገዳማት የሆነዉ ከብዙዎች አንዱ የጥላቻ ማሳያ እንጂ አዲስም መጨረሻም አይሆንም፡፡

አማኞች ጫማጨዉን አዉልቀዉ በሚከበሯት ቤ/ክርስቲያን የእምነት ተከታይ ያልሆነ ጓዳ ጎድጓዳ ያለምንም ከልካይ በሚወጣ በሚገባባት እንደ አዲስ አያወሩ መታከት ለምንም ለማንም አይሆንም ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  " የሰው ልጅ በኃይልህ ፈፅሞ አትመካ... " መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

የኢትዮጵያን ታላቅነት ፣ጥንታዊነት፣ታሪካዊነት ከኢትዮጵያ ቀደምት ሠሪዎች፣መስራቾች እና መሪወች ዕዉነት በማይቀበሉ እና በተከበሩበት መንበር ለመቀመጥ፤ በተጠቀሙበት ዕቃ ለመጠቀም በፍርኃት እና በጥላቻ የሚመለከቱትን ገዳማት ክፍት መሆን ከዚህ በላይ ቢሆን የሚደነቅ ቢኖር ሰባዊነትም ፤ዕምነትም የከዳዉ መሆን አለበት ፡፡
ዕምነት ፤ኃይማኖት ፣ባህል እና አገርን ለያይቶ ማየት ያስከተለዉ መዘዝ እና አድር ባይነት የበዛበት ቸልተኝነት ኢትዮጵያን ከሚጠሉት ጋር የሚስማሙ የጂብ ጓደኛ ከጥንብ ያደርሳል እንዲሉ የሆነዉ እና የሚሆነዉ ሁሉ የታወቀ እና የተጠበቀ ነበር ፤ ነዉ፡፡ “ጥንብ ባለበት ሁሉ ጂብ አይጠፋም ” እና ከታሪክ እና ከመከራ አለመማር አለመኖር ነዉ ፡፡
“አንድነት ኃይል ነዉ ”

Allen

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share