ግልጽ ደብዳቤ፣ ለፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ከልስጣን ይልቀቁ – ግርማ ካሳ

June 7, 2023

351172322 274102978332476 4246366242492567474 n 1 1

ወደዚህ ምድር ከመጡ 73 ዓመት ሆኖዎታል፡፡ ከደርግ ዘመን ጀምሮ፣ ፈረንሳይን ጨምሮ በበርካታ አገሮች የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስት በተለያዩ ሃላፊነት ላይ ሰርተዋል፡፡ በባንኪ ሙን ጊዜ፣ በናይሮቢ የተባበሩት መንግስት የአፍሪካ ቀን ጽ/ቤት ሃላፊ የነበሩ ሲሆን፣ ባንኪ ሙንን በመተካት አንቶኒዮ ጉቴሪዝ ሲመጡ፣ በተባበሩት መንግስታት ረዳት ዋና ጸሃፊ ስልጣን ፣ በአፍሪካ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ተጠሪ ሆነው፣ ያልዎትን ትልቅ ብቃት አሳይተዋል፡፡ በዚሁ ሁሉ ዘመን ለአገርዎት፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ላበረከቱት ትልቅ አስተዋጾ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ላመሰግንዎት እወዳለሁ፡፡

ከአምስት አመት በፊት ፣ በኦህዴድ/ብልጽግና ዘመን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ሆኑ፡፡ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ኢዩ ቢለዩ ቤተ መንግስት እየኖሩ ነው፡፡

ከማንም በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለውን እጅግ በጣም ልብ የሚሰብሩ፣ አንገት የሚያስደፉ፣ አሳዛኝ ክስተቶች፣ እርስዎንም እያሳሰበ፣ እያሳዘነ እንዳለ አልፎ አልፎ ከሚናገሩት ንግግሮች ማወቅ ይቻላል፡፡ ሆኖም ይኸው አምስት አመት አደረጉ፣ ነገሮች እየተባባሱ እንጂ እየተሻሻሉ አይደለም፡፡

የሊሴ ገብረማሪያም ተማሪ ነበሩ፡፡በፈረንሳይ አገር ሞንትፐሊዬ ከተማ በሚገኘም ዩኒቨቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርት ተምረዋል፡፡ በመሆኑም ለፈረንሳይ ታሪክ እንግዳ ይሆናሉ ብዬ አላስብም፡፡ እስቲ በፈረንሳይ ስለነበሩ ሁለት ሰዎች ትንሽ ላስታውስዎት፡፡ በ18ኛ ክፍለ ዘመን የሉዊስ 16ኛ ባለቤት የነበረችው የፈረንሳይ ንግስት፣ ማሪ አንትዋኔትንና በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ወቅት፣ መቀመጫውን በቪሺ(Vichy) ከተማ አድርጎ፣ በግማሹ የፈረንሳይ ግዛት ሲገዛ የነበረው ፊሊፕ ፔተን፡፡

በማሪ አንቷኔት ጊዜ፣ የፈረንሳይ ህዝብ ለከፍተኛ ችግርና ረሃብ ተጋልጦ ነበር፡፡ ህዝቡከሽግሩ የተነሳ ተቃውሞ ማሰማት ጀመረ፡፡ እዚያ ቨርሳይን ቤተ መንግስት ድረስ በመሄድ፡፡ ተቃውሞዉን ማሪ አንቷኔት ሰማች፡፡ “ምንድን ነው የሚፈልጉት ?” ብላ ጠየቀች፡፡ “ዳቦ እያሉ ነው” የሚል መልስ ተሰጣት፡፡ ማሪ አንቲአኔትም፣ “ታዲያ ለምን ኬክ አትሰጧቸውም” አለች ይባላል፡፡ ንግስቲቱ በቤተ መንግስት ተቀምጣ፣ ከቤተ መንግስት ውጭ ካለው ሁኔታ ጋር የተለየች፣ out of touch ነበረች፡፡

በሁለተኛ ዓለም ጦርነት የሂትለር ናዚዎች በመላው አውሮፓ ወረራ በፈጸሙ ጊዜ፣ ፈረንሳይም ቀድም ከተወረረችው አገር መካከል ነበረች፡፡ እነ ቻርልስ ደጎል ፣ በሽምቅ ውጊያ ናዚዎችን ሲዋጉ፣ ሌላው ፈረንሳዊው ፊሊፕን ፔተን ግን ከነ ሂትለር ጋር አብሮ መስራት ጀመረ፡፡ ለአጋረነቱም፣ ናዚዎች ፓሪስን ጨምሮ ሰሜናዊ ፈረንሳይ በቀጥታ ሲያስተዳድሩ፣ ደቡብን እርሱ እንዲያስተዳድር አደረጉት፡፡ የናዚዎች ተባባሪ ሆኖ ግማሹን ፈረንሳይ መግዛት ጀመረ፡፡ አገሩንና ህዝቡን ክዶ፡፡

ክብሩ ፕሬዘዳንት ሳህለ ወርቅ፣

ምን አልባት እንደ ማሪ አንቷኔት ቤተ መንግስት ውስጥ ስላሉ፣ በአገሪቷ እየተሰቃየ ያለው ህዝብ ስቃይና መከራ አልተሰማዎት ይሆን ? ናዚዛዊውና ዘረኛ የሆነውን የአብይ አህመድ ተረኛና ክፉ አገዛዝ እያዩ፣ የዚህ ስርዓት አካል መሆኗንዎ፣ ከሂትለር ጋር እንደ ተባበረው ፊሊፕ ፔተን ሆነው ይሆን?

በእድሜ ባለጠጋ ኖት፡ እግዚአብሄር ይመስገን፡፡ አገርዎትን በጥሩ ሁኔታ ለአስርተ አመታት አገልግለዋል፡፡

ታዲያ በመጨረሻው ሰዓታት ስምዎትን፣ ክብርዎትን ለምን ያበላሻሉ ? በታሪክስ፣ መጪው ትውልድ፣ “ከአብይ አህመድ ጋር ሲሰሩ የነበሩ ናቸው፣ ያ ሁሉ ጦርነት ሲደረግ፣ ያ ሁሉ ጄኖሳይዶች ሲፈጸሙ፣ አገር ስትተራመስ፣ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ቤተ መንግስት ነበሩ፣ የአገዛዙ አካል ነበሩ” ለምንስ ይባላሉ ? በዝምታዎት የተረኛው አገዛዝን እንደደገፉ ተድርጎስ ሊቆጠር አይችልም ወይ ? ማሪ አንቷኔት ከባሏ ሉዊስ 16ኛ ጋር በአደባባይ አንገቷ እንደተቆረጠው፣ እርስዎስ በህዝብ ቁጣ የማሪ አንቷኔት እጣ እንደማይደርስዎት ምን ማስተማመኛ አልዎት ? የሂትለር ጦር ሲሸነፍ፣ ከናዚዎች ጋር አብሮ ሲሰራ የነበረው የፊሊፕ ፔተን አይነት እጣስ፣ ተረኛው አገዛዝ በህዝብ ትግል ሲወገድ የርስዎም ሊሆን እንደሚችል አስበውታልን ?

ከትልቅ አክብሮት ጋር፣ “ታሪክዎትን በወርቅ ይጽፉ ዘንድ፣ ከህዝብ ወገን ይሆኑ ዘንድ እጠይቅዎታለሁ፡፡ “ስልጣንዎትን በመልቀቅ፣ ራስዎን በይፋ ከዘረኛው አገዛዝ በመለየት፣ የአገርዎንና የህዝብን ክብር ያስጠብቁ፡፡ ስምዎትን ያድሱ፡፡ ይሄን በማድረግዎ አገርን ለማዳን በሚደረገው ትግል ትልቅ አስተዋጾ ያደርጋሉ” እልዎታለሁ፡፡

 

የአብይ አህመድ የግፍ እስረኞች

347239179 780841970198999 3185231952645145302 n 1 1
#image_title

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop