May 15, 2023
14 mins read

የዝቅጠት፣ የሰብእና የህሊና እውርነት ጥግ! – ነአመን ዘለቀ

ተጠያቂነትና ግልጽነት የሌላቸው የጠ/ሚንስትሩ የቤተ መንግስት ግንባታና፣ የቅንጦት ፕሮጄከቶች 850 ቢሊዮን ብር (15 ቢሊዮን $) እንዲሰረዝ፣ የሚሊዮኖች ዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት እንዲሟላ መሞገት፣ መታገል ያስፈልጋል። ለውጭ መንግስታት፣ ተቋማት መሞገት፣ ማቅረብ አለብን። አገዛዙ 2 ቢሊዮን $ ከአለም ባንክ ብድር ይለምናል፣ በአጻፉ ደግሞ በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ሚሊዮኖች በቂ ትኩረት አይሰጥም፣ በመቶ ሺዎች ያፈናቅላል፣ ለልመና ይዳርጋል፣ በየመጠለያው ያስርባል። በሌላ በኩል ደግሞ የ 15 ቢሊዮን ዶላር+ ቤተ መንግስት ግን ይገነባል። የዝቅጠት፣ የሰብእና የህሊና እውርነት ጥግ !

የውጭ ብድሮችና ኢኮኖሚያዊ እርዳታዎች ቅድመ ሁኔታ እንዲደረግ በውጭ የምንገኝ ሀገር ወዳዶች ሁሉ መታገል፣ መሟገት ወቅቱ የሚጠይቀው ሰላማዊ የትግል ስልቶች አንዱ ነው።የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄዎች– ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ ሰብአዊ መብቶች፣ፍትህ፣ የህግ የበላይነት- እንዲከበሩ እንዲረጋገጡ ተደራጅተን፣ ተናበን መሞገት መታገል አለብን።

የኢትዮጵያ ህዝብ መሰረታዊ ፍላጎቶች-መጠለያ፣ ምግብ፣ ንጹህ ወሃ፣ መብራት፣ ለመሰረት ልማት- የብድሮችና የእርዳታዎች ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሆኑ መታገል፣ መሟገት የትግሉ አካል ነው፣
በጠ/ሚኒስትሩ አይዞህ ባይነት በኦሮሞ ብልጽግና መሪ ካድሬዎች የሚዘወረው፣ ኢ-ሕገ-መንግስታዊነት፣ጋጠ ወጥነት፣ ምዝበራና ሙስና፣ ሰፊ አፈና እና ሰብአዊ መብቶች ረገጣ፣ ነቀላና ፍንቀላ በአግባቡ ተሰንዶ፣ ለመንግስታት ለአለም አቀፍ ተቋማት ማቅረብ።
የኢትዮጵያ ህዝብ የሚገኝበትን አስከፊና፣ አስቆጪና አሳዛኝ ሁኔታ ቁብ የማይሰጣቸው በኦሮሞ ብልጽጋና የሚጋለቡ የዲጂታል ካድሬዎች መራሩን ሃቅ እይዋጥላቸውም። እንደ አለቆቻቸው ሞራለ አልቦ ስለሆኑ እእምሮና ህሊና እከራይተው የተጻፈላቸውን ይለጥፋሉ።

ኢትዮጵያን ከመፍረስ የመታደግ ጥሪ!

“ለውጥ”ተብሎ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ  በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በቀናነት ለማገልገል ጥረት አድርገዋል። በጦርነቱ ወቅት ከወገኔ ጋር ሞቸ አገሬን አድናለሁ ብለው ከሚኖሩባቸው አገራት ወደኢትዮጵያ በመሄድ አገራቸውን በቁርጥ ሰዓት አገልግለዋል። በዲፕሎማሲውና ሌሎች ዘርፎች ለአገራቸው በርካታ እገዛዎችን አድርገዋል። ይሁንና በለውጥ ስም የቡድንና የግለሰብና የቡድን ስልጣንና ጥቅምን ለማባከን ሲል ኢትዮጵያውያን ለአገራቸው የሚያደርጉትን እገዛ በዜሮ እያባዛ አገርን ለማፍረስ እየሰራ ይገኛል። የሰላም ስምምነት በተደረገ ማግስት ሌላ ጦርነት ከፍቶ ህዝብን እያሰቃየ ይገኛል። በኃይማኖት ተቋማት እጁን አስገብቶ ለማፍረስ እየሰራ ነው። በአዲስ አበባና በአካባቢው በንፁሃን ላይ የሚፈፀመውን ዘግናኝ ወንጀል በከተሞችም የዘር ፍጅት ሊፈፀም እንደሚችል አስደንጋጭ ምልክት ነው። በእውር ድንብስና የራስን ቡድን ለመጥቀም ብቻ የሚያደርገው አካሄድ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ምስቅልቅል ውስጥ አስገብቶታል። የራሱን ኢኮኖሚ ጥቅምና የገንዘብ ፍላጎት ለማሟላት አገራዊ ተቋማትን ባልተጠና መልኩ እየሸጠ ይገኛል። የመንግስት ሹማምንት በአገር ሀብት የቅንጦት ጥቅማጥቅም በሚጨመርላቸው በዚህ ወቅት ሰራተኛው ከዚህ ግባ በማይባል ገቢ የችግር ህይዎትን እየመራ ነው። የመንግስት የቅንጦት ድግስን በየጊዜው በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ለህዝብ እየቀረበ፣ በርካታ ዜጎች ኑሮን መሸከም አቅቷቸው ጎዳና ላይ ወድቀዋል። በአገር ውስጥ የሚደረገው ጦርነት አልበቃ ብሎ የጎረቤት አገር ጋር ወደ ግጭት ለመግባት በየመድረኩ ፉከራዎች ተጧጡፈዋል።

የብልፅግና መንግስት በኢኮኖሚው፣ በግጭት፣ ዜጎችን በማሰቃየት፣ አገራዊ ተቋማትን በሴራ የማፍረስና ሌሎች አደገኛ አካሄዶች አገር ለማፍረስ እየሰራ እንደሚገኝ አረጋግጧል። ይህ የብልፅግና ተግባር አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሊታገሉት የሚገባ ሲሆን በውጭ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያንም ከብልፅግና ጋር ባለመተባበር  ብሎም ጫና በማድረግ አገርን ለማዳን የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ ግድ የሚልበት ጊዜ ላይ ይገኛሉ።  የብልፅግና መንግስት ለግልና ለቡድን ጥቅምና ስልጣኑ የውጭ ምንዛሬን አብዝቶ የሚፈልግበት ጊዜ ላይ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ይህን በመገንዘብ ተገቢውን እርምጃ የሚወስዱበት ጊዜ ነው።  ከውጭ እርዳታና ብድር ከሚያገኘው  ዶላር በቁጥሩ ከፍ ያለውን የሚያገኘው ከዳያስፖራው እንደሆነ ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁንና ይህ ሁሉ የውጭ ምንዛሬ የሚውለው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ለማያስፈልጓቸው ወሳኝ ጉዳዮች ሳይሆን ለብልፅግና መንግስት  የግለሰብና ቡድናዊ ጥቅምና ስልጣን ነው።

በአሁኑ ወቅት የአገርን ኢኮኖሚ አዘቅት ውስጥ ያስገባው ብልፅግና ብድርና እርዳታን እንዲሁም ከዳያስፖራው የማገኘውን ዶላር የሚጠቀምበት ለባለስጣናቱ ቅንጦት እንጅ ለወደቀው ኢኮኖሚ ማገገሚያ እንዳልሆነ በበርካታ መረጃዎች የተረጋገጠ ሀቅ ነው። በአርሶ አደሩ ማዳበሪያ፣ ለህፃናትና እናቶች መድሃኒት መግዥያ መዋል የነበረበት የውጭ ምንዛሬ ለባለስልጣናት ስልክ መግዥያ፣ ውጭ አገር ሄደው መታከሚያ፣ ለልጆቻቸቸውና ቤተሰቦቻቸው የውጭ ትምህርት  ወጭ የሚውል ሆኗል። በጦርነቱ የወደሙ ተቋማትን መገንባት ሲገባ የብልፅግና ባለስልጣናት በእርዳታና ብድር በአገር ስም የተገኘን ገንዘብ በአሻጥር ወደ ውጭ አገር እያሸሹ እንደሚገኙም መረጃዎች አሉ። በጦርነቱ ወቅት ኢትዮጵያ ጫና ሲደረግባት በዲፕሎማሲው ከመታገል አልፎ በጦርነቱ ምክንያት ኢኮኖሚው እንዳይጎዳ በውጭ ምንዛሬ ወደ አገር በመላክ ሲያግዙ የነበሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ጠላት ተቆጥረው፣ በጦርነቱ ወቅት ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተቃራኒ ሆነው ኢትዮጵያን ሲወጉ የነበሩት ፀረ ኢትዮጵያ ተላላኪዎች ከየሚኖሩበት አገር ተጠርተው ኢትዮጵያ ውስጥ እየተዝናኑና ጥቅማጥቅም እየተሰጣቸው ያለው ለአገር ኢኮኖሚ ማገገሚያ መዋል ከነበረበት የውጭ ምንዛሬ ተቆንጥሮ ነው። ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ የሚላከው ገንዘው በንፁሃን ኢትዮጵያውያን ላይ ለተከፈተው ጦርነት ጥይት መግዥያ፣ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንን ለማጥላላት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚሰራ የብልፅግና ፕሮፖጋንዳ እየዋለ ይገኛል። በጥቅሉ  የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ለቤተሰቦቹም ሆነ ለአገሩ የሚልከው የውጭ ምንዛሬ ለሚፈለግለት አላማ ሳይሆን ለስርዓቱ የአገር ማፍረስ ፕሮጀክት እየዋለ ይገኛል። የብልፅግና መንግስት ብር እያተመ በጥቁር ገበያ ጭምር ዶላር እየገዛ ኢኮኖሚውን ምስቅልቅሉን አውጥቶታል። ለአገሩ ህልውና፣ ለህዝቡ ደህንነት  የታገለ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ በትንሹ የብልፅግና መንግስት ለሚያደርገውን የአገር ማፍረስ በዶላር ባለማገዝ፣ ከፍ ሲል ደግሞ በዲፕሎማሲና ሌሎች ጫናዎች አገር አድን ትግል ማድረግ ይጠበቅበታል።

አገር ወዳዶች ለህዝብና ለአገራቸው ብለው የሚልኩትን ገንዘብ ህዝብን መጨቆኛና አገር ማፍረሻ እንዲያደርግ የማይፈቅድ ከመሆኑም በላይ የሚላከው ዶላር ብልፅግና ያበላሸውን ኢኮኖሚ ከማዳን ይልቅ ይቀልጥ የከፋ እያደረገው የሚገኝ በመሆኑ ዳያስፖራው በቀናነት ለአገርና ለህዝቡ ብሎ የሚልከው ገንዘብ የዘር ጭፍጨፋና አገር ለማፍረስ ግብአት እንዳይሆን ደግሞ ደጋግሞ ሊያስብበት ይገባል። በቀጣይ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር የአፈፃፀም ሁኔታዎችን የምናቀርብ ሲሆን ለጊዜው ወደ አገር ቤት የሚላከው ገንዘብ ለህዝባችን መፍትሄ ከማምጣቱ ይልቅ መጨፍጨፊያው፣ የአገር ኢኮኖሚን ከማገዙ ይልቅ የብልፅግናን የቡድን ማፊያ  አካሄድ አግዞ የአገር ኢኮኖሚን የሚጎዳ፣ ከህፃናትና እናቶች መድሃኒት፤

ከአርሶ አደሩ ማዳበሪያ መግዥያ ተመጥቆ ለጦርነትና የዘር ጭፍጨፋ መደገፊያ እያገለገለ መሆኑን በመረዳት ለአገርና ህዝባችን ማነቂያ ገመድ እንዳናቀብል እንድናስብበትና አስቸኳይ የማስተካከያ እርምጃ እንድንወስድ አስፈልጓል። በጉዳዩ ላይ በርካታ አገር ወዳድና በሙያው የተካኑ ኢትዮጵያውያን ጭምር የተካተቱበት ግብረ ኃይል ተዋቅሮ እየሰራ ሲሆን እጃችን ላይ ባለው በዚህ መሳርያ አገር እንዳይጠፋ፣ ህዝብ እንዳይጨፈጨፍ ጥንቃቄ አድርገን፣ አገር እያፈረሰ ያለውን የብልፅግና ኃይል ተገቢ ትምህርት ልይሰጥበት ይገባል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop