June 23, 2022
3 mins read

የአቢይ አህመድ የጥላቻ ንግግር

Abiy Gragn Mohamed 1 1
#image_title
Abiy Gragn Mohamed 1 1
#image_title

ጥላቻና ዛፍ ተከላ፤ ቀይና አረንጓዴ አሻራ

የሕግ የበላይነት በአገራችን ተረጋግጦ ቢሆን ኖር ጠ/ር አብይ አህመድ በፓርላማው የመጨረሻው ቆይታቸው አዲስ አበባን እና የኦሮሞን ሕዝብን አስመልክተው ባደረጉት ንግግራቸው አንድ የጥላቻ እና አንድ የሐሰት መረጃ በማሰራጨት ሕግ በመተላለፍ ይጠየቁ ነበር፤
1ኛ/ “አዲስ አበባ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኦሮሞ ጥላቻ አለ” በሚል በተናገሩት ንግግራቸው የጥላቻና ሕዝብን ለግጭት የሚዳርግ ንግግር አድርገዋል፣ (አዲስ አበባ ውስጥ ለአንድ ወይ ለሌላ ብሔር ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች የሉም እያልኩ አለመሆኑ ይሰመርበት)

2ኛ/ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ በስም በተጠቀሱ አለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች የየአገሩ መዝሙር ይዘመራል የሚል የሐሰት መረጃ ለፓርላማውና ለሕዝብ አሰራጭተዋል፤

በእነዚህ ንግግሮቻቸው ብቻ እንኳ የጥላቻ እና የሐሰት መረጃዎች ስርጭቶችን ለመቆጣጠር እራሱ ፖርላማው ባወጣው ሕግ ሊጠየቁ ይገባ ነበር። ይህ ንግግር በአንድ ተራ ፖለቲከኛ ወይም አክቲቪስት ቢነገር በሕግ ማስጠየቁ እንደተጠበቀ ሆኖ ብዙም ላያስደምም ይችላል። ነገር ግን መቶ ሃ ሚሊዬን ሕዝብ ያለባትን እና የብዙ ብሔሮችና ሀይማኖቶች ስብጥር ያለባትን ሀገር የሚመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህን አይነት የጥላቻ እና ማህበረሰቦች መካከል ከፍተኛ ቅራኔን የሚፈጥር ንግግር፤ ሊያውም ፖርላማው ላይ ቀርበውና ሚሊዮኖች በሚያደምጧቸው መድረክ ላይ መናገራቸው ትልቅ የፖለቲካ ክሽፈት ብቻ ሳይሆን የህግ ጥሰትም ነው። በሌላው አለም ቢሆን ክሱንም ይቀምሳሉ፤ አፍንጫቸውንም ተይዘው ሕዝብን በይፋ ይቅርታ ይጠይቃሉ።

ትላንት መለስ ዜናዊ የቀበረው የጥላቻ መርዝ ዛሬ እርስ በርስ እያባላን ነው። ዛሬ ጠ/ር አብይ ከዛፋ እኩል የሚቀብሩት መርዝ የነገ መጥፊያችን ይሆናል። ሁለት የሚጋጩ አሻራዎች አረንጓዴና ቀይ አሻራ በአንድ መዳፍ ነው የሚሆነው። የጥላቻ እና የሐሰት መረጃ ስርጭት ይቁም! ቢያንስ ሕዝብን ይቅርታ ይጠይቁ። በሕግ አምላክ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

289421525 5646411158724029 2446822110881929514 n
Previous Story

ቅዱስ ፓትርያርኩ የወለጋና ጋምቤላውን ጭፍጨፋ አወገዙ

Abiy Ahmed parlament
Next Story

ይቺ ያንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት ዋጋዋ ስንት ቢሆን ነው ፓርላማው የቆጠባት? – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop