June 23, 2022
3 mins read

የአቢይ አህመድ የጥላቻ ንግግር

Abiy Gragn Mohamed 1 1
#image_title

ጥላቻና ዛፍ ተከላ፤ ቀይና አረንጓዴ አሻራ

የሕግ የበላይነት በአገራችን ተረጋግጦ ቢሆን ኖር ጠ/ር አብይ አህመድ በፓርላማው የመጨረሻው ቆይታቸው አዲስ አበባን እና የኦሮሞን ሕዝብን አስመልክተው ባደረጉት ንግግራቸው አንድ የጥላቻ እና አንድ የሐሰት መረጃ በማሰራጨት ሕግ በመተላለፍ ይጠየቁ ነበር፤
1ኛ/ “አዲስ አበባ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኦሮሞ ጥላቻ አለ” በሚል በተናገሩት ንግግራቸው የጥላቻና ሕዝብን ለግጭት የሚዳርግ ንግግር አድርገዋል፣ (አዲስ አበባ ውስጥ ለአንድ ወይ ለሌላ ብሔር ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች የሉም እያልኩ አለመሆኑ ይሰመርበት)

2ኛ/ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ በስም በተጠቀሱ አለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች የየአገሩ መዝሙር ይዘመራል የሚል የሐሰት መረጃ ለፓርላማውና ለሕዝብ አሰራጭተዋል፤

በእነዚህ ንግግሮቻቸው ብቻ እንኳ የጥላቻ እና የሐሰት መረጃዎች ስርጭቶችን ለመቆጣጠር እራሱ ፖርላማው ባወጣው ሕግ ሊጠየቁ ይገባ ነበር። ይህ ንግግር በአንድ ተራ ፖለቲከኛ ወይም አክቲቪስት ቢነገር በሕግ ማስጠየቁ እንደተጠበቀ ሆኖ ብዙም ላያስደምም ይችላል። ነገር ግን መቶ ሃ ሚሊዬን ሕዝብ ያለባትን እና የብዙ ብሔሮችና ሀይማኖቶች ስብጥር ያለባትን ሀገር የሚመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህን አይነት የጥላቻ እና ማህበረሰቦች መካከል ከፍተኛ ቅራኔን የሚፈጥር ንግግር፤ ሊያውም ፖርላማው ላይ ቀርበውና ሚሊዮኖች በሚያደምጧቸው መድረክ ላይ መናገራቸው ትልቅ የፖለቲካ ክሽፈት ብቻ ሳይሆን የህግ ጥሰትም ነው። በሌላው አለም ቢሆን ክሱንም ይቀምሳሉ፤ አፍንጫቸውንም ተይዘው ሕዝብን በይፋ ይቅርታ ይጠይቃሉ።

ትላንት መለስ ዜናዊ የቀበረው የጥላቻ መርዝ ዛሬ እርስ በርስ እያባላን ነው። ዛሬ ጠ/ር አብይ ከዛፋ እኩል የሚቀብሩት መርዝ የነገ መጥፊያችን ይሆናል። ሁለት የሚጋጩ አሻራዎች አረንጓዴና ቀይ አሻራ በአንድ መዳፍ ነው የሚሆነው። የጥላቻ እና የሐሰት መረጃ ስርጭት ይቁም! ቢያንስ ሕዝብን ይቅርታ ይጠይቁ። በሕግ አምላክ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop