April 10, 2023
11 mins read

የአማራ ክልል ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው – ግርማ ካሳ

የአማራ ክልል ውሎ፣ መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ/ም

ችግርና ቀውጥ በተነሳ ቁጥር ህዝብ መረጃ እንዳያገኝ ኔትዎርክ መዝጋት የለመደው፣ የአብይ አህመድ አገዛዝ በብዙ ቦታዎች የኦንተርኔትና የኔትዎርክ አገልግሎቶች እንዲቆራረጡ የማድረግ አሳፋሪና አፋራሽ ስራዎችን እየሰራ ነው፡፡
እንደዚያም ሆኖ ግን፣ የአብይ አገዛዝ ትልቅ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበረሰባዊና ወታደራዊ ክስረት እየደረሰበት እንደሆነ የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡
የህዝብ አመጽና ቁጣ

340276110 2987970248012957 2776254055951925986 n 1 1 1 1

ከመጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ፣ ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ ፣ እንዲሁም የአማራ ልዩ ኃይልንና ፋኖዎችን ትጥቅ አስፈታለሁ ያለውና፣ ለኦነጋዊው አብይ አህመድ አገዛዝ የሚታዘዘውን ጦር እንደልቡ እንዳይንቀሳቀስ ለማድረግ ፣ መንገዶችን የመዝጋት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በበርካታ የአማራ ክልል አካባቢዎች እየተደረጉ ነው፡፡
– በዋገመራ ዞን ፡ በኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታ፣ ሰቆጣ ከተሞች፣
– በሰሜን ወሎ ዞን ፡ በቆቦ፣ ወልዲያ፣ መርሳ፣ ኡርጌሳ፣ ጎብዬ፣ ጋሸና፣ መቄት፣ ዓላማጣ፣
– በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በይፋት/ራሳ፣ ምንጃር/አረርቲ፣ ሸዋሮቢት፣
– በምዕራብ/ደቡብና ሰሜን ጎንደር፣ በመተማ፣ ገንዳ ውሃ፣ ዳባት፣ ወረታ ፣ ፎገራ እንዲሁም ጎንደር ዙሪያ፣
– በምስራቅ ጎጃም ዞን፣ በደብረ ማርቆስ፣ ደጀን፣ አባይ በረሃ፣ ቢቸና፣ ግንደ ወይን፣ ደብረወርቅ፣ ሉማሜ አዋበል፣
– በምእራብ ጎጃም ዞን፣ በደምበጫ፣ ቡሬ፣ ጅጋ፣ መራዊ፣ ፍኖተ ሰላም፣
እና ሌሎች ቦታዎች፣ ባመረረ መልኩ ነው በብልጽግና አገዛዝ ላይ፣ ያለውን ብሶት፣ ምሬትና ተቃውሞ ህዝብ እየገለጸ ያለው፡፡
ጀነራል አበባው ታደሰ፣ በቴሌቪዥን መስኮት በመቅረብ፣ “ከትግራይ ተማሩ፣ እምቢ ያለ ካለ (አብይ አህመድን የማይታዘዝ ማለቱ ነው) ፣ ልክ እናስገባቸዋለን” በሚል ህዝቡን ለማስፈራራት የሞከረ ቢሆንም፣ የህዝቡ ግብረ መልስ ግን ተቃውሞዉን የበለጠ ማጠናከር ሆኗል፡፡
በጎንደር ከተማ ፣ “አብይ ኦነግ ነው”፣ “አማራ ተነስ” ፣ “ከልዩ ኃይላችን ጎን ነን”፣ “ብልጽግና ይውደም” የሚሉ መፈክሮች በትልቁ ተጽፈው በብዙ ቦታዎች ተለጥፈዋል፡፡ በደብረ ማርቆስ የህዝብ መዓበል የነበረ ሲሆን፣ ከዚህ ማዕበል፣ ውስጥ ይሰሙ ከነበሩ ድምጾች መካከል “ዘመነ ካሴ፣ ያሳምነው ልጅ”፣ “ይለያል ዘንድሮ”፣ ” አብይ አህመድ ይውረድ” የሚሉ ነበሩ፡፡
የአማራ ልዩ ኃይሎች ሁኔታ
============

339335692 1298744800989991 1883147134541045752 n 1 1 1

እስከ አሁን በተገኘው መረጃ፣ በብዙ ቦታዎች ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ ለማስፈታት የታቀደውና የታሰበው ሙሉ ለሙሉ ከሽፏል፡፡ ባህር ዳር ከተማ ጨምሮ ትጥቁን የፈታን አንድም የልዩ ኃይል አባል የለም፡፡
በአንዳንድ ቦታዎች ተኩስ የነበረ ቢሆንም፣ በብዙ ቦታዎች የመከላከያ አባላት የህዝቡን ቁጣ አይተው፣ እንዲሁም አብረውን በየጦር ሜዳው ሲዋጉ የነበሩ ወንድሞቻችን ላይ አፈሙዝ አናዞርም ብለው የተመለሱበት ሁኔታም እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በአንዳንድ ቦታዎች የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ ህዝቡን ልዩ ኃይሎችን፣ ፋኖዎች፣ እንዲሁም የመከላከያ አባላት በማነጋገር ፣ መረጋጋት እንዲመጣ ማድረጋቸውን እየሰማን ነው፡፡የአማራ ልዩ ኃይል የተለያዩ ብርጌዶችም አንድነታቸውንና ትስስራቸውን እያጠናከሩ ሲሆን፣ ከፋኖ ህዝባዊ ኃይል ጋር በመናበብና በንቅጀት መስራት ጀምረዋል፡፡
በጎንደር፣ በሰቆጣ፣ በመተማና በርካታ ቦታዎች የአማራ ክልል እናቶችና እህቶች፣ ለአማራ ልዩ ኃይሎች ያላቸውን ድጋፍና አጋርነት በማሳየት፣ እንጀራ፣ ዳቦ ፣ ስንቅ እየያዙ በመምጣት፣ ለልዩ ኃይል አባላት ድጋፋቸውንና አጋርነጋቸው እያሳዩ ነው፡፡
የአማራ ክልል መንግስትና ፊዴራሉ አገዛዝ
====================

339748900 160017223653443 5546421025620999721 n 2 1 1
#image_title

የአማራ ክልል መንግስት ምን ደረጃ ላይ እንዳለ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ በርካታ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንወክለዋለን የሚሉትን ህዝብ ሸሽተው፣ ወደ አዲስ አበባና ናዝሬት እንደሄዱ ይነገራል፡፡ የክልሉ ርእስ መስተዳደር ዶር ይልቃል ከፍያለ ፣ ለስራ ጉብኘት ወደ አውሮፓ ከሄዱበት የተመለሱ ሲሆን፣ ወደ ባህር ዳር ሄደው እንደነበረ፣ ሆኖም ግን ባህር ዳር ይቆዩ፣ ወደ አዲስ አበባ ሌሎችን ለመቀላቀል ይሄዱ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡
አንድ ግልጽ የሆነው ነገር ግን በአሁኑ ወቅት የአማራ ክልል ብልጽግና መንግስት ፣ እንደ መንግስት በባህር ዳር እየተንቀሳቀሰ እንዳልሆነ ነው፡፡ ከታችኛው የዞን አመራሮች ጋር ያለው የ ዕዝ ሰንሰለት ተበጥሷል፡፡
በፌዴራል መንግስቱና በመከላከያ አመራሮች ውስጥ ከፍተኛ የርስበርስ ውዝግቦች እንደተነሱም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ መንግስት የወሰደውን አፍራሽ ውሳኔ እንዲያነሳና የህዝቡን ጥያቄ በማዳመጥ ያለውን ችግር በውይይት መፍታት፣ ነገሮችን ማለዘብ ያስፈልጋል የሚሉ አመራሮች ቢኖሩም፣ አብይ አህመድ እነርሱም ሊሰማቸው አልቻለም፡፡ “አሰለጠንኩ፣ አደራጀሁ” ባለው ጦር በመመካትና፣ ምን አልባትም ህወሃቶች ያግዙኛል በሚል፣ የኃይል እርምጃ መውሰድ ፣ የተነሳዉን ተቃውሞ በጉልበት ለመጨፍለቅ፣ ከሰኞ ሚያዚያ 2 ቀን ጀምሮ፣ በኦነግ ጀነራሎች እንድትመራ ለማድረግ፣ በአማራ ክልል ኮማንድ ፖስት ለማቋቋም እንዳሰበ ምንጮ እየተናገሩ ነው፡፡
ማጠቃለያ
====
በአማራ ክልል ሕዝባዊ አመጽ ከተቀሰቀሰ አንድ ሳምንት ሆነው፡፡ ቀን በሄደ ቁጥር ተቃውሞው እየተጠናከረ እንጂ እየቀነሰ አይደለም፡፡
አብይ አሀመድ ጎንደር፣ ጎጃም እያለ የአማራውን ማህብረሰብ ለመከፋፈል ብዙ ሞክሯል፡፡ ሆኖም ሙከራዎቹ ከሽፈዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመላው የአማራ ክልል ፣ ምንም አይነት ልዩነት ሳይኖር ህዝቡ አንድ ሆኖ የተነሳበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በአማራ ክልል ያለው ህዝብ፣ አማራው ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን በአማራ ክልል እየተደረገ ላለው የሰላም፣ የፍትህ፣ የእኩልነት፣ በህይወት የመኖርና ኢትዮጵያን ከጥፋት የማዳን ትግል አጋርነቸውን እየገለጹ ነው፡፡
አገዛዙ የህዝብን ጥያቄ ከመስማትና ከመቀበል ውጭ ሌላ ምርጫ የለውም፡፡ ብረት ይዞ ህዝቡን ለማንበርከክ ከመጣ የሚገጥመው እድል መደምሰስ ነው፡፡ አገዛዙ ካልሰማ፣ ህዝባዊ ሰላማዊ እምቢተኝነት ከማድረግ ባለፈ ፣ የህዝብን ጥያቄ ለማፈን በተነሱት ላይ እርምጃዎች ለመውሰድ ማህበረሰቡ ሊገደድ እንደሚችል ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ አብይ አህመድና የብልጽግና ከፍተኛ አመራሮች፣ ከእሳት ጋር ባይጫወቱ ይሻላቸዋል፡፡ ህዝቡ እኮ ለሰላም፣ ለኢትዮጵያ አንድነት ብሎ እንጂ እየተጎዳም እስከአሁን የታገሳቸው፣ አንዴ ተነስቶ እፍ ቢላቸው ድራሻቸ አይገኝም፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop