February 18, 2023
3 mins read

የሚታረቀን መቼ የበለስ ፍሬ መጋጡን ትተን ነው? – በላይነህ አባተ

Adam and Eve 1

ጳጳስ መስቀል ጨብጦ ከሳጥናኤሉ ተከታይ ድርድር ሲያደርግ ውል ሲያስር፣
ተመልካች ውሉ እንደሚጠና በማመን “እንኳን ደስ አለን” እያለ ሲጨፍር፣
የሚመለከት መለኮት በአንክሮ የትዝብት መስኮት በርግዶ ከጠፈር፣
ምን በጎ ነገር አይቶብን መስልጦ ያውጣን ከገባንበት መቀመቅ ከችግር?

 
ሳጥናኤል ሰውን ለመጥለፍ እባብን መርጦ አፉን አስልቶ ሲልከው፣
ሄዋን አዳምም የበለስ ፍሬ መጋጡ ገደል የሚከት መሆኑ ሳይገባው፣
በቀለበት ውስጥ አዙሪት ስንሽከረከር አምስቱን ዘመን ደፈነው፡፡

 
የጥፋት ውሀው ቅጣቱ ምልክት ልምድና ትምህርት ሳይሆነው፣
ቃል ኪዳን ብሎ ያሳየው ቀስተ ደመና ወይም ደመ ነፍስ ሳይገታው፣
ጫካ ተሚኖር አውሬ አንሶ አንዱ ሌላውን በአገሩ ምድር አረደው፡፡

 
የጭራቅ የእርጉሞች ተንኮል በክፋት የሚልቅ ሰዶም ገሞራን፣
ሕዝብን ተሕዝብ አናክሶ በደም አበላ የሚያለብስ መሬቱን፣
የቅጣት እሳት በማምጣት አቃጥሎ አሁንም እንዳያነዳት ምድሪቱን፣

የእውነት የፍትህ ሰዎች በገዳማት ውስጥ ታላችሁ በፀሎታችሁ ታደጉን፣
አንድም የእውነት ሰው ቢገኝ መለኮት ቁጣዬን አስታግሳለሁ ስላለን፡፡

 

ሰውን በሥራው መዝን እያለ ደጋግሞ እያስተማረ መጣፉ በአዲስ ኪዳኑ ብሉዩ፣
በማያልቅ የውሸት ስብከት እየተነዳ ምሁር ተብየው ካህኑ ሼሁ መንጋው፣
የሙሴ ኢያሱ የዳዊት ዓይነት መሪዎች እንዴት ባገር ተዘርተው ይብቀሉ?

 

ተፈሪሳውያን አብረው እስጢፋኖስን በድንጋይ ወግረው የገደሉቱ፣
ተዳር ቆመውም ብትር እያቀበሉ በለው እያሉ በጩኸት ያስወገሩቱ፣
ዛሬም ተስልጣን ወንበር ቁጭ ብለው ፀፀት ሱባኤ ንስሃ ገዳም ሳይገቡ፣
ፍትህ ፍቅርና ሰላም እንዴት ተዘርተው በቅለው አብበው ለፍሬ ይብቁ?

 
በሐሰት ከሳሽ ነፍሰ ገዳዮች በድሎት ተወንበር ዙፋን ያለ ነቅናቂ ቁጭ ብለው፣
ስመው ጠቁመው ሰጪዎች አሁንም እንደ ፍልፈሎች ተራብተው በርክተው፣
ፍርድ አጣማሚ ዳኛዎች  ፍትህ መግደሉን እንደቀጠሉ በመዶሻቸው ጨፍልቀው፣
ሕዝብም እየተገዛ ዝምብሎ ተሸክሟቸው በጫንቃው እየተደፋም ተግራቸው፣
እግዜር ይቅር የሚለን ምን በጎ ተግባር የእውነትን መንገድ ስንከተል አይቶ ነው?
በእባቡ ምላስ እየተሰበክን መቼ የበለስ ፍሬ ግጦ መብላቱን ትተን ነው?

 

በላይነህ አባተ ([email protected])

የካቲት ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

 

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop